fa
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

رفتن به کانال در Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

نمایش بیشتر
4 480
مشترکین
-124 ساعت
+147 روز
+3130 روز
آرشیو پست ها
ወልቂጤ ••• የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓ ቋሚ የገቢ ምንጭ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስልን በማስተባበር የፕሪንት ቤት
+2
ወልቂጤ ••• የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓ ቋሚ የገቢ ምንጭ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስልን በማስተባበር የፕሪንት ቤት አበረከተ ! ! ! ••••••••••••••••••••••••••••••••• የካቲት 18 / 2018 ዓ.ል ••••••••••••••••••••••••••••••••• የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ጀመዓዎች ቋሚ የገቢ ምንጭ እንዲኖራቸው በማድረግ የፋይናንስ ነፃነት እንዲኖራቸው ማድረግ ከሚሰራቸው ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ሲሆን በዘንድሮው አመት ጀመዓዎችን ፕሮፖዛል እንዲያስገቡ በማድረግ አወዳድሮ አሸናፊ ለሆኑት የተሟላ ፕሪንት ቤት አበርክቷል:: አሸናፊ ከሆኑት ጀመዓዎች መካከል የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓ አንዱ ሲሆን ሙሉ ማቴርያሎችን ተቀብሎ ወደ ስራ እንደገባ የሕብረቱ ፕሬዚዳንት በአካል ተገኝቶ አይቷል:: የዩኒቨርሲቲው ጀመዓ አመራሮች መሠል ተግባራት የዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎችን በማጠናከር ረገድ አይተኬ ሚና እንዳላቸው የገለፁ ሲሆን ጀመዓዎች ለሚያደርጉት እንቅስቃሴ አስተማማኝ የሆነ የፋይናንስ ምንጭ እንደሚሆን ተናግረዋል:: ይህንንም ተከትሎም የያዙትን በማሳደግ ሌሎች ቋሚ የገቢ ምንጮችን በማቋቋም ጀመዓቸውን ከመጥቀም ባሻገር ለማህበረሰቡ አገልግሎት የሚውሉ ስራዎችን እንደሚሰሩ ገልፀዋል:: በስተመጨረሻም የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስልን እና ሕብረቱን አመስግነዋል:: ከዚህም በተጨማሪ የጀመዓው አመራሮች ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፕሬዚዳንት ሙሐመድአሚን ካሳው ጋር ስለወደፊት አቅጣጫ እና ጉዞ ፍሬያማ ውይይት አካሂደዋል:: https://t.me/EHEMSU

ተሻሻለ ተብሎም ያልተሻሻለው የመውጫ ፈተና ፕሮግራም ! ! ! ጁምዓ ሳምንታዊ በዓላችን እንደሆነ እየታወቀ: ከ5:30 - 7:30 ባለው ሰዓትም በመንግስት መስሪያ ቤቶች አገልግሎት እንደማይሰጥ በግልፅ
ተሻሻለ ተብሎም ያልተሻሻለው የመውጫ ፈተና ፕሮግራም ! ! ! ጁምዓ ሳምንታዊ በዓላችን እንደሆነ እየታወቀ: ከ5:30 - 7:30 ባለው ሰዓትም በመንግስት መስሪያ ቤቶች አገልግሎት እንደማይሰጥ በግልፅ ተቀምጦ ሳለ ... ትምህርት ሚኒስቴር ግን በጁምዓው ቀን ከ5:00 - 7:30 የመውጫ ፈተናን ለመስጠት ከ2 ቀን ቡሃላ ቀጠሮ ይዟል:: ተማሪዎች ድምፃቸውን እያሰሙ ያሉ ቢሆንም ጆሮ ዳባ ልበስ እንዳለ ነው:: ማሻሻያ አወጣሁ ብሎ ማስታዎቂያ ቢያወጣም ስለ ሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ ግን ምንም አይነት ማሻሻያ የለም:: አሁንም ቢሆን መሠል አካሄዶች ከሙስሊም ማህበረሰብ ተራርቆ ያለውን የትምህርት ሚኒስቴር ይበልጥ የሚያቃቅር እና የሚያቀያይም እንደሆነ ታሳቢ ተደርጎ በቶሎ ማስተካከያ በማድረግ ለተሰራው ጥፋትም በይፋ ይቅርታ መጠየቅ እና አጥፊዎችን መቅጣትም ይጠበቅበታል:: ተቋሙ የመላው ኢትዮጵያዊ እንደመሆነ በሕዝበ ሙስሊሙ ላይ ሸፍጥ የሚሰሩ አካላት ግማሹን ሕዝብ አግልለው የሚመሩትም ሆነ ለሀገር የሚሰሩት መልካም ስራ አይኖርምና በትልቁ ሊጠየቁ ይገባል:: መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ ይሰራጭ ! ! ! ፍትሕ ለሙስሊም ተማሪዎች ! ! !

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ሲሰበስበው የነበረውን ፊርማ ከደብዳቤ ጋር አስገባ ••••••••••••••••••••••• የአ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ሲሰበስበው የነበረውን ፊርማ ከደብዳቤ ጋር አስገባ ••••••••••••••••••••••• የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ላለፉት ጊዜያት ወደ 1141 ከሚሆኑ የዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች የሰበሰባቸውን ፊርማዎች ከደብዳቤ ጋር አስገብቷል። ህብረቱ በደብዳቤው ላይ በዩኒቨርሲቲው ከ2017 ዓ.ል ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው የዲሲፕሊን መመሪያ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ኒቃብ እንዳይለብሱ የሚደነግገው አንቀፅ እስካሁን ድረስ ተፈፃሚ መደረጉ በተማሪዎች ላይ ከፍተኛ ቅሬታንና የስነ-ልቦናን ጫና ያሳደረ መሆኑን ገልጿል። የሙስሊም ተማሪዎች ህብረትም ችግሩን ለመቅረፍ በተደጋጋሚ ጊዜ ውይይት ለማድረግ ጥረት ማድረጉናን በዩኒቨርሲቲው በኩል ግን የጉዳዩን አሳሳቢነት ባላገናዘበ መልኩ ችላ እየተባለ እንደቆየም አክሎ አስቀምጧል። በመቀጠልም ይህ ጥያቄ የሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ መሆኑን ለማረጋገጥ ከ1000 በላይ (1141 የሚሆኑ) ተማሪዎች በገዛ ፈቃዳቸው የፈረሙትን ፊርማ አያይዞ ማቅረቡን የገለፀ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው የጉዳዩን አሳሳቢነት ተገንዝቦ በአስቸኳይ አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ 6 ላይ ያለውን የኒቃብ ክልከላን እንዲያነሳና የተማሪዎችን ህገ-መንግስታዊ እና ሰብአዊ መብቶችን በተግባር እንዲያከብር አሳስቦ ተቋሙ ሊዚህ የተማሪዎች ድምፅ በአፋጣኝ አዎንታዊ ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ ተማሪዎች በሚሰማቸው ቅሬታ ለሚፈጠሩ የትኛውም አለመረጋጋቶችና ሂደቶች ህብረቱ ምንም አይነት ሀላፍትና እንደማይወስድና ሀላፍትናው የዩኒቨርሲቲው እንደሆነ አስቀምጧል። መብቶቻችንን ለማስከበር ከአሁን በኋላ የቀረን ምንም አይነት ትዕግስት የለም!!! @aaumsu

Dhugaaf, Haqaf, fi Bilisummaaf daqiiqaa 2 haa kenninu! ​"FEDERATION OF AFRICAN LAW STUDENTS!" – Barattoonni mirga isaanii ilaalchisee haalli mana barumsaa keessatti qaban maal akka fakkaatu qorannoo gaggeessaa jira. Qorannoon kun akkuma xumurameen jijjiiramni akka dhufuuf akka hojjetu beeksiseera. ​Gaaffilee hedduun dhiyaatanis, gaaffiin "Yuunivarsiitiin keessan mirga bilisummaa amantii keessanii ni kabaja?" jedhus keessatti argama. Kanaafuu, sarbamni mirga amantii nurra gahaa jiru hundaaf akka gahuuf, filannoo dhugaa jiru ibsu filadha. Yoo EMAIL dhaan isin quunnaman, barreeffama bal'aa furaa dhiyeessaafii. ​Guutuudhaaf hidhaa (link) kana fayyadamaa: https://forms.gle/YRjk2qqPqaNPHieX7 ​Dhugaaf Haqaf Bilisummaaf ... Share haa taasifamu! ! ! https://t.me/EHEMSU

ለሐቅ: ለፍትሕ: ለነፃነት 2 ደቂቃ እንስጥ! "FEDERARION OF AFRICAN LAW STUDENTS!" - ተማሪዎች መብታቸውን አስመልክቶ በትምህርት ቤት ያላቸው ሁኔታ ምን ይመስላል የሚል የዳሰሳ
ለሐቅ: ለፍትሕ: ለነፃነት 2 ደቂቃ እንስጥ! "FEDERARION OF AFRICAN LAW STUDENTS!" - ተማሪዎች መብታቸውን አስመልክቶ በትምህርት ቤት ያላቸው ሁኔታ ምን ይመስላል የሚል የዳሰሳ ጥናት እየሰራ ይገኛል:: ጥናቱ እንዳለቀም ለውጥ ይመጣ ዘንድ እንደሚተጋ አሳውቋል:: የተጠቀሱ ብዙ ጥያቄዎች ቢኖሩም "ዩኒቨርሲቲያችሁ የሀይማኖት ነፃነታችሁን ያከብራል?" - የሚል ጥያቄም አለው:: ስለሆነም እየደረሱብን ያሉት የሀይማኖት የመብት ጥሰቶች ለሁሉም ይደርሱ ዘንድ እውነታውን የሚገልፀውን ምርጫ ምረጡ:: በEMAIL Contact ካደረጓችሁ ዝርዝር ነገር አስቀምጡላቸው:: ለመሙላት https://forms.gle/YRjk2qqPqaNPHieX7 ይጠቀሙ:: ለእውነት ለፍትሕ ለነፃነት ! ! !

ከጁምዓ ቀን የስራ ሰዓት ጋር ተያይዞ ያለው አዋጅ በዚህ ዶክመንት ውስጥ ይገኛል:: በዶክመንቱ ገፅ 86 እና 87 ላይ እንደተቀመጠው አዋጁ ጁምዓ ቀን የስራ ሰዓት ከጧት እስከ 5:30 ከሰዓት ደግሞ ከ7:30 ጀምሮ እንደሆነ ይደነግጋል:: https://t.me/EHEMSU

ትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናን በጁምዓ ቀን ከ5:00-7:30 ለመስጠት ፕሮግራም አውጥቷል! ሆን ብሎ በሚመስል መልኩ አመት በአመት የሙስሊም ተማሪዎችን መሠረታዊ መብቶችን የሚጥሱ ፕሮግራሞችንና አ
ትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናን በጁምዓ ቀን ከ5:00-7:30 ለመስጠት ፕሮግራም አውጥቷል! ሆን ብሎ በሚመስል መልኩ አመት በአመት የሙስሊም ተማሪዎችን መሠረታዊ መብቶችን የሚጥሱ ፕሮግራሞችንና አሰራሮችን የሚያወጣው ትምህርት ሚኒስቴር በዘንድሮው አመትም በጁምዓ ቀን ከ5:00 - 7:30 EXIT EXAMን ለመፈትን ፕሮግራም አውጥቷል:: ባለፈው አመት ተመሳሳይ ፕሮግራም አውጥቶ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የተማሪዎችን ጥያቄ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ይዞ ካቀረበ ቡሃላ ማስተካከያ ማድረጉ ይታወሳል:: በዘንድሮው አመትም ተመሳሳይ ስህተቶ መፈፀሙ በተማሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ የፈጠረ ሲሆን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚከውናቸው ተግባራት ሙስሊም ተማሪዎችን ታሳቢ ያላደረገና መብታቸውን የሚጥስ መሆኑን ያመላከተ ነው:: የጁምዓ ቀን በመንግስት ተቋማት ውስጥ ከ5:30 - 7:30 አገልግሎት እንደማይሰጥ በአዋጅ የተደነገገ እና ቀኑም የሙስሊሞች ሳምንታዊ በዓል ከመሆኑ ባሻገር ከ5:30 - 7:30 ባለው ሰዓት ውስጥ የጁምዓ ስግደት የሚፈፀምበት መሆኑ እየታወቀ ይህንን በመግፋት የወጣው ፕሮግራም ፍፁም ስህተት እንደሆነ ተመላክቷል:: ስለሆነም ትምህርት ሚኒስቴር በተደጋጋሚ እየፈጠራቸው ላሉት ስህተቶች ሙስሊም ተማሪዎችን ይቅርታ በመጠየቅ: ይህንን ስህተት በተደጋጋሚ የሚፈጥሩ አካላት ላይ እርምጃ በመውሰድ ፈተናው ከመድረሱ በፊት ማስተካከያ ያደርግ ዘንድ እንጠይቃለን::

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ለሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓ ቋሚ የገቢ ምንጭ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስልን በማስተባበር የፕሪንት ቤት አበረከተ ! !
+1
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ለሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓ ቋሚ የገቢ ምንጭ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስልን በማስተባበር የፕሪንት ቤት አበረከተ ! ! ! ••••••••••••••••••••••••••••••••• የካቲት 9 / 2018 ዓ.ል ••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጀመዓዎች ቋሚ የገቢ ምንጭ እንዲኖራቸው በማድረግ የፋይናንስ ነፃነት እንዲኖራቸው ማድረግ ከሚሰራቸው ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ሲሆን በዘንድሮው አመት ጀመዓዎችን ፕሮፖዛል እንዲያስገቡ በማድረግ አወዳድሮ አሸናፊ ለሆኑት የተሟላ ፕሪንት ቤት አበርክቷል:: አሸናፊ ከሆኑት ጀመዓዎች መካከል ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓ አንዱ ሲሆን ሙሉ ማቴርያሎችን ተቀብሎ ወደ ስራ እንደገባ የሕብረቱ ፕሬዚዳንት በአካል ተገኝቶ አይቷል:: የዩኒቨርሲቲው ጀመዓ አመራሮች መሠል ተግባራት የዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎችን በማጠናከር ረገድ አይተኬ ሚና እንዳላቸው የገለፁ ሲሆን ጀመዓዎች ለሚያደርጉት እንቅስቃሴ አስተማማኝ የሆነ የፋይናንስ ምንጭ እንደሚሆን ተናግረዋል:: ይህንንም ተከትሎም የያዙትን በማሳደግ ሌሎች ቋሚ የገቢ ምንጮችን በማቋቋም ጀመዓቸውን ከመጥቀም ባሻገር ለማህበረሰቡ አገልግሎት የሚውሉ ስራዎችን እንደሚሰሩ ገልፀዋል:: በስተመጨረሻም የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስልን እና ሕብረቱን አመስግነዋል:: :- እንደ ሕበረት መሠል ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸው የምናምን ሲሆን የዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎች በፋይናንስ ተጠናክረው ለሀገር የሚጠቅም ስራ አበርክተው ይሰሩ ዘንድ ማህበረሰቡ እንዲያግዝ ጥሪያችን ነው::

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጋር ውይይት አደረገ ! ! ! ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የካቲት
+3
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጋር ውይይት አደረገ ! ! ! ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የካቲት 9 / 2018 ዓ.ል ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች: ከጀመዓው የሹራ አባላት እንዲሁም አሚሮች ጋር በጀመዓው እንቅስቃሴ እና ክንዋኔዎች ዙሪያ ውይይት አካሂዷል:: በውይይቱ ወቅት ከሕብረቱ ጋር በመሆን የዩኒቨርሲቲ ጀመዓ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ለማስከበር ሲደረጉ የነበሩ እንቅስቃሴዎች እንዲሁም እንደጀመዓ ሲሰሩ የነበሩ እና ሊሰሩ በታቀዱ ስራዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል:: የዩኒቨርሲቲው ጀመዓ ሕብረቱ እያደረገ ላለው መልካም እንቅስቃሴ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን የሕብረቱ ፕሬዚዳንት ሙሐመድአሚን ካሳውም ሕብረቱ ጀመዓዎችን ለማጠናከር የጀረውን ውጥን በቀጣይነት እንደሚሰራበት ገልፇል:: በስተመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው ጀመዓ እያከናወናቸው ያሉት እንቅስቃሴዎች ተስፋ ሰጪ እንደሆኑ ተመላክቷል::

የ3ቱ ፎቶዎች ወግ ተምሳሌት ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ካምፓስ ጀመዓ ! ! ! የመጀመሪያው ፎቶ ከአንድ አመት እና 11 ወራት በፊት የነበረ የተማሪዎች መስጂድ ነው:: ክረምት ሲመጣ የሚያፈስ: ፀሐዩ
+2
የ3ቱ ፎቶዎች ወግ ተምሳሌት ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ካምፓስ ጀመዓ ! ! ! የመጀመሪያው ፎቶ ከአንድ አመት እና 11 ወራት በፊት የነበረ የተማሪዎች መስጂድ ነው:: ክረምት ሲመጣ የሚያፈስ: ፀሐዩ ሲበረታ የሚያቃጥል ነበር:: ይህን ከአላህ ጋር በጥረታቸው ለማስተካከልና የተሻለ እና ሁሉንአቀፍ የሆነ መስጂድ ለመገንባት የቆረጡ ተማሪዎች መንገድ ጀመሩ:: የ2ተኛው ፎቶ ደግሞ ከአንድ አመት እና 3 ወራት ጥረት ቡሃላ በአላህ ፈቃድ የደረሱበት ደረጃ ነበር:: በስተመጨረሻ ላይ የሚታየው ፎቶ ሁለት አመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እውን የሆነን ሕልም ያሳያል:: በትብብር ከተለፋ እና ከተሰራ ከየት መድረስ እንደሚቻል እውነተኛ ተምሳሌት ናቸው:: ይህ ደግሞ የስራቸው መጨረሻ አይደለም:: ለጀመዓቸው ቋሚ የገቢ ምንጭ የሚያስገኙ ፕሮጀክቶችን ነድፈው እውን ለማድረግ በርትተው እየሰሩ ነው:: አላህ ካሰቡት በላይ ስኬትን ይወፍቃቸውና!!! እኔስ? አንተስ? አንቺስ? እኛስ? ሌሎች ጀመዓዎችስ? ምን ሰራን? ምንስ ለመስራት ውጥን ይዘናል?

ልፋታቸው ከውጤት በቅቷል! በድጋሜም አመስግነዋል!! የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ካምፓስ ተማሪዎች ከአመታት በፊት የነበረባቸውን የመስጂድ እጦት ለመቅረፍ ላቀረቡት ጥሪ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊ
+2
ልፋታቸው ከውጤት በቅቷል! በድጋሜም አመስግነዋል!! የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ካምፓስ ተማሪዎች ከአመታት በፊት የነበረባቸውን የመስጂድ እጦት ለመቅረፍ ላቀረቡት ጥሪ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች አስተባባሪነት አብዛኞቻችሁ ተረባርባችሁ ነበር:: እነሆ ዛሬ ከፍፃሜ ደርሰዋል:: በድጋሜም ምስጋናቸውን አድርሰዋል:: እንኳን ደስ አለን!!! አላህ ያበርታቸው!!! አላህ ይቀበላችሁ!!""

ሰላሌ ዩኑቨርሲቲ ጀመዓ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት እና አመራሮች ጋር በነበረው ውይይት ረመዷን ላይ በሚያስፈልጉ ዝግጅቶች ዙሪያ ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ ላይ እንደደረሱ ገልፀዋል:: ካፌ ላይ ከሚኖሩ የስሁር እና ኢፍጣር ዝግጅቶች በተጨማሪ የሶላት ሁኔታም ተነስቶ ነበር:: ከዚህም በተጨማሪ የጁምዓ ቀን የትምህርት ክ/ጊዜ ከጧት እስከ 5:30 ከሰዓት ደግሞ ከ7:30 ጀምሮ እንዲሆን ከስምምነት ደርሰዋል:: :- የሚበረታታ ለውጥ ነው:: ተማሪዎች ተስፋ ሳይቆርጡ በሚያደርጉት ሰላማዊ ጥያቄ ምክንያት በአንድ ወቅት ለሙስሊም ተማሪዎች በጣም የማይመች የነበረው ግቢ መጠነኛ ማሻሻያ እያደረገ ነው:: ጥያቄዎች መቀጠል ያለባቸው ሲሆን ሌሎች ጀመዓዎችም መሠል ልምዶችን በመውሰድ ፍትሐዊ የሆነ ከባቢ እስኪፈጠር እና አሰራሮች እስኪስተካከሉ ድረስ መጠየቅን ልማድ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል::

ረመዷን ከደጅ ደርሷል ... የሚከተሉት ጥቆማዎች ለዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎች ...   ♢ ረመዷን ውስጥ ከሌላው ወር የተለየ የምግብ ፕሮግራም: በር ላይ የተለየ የመግቢያ መውጫ ሰዓት እንዲሁም በመሐል የሚዘገጃጁ ፕሮግራሞች ቅድመ ዝግጅት ስለሚያስፈልጋቸው ከአሁኑ ቀድማችሁ ፎርማል በሆነ መልኩ አሳውቋቸው:: በተለይም የመጀመሪያው ቀን ላይ ስሁር የሚዘነጋበት ሰፊ እድል ስላለና በየአመቱ እየተደጋገመ ስለሆነ ቀድማችሁ ከአሁኑ አሳውቋቸው:: ♢ እስከ ዛሬ ስሁር የማይዘጋጅላችሁ ግቢዎች መብታችሁ ስለሆነ በዘንድሮው እንዲያስተካክሉ አድርጉ ♢ እስከ ዛሬ ለስሁር ሰራተኛ የማይቀጥሩላችሁ ግቢዎች መብታችሁ ስለሆነ በዘንድሮው እንዲያዘጋጁ አድርጉ ♢ እስከ ዛሬ ለተራዊህ እና ተሐጁድ መውጣትን የማይፈቅዱላችሁ ግቢዎች መብታችሁ ስለሆነ በዘንድሮው እንዲያስተካክሉ አድርጉ ♢ እስከ ዛሬ ከግቢው ማህበረሰብ ጋር የምትሰባሰቡበትን ፕሮግራም የማታዘጋጁ ጀመዓዎች ፋይዳው ላቅ ያለ ነውና ከዘንድሮ ጀምራችሁ ብታዘጋጁ ይመከራል አላህ ያግዘን ... በርታ በሉ ... አንድ ነገር አስተካክሎ ማለፍ በራሱ ትልቅ ነገር ነው ! ! ! https://t.me/EHEMSU

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት (AAUMSU) በኒቃብ በሚለብሱ እህቶቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለውን መድልዎ እና የመብት ጥሰት በዘላቂነት ለመፍታት የሚያደርገውን ጥረት በመቀጠል፣ ለ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት (AAUMSU) በኒቃብ በሚለብሱ እህቶቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለውን መድልዎ እና የመብት ጥሰት በዘላቂነት ለመፍታት የሚያደርገውን ጥረት በመቀጠል፣ ለፌዴራል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ይፋዊ የቅሬታ ደብዳቤ አስገባ። ••••••••••••••••••••••••••• ህብረቱ ለተቋሙ ባስገባው ደብዳቤ ዩኒቨርሲቲው ባወጣው "የተማሪዎች የሥነ-ምግባርና የዲሲፕሊን ውስጠ ደንብ" ላይ ማንነትን ለመለየት በሚል ኒቃብ መልበስን መከልከሉ እና ይህም እህቶቻችን በትምህርታቸው ላይ ከፍተኛ እንግልት እንዲደርስባቸው ማድረጉ ገልጿል። ህብረቱ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ለማድረግ ጥረት እንዳደረገና የመፍትሔ ሀሳቦችንም እንዳቀረበ የጠቀሰ ሲሆን፣ በዩኒቨርሲቲው በኩል ተቀባይነት ሳያገኝ እንደቀረ ገልጿል። ይህ ክልከላ ደግሞ የሀገሪቱን ህገ-መንግስት እና አለምአቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌዎችን የሚፃረር ከመሆኑም በላይ፣ ተማሪዎች በነፃነት የመማር መብታቸውን እየጣሰ ይገኛል። በመጨረሻም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው ተቋም እንደመሆኑ ጉዳዩን በመገምገም ለተማሪዎቹ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ አሳውቋል። የዚህም ደብዳቤ ግልባጭ በተመሳሳይ ለፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት የገባ ቢሆንም ለመቀበል ፍቃደኛ አለመሆናቸውንም ለማሳወቅ እንወዳለን #እንደለበሰች_ትማራለች ©️ aaumsu @MohammadamminKassaw

የአዲስ አበባ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየተደረገ ስላለው የመብት ጥሰትን አስመልክቶ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ደብዳቤ አስገባ ህብረቱ ለተቋሙ
የአዲስ አበባ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየተደረገ ስላለው የመብት ጥሰትን አስመልክቶ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ደብዳቤ አስገባ ህብረቱ ለተቋሙ ባስገባው ደብዳቤ ዩኒቨርሲቲው ባወጣው "የተማሪዎች የሥነ-ምግባርና የዲሲፕሊን ውስጠ ደንብ" ላይ ማንነትን ለመለየት በሚል ኒቃብ መልበስን መከልከሉ እና ይህም እህቶቻችን በትምህርታቸው ላይ ከፍተኛ እንግልት እንዲደርስባቸው ማድረጉ ገልጿል። በተጨማሪ ህብረቱ ለዩኒቨርሲቲው አመራር ምክንያታዊ አማራጮችን ቢያቀርብም፣ የዩኒቨርሲቲው አመራር ይህንን ሳይቀበል ቀርቷል። ይህ ድርጊት በኢትዮጵያ ህገ-መንግስት የተቀመጡትን የሃይማኖት ነፃነት፣ የእኩልነት እና የመማር መብቶችን የሚጥስ ከመሆኑም በላይ፣ እንደ UDHR እና ACHPR ያሉ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችንም የሚጋጭ መሆኑ ተብራርቷል። በመጨረሻም ህብረቱ ጉዳዩን የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በቅርበት እንዲከታተለው፣ ፈጣን ምርመራ እንዲያደርግ እና በዘላቂነት መፍትሄ እንዲያገኝ ጥሪ አቅርቧል። በተጨማሪ ህብረቱ የደብዳቤውን ግልባጭ ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት ለማስገባት የሞከረ ቢሆንም ነገር ግን ደብዳቤውን ለመቀበል ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል ህብረታችን የተማሪዎችን መብት ለማስከበር በሰላማዊ እና በህጋዊ መንገድ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል። #እንደለበሰች_ትማራለች @aaumsu

የAAU ሙስሊም ተማሪዎችን የሰብዓዊ መብት ጥያቄ አስመልክቶ ዶክተር ሳሙኤል በሰጡት መልስ ላይ የተነሱ ጥያቄዎች እና መጠነኛ ማብራሪያዎች:- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደ ኒቃብ ያሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን የሚገድብ መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ፣ ለቀረቡ ጥያቄዎች የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የሰጡት ምላሽ ከመንደርደሪያ እስከ መደምደሚያው መሠረታዊ የሕግ እና የፅንሰ-ሐሳብ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ሆኖ ተገኝቷል። ፕሬዚዳንቱ ትምህርት ማህበራዊ ልማት ስለሆነ ከባህል፣ ከሃይማኖት እና ፖለቲካ ተፅዕኖ ውጪ ይፈፀማል በሚል መንደርደሪያ ንግግራቸውን ቢጀምሩም፣ አንዲት ሙስሊም ተማሪ ኒቃብ በመልበሷ በትምህርት ሂደት ላይ የምታሳድረው "ሃይማኖታዊ ተፅዕኖ" ምን እንደሆነ ግን ግልጽ አይደለም። ሴኩላር እንዲሆን የሚፈለገው የትምህርት ስርዓቱ እንጂ የተማሪው ማንነት አለመሆኑ ሊሰመርበት ይገባል። እንደ ኒቃብ ያሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን መገደብና "ካላወለቃችሁ አትማሩም" ወይም "የዩኒቨርሲቲውን አገልግሎት አታገኙም" ማለት ዓለምአቀፋዊ የሆነውን ሰብዓዊ መብት ከመጋፋትም በላይ፣ "ሃይማኖትህን ጥለህ ካልገባህ አትማርም" የሚል አግባብነት የሌለው ጣልቃ-ገብነት በመሆኑ የሴኩላሪዝምን መርህ ይጥሳል። ተማሪውንም ከሃይማኖቱ ነጥሎ ምን ዓይነት ትውልድ ለመፍጠር ታስቦ እንደሆነ የሚያጠያይቅ ሲሆን፣ ሃይማኖት አልባነትም ራሱን የቻለ እሳቤ መሆኑን ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች የሚሰወር አይሆንም። ፕሬዚዳንቱ አክለውም ሳይንስ ሰውን ከመጣበት የዝግመተ ለውጥ (Evolution) ታሪክ አንጻር እንደሚያስተምርና ተማሪውም ይህ ከሃይማኖቴ ጋር ይጋጫል ብሎ "አልፈተንም" ማለት እንደማይችል ጠቅሰዋል። ይህ ትክክለኛ ገለፃ ቢሆንም፣ ከተማሪዎቹ የእምነት ነፃነት ጥያቄ ጋር ግን በቀጥታ አይገናኝም። ተማሪዎች እያነሱ ያሉት ጥያቄ "ትምህርቱ ከእምነቴ ጋር ስለሚጋጭ አልማርም" የሚል ሳይሆን፣ ትምህርቱን እየተማሩ እምነታቸው የሚያዘውን መለኮታዊ አለባበስ በተለይም የኒቃብ አጠቃቀምን የመተግበር መብታቸው እንዲከበር ነው። ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ሳይንሳዊ እውቀትን እንዲቀስሙ የማድረግ መብት እንዳለው ሁሉ፣ የአንድን ተማሪ ሃይማኖታዊ አለባበስ "አውልቅ" ብሎ የማስገደድ ስልጣን ግን የለውም። እዚህ ጋ ማነው ሕገ-መንግስቱን፣ ዓለምአቀፍ ሰብዓዊ መብቶችን እና ከመማርና ሃይማኖትን ከመተግበር ጋር የተደነገጉ ሕግጋትን እየጣሰ ያለው የሚለው ነጥብ ትልቅ ጥያቄ ያስነሳል። በተጨማሪም ትምህርት ማንነትን በግልፅ እንዲታይ እና መምህር የተማሪን ስሜት ማንበብ የሚችልበትን የፊት ለፊት ግንኙነት እንደሚፈልግ፣ ለዚህም ሲባል የኒቃብ አለባበስን የመተግባር መብት ሊገደብ እንደሚችል የቀረበው መከራከሪያ በዘመናዊው የትምህርት ዓለም ተቀባይነት ያለው አይደለም። መምህር የተማሪን ስሜት ማንበብ ግዴታ ከሆነ፣ በአሁኑ ወቅት በስፋት እየተሰጡ ያሉ የርቀት ትምህርቶች ስህተት ናቸው ሊባል ነውን? በዓለም ዙሪያ ያሉና በትምህርት ጥራት ከዩኒቨርሲቲያችን የሚልቁ የልህቀት ማዕከላት እንደ ኒቃብ ያሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶችን ሳይከለክሉ ስኬታማ መሆናቸው እየታወቀ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይህንን እንደ ምክንያት ማቅረቡ አሳማኝ አይሆንም። ፕሬዚዳንቱ "ተማሪ Civic እንዲሆን እንፈልጋለን" በማለት የሰጡት መደምደሚያም ቢሆን፣ ሲቪክ መሆን ማለት ሃይማኖትን ከመተግበርና ከመከተል ነፃ መሆን ማለት ነው የሚል እሳቤ ካለው ወዴት እያመራን እንደሆነ ጥያቄ ያስነሳል። ሲቪክ መሆን እና አማኝ መሆን እርስ በእርስ የሚደጋገፉ እንጂ የሚቃረኑ እሴቶች አይደሉም። ሰብዓዊ መብቶች ሊገደቡ የሚችሉት በፓርላማ በሚወጣ አዋጅ እንጂ ተቋማት በሚያወጡት መመሪያ ብቻ ሊሆን አይገባም። በዚህ ጉዳይ ፓርላማው አዋጅ ሳያወጣ ወይም ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ ሳያፀድቅ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተለይቶ መብቶችን የሚገድብ መመሪያ ያወጣው ለምንድን ነው? ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ም ባወጣውና በያዝነው ዓመት ባሻሻለው የተማሪዎች ዲሲፕሊን መመሪያ መሠረት፤ ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብን፣ የክርስትና እምነት ተከታዮች ደግሞ ነጠላን ለብሰው የዩኒቨርሲቲውን አገልግሎት እንዳያገኙ የሚከለክል አንቀጽ መኖሩን ልብ ይሏል። በመሆኑም ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ከትምህርታቸው የሚያዘናጋ አጀንዳ ከመስጠት ይልቅ፣ ዓለምአቀፍ ተሞክሮዎችን በመውሰድ የተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት በማክበር ለተሻለ የትምህርት ስርዓት ግብዓት እንዲሆኑ ማስቻሉ መልካም ነው። ©️ aaumsu https://t.me/EHEMSU

"AAU ኒቃብን በመከልከሉ ምክንያት ለ15 ቀናት ከካፌ የታገዱ ሙስሊም ተማሪዎች ነበሩ:: በFBE: Commerce: ያሬድ ካምፓሶች አትገቡም ተብለው ከበር የቆሙበት ጊዜም ነበር:: መማሪያ ክፍል ውስጥም የተለያዬ እንቅፋት የተፈጠረባቸው ተማሪዎች አሉ:: ይህ ሁሉ የሆነው ሕገ- መንግስታዊ መብቶችን በማፈን በወጣው መመሪያ ምክንያት ነው:: እስካሁን የደረሰባቸው መበደልም ቆሞ ለመብታቸው ዋስትና የሆነን መመሪያ በማውጣት ሊካሱ ይገባል::" - ተማሪ ሙሐመድአሚን ካሳው ETV ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ከተናገረው ሆኖም ግን ከተለቀቀው ፕሮግራም እንደተገነዘብነው ይህ እና መሠል የተማሪዎችን ጥያቄ የሚገልፁ መልዕክቶች ተቆርጠው ቀርተዋል:: ይህም በመሆኑ የጥያቄው ሙሉ መንፈስ ሊንፀባረቅ አልቻለም:: ለመሠል ፕሮግራሞች ሽፋን የሚሰጡ ሀገራዊ ሚዲያዎች ለተቋም ግንባታ ያላቸውን አስተዋፅዖ ታሳቢ አድርገው ተማሪዎች እየጠየቋቸው ያሉትን የመብት ጥያቄ ሀላፊነት በተሞላበት መልኩ እንዲያስተላልፉ እንጠይቃለን:: የዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የሰጡት ምላሽም በተማሪዎች ዘንድ ሰፊ ጥያቄን በማስነሳት ላይ ያለ ከመሆኑም ባሻገር ለመልሳቸው በራሱ ብዙ ጥያቄዎች አሉን:: ስለሆነም ETVም ሆነ ከእርሱ ውጪ ያሉ የመንግስት ሚዲያዎች: ለሙስሊሙ ማህበረሰብ የተቋቋሙ ሚዲያዎች እንዲሁም ስለ ሰብዓዊ መብት የሚጠይቁ አካላት ሁሉ ከፀደቀ ጀምሮ የሙስሊም ተማሪዎች መብት እንዲጣስ እያደረገ ስላለው የAAU መመሪያ እንዲጠይቁ እና ፍትሐዊ የሚዲያ ሽፋን እንዲሰጡ እንጠይቃለን:: @aaumsu

የAAU ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ኒቃብን እና ሌሎች የተማሪዎች ሕገ-መንግስታዊ መብቶችን አስመልክቶ ከተማሪ ሙሐመድአሚን ለቀረበላቸው ጥያቄዎች የሰጡት መልስ ነው:- "መምህር የተማሪን ፊት ማየት እና Emotion ማንበብ አለበት:: ተማሪዎች Civic መሆን አለባቸው:: አለባበሶች እና የግል ሁኔታዎች ሊገደቡ ይችላሉ:: ተማሪዎቻችን ተማሪ እንዲመስሉ እንፈልጋለን:: ተማሪን Civic ማድረግ ሕገ-መንግስታዊ ሁኔታዎችን አይጋፋም:: በዚህ ረገድ ሕገ-መንግስታዊ መብቶችን መገደብ እንችላለን::" ሙሉውን አዳምጡት ተማሪ ተማሪ መሠለ የሚባለው መች ነው? ተማሪ Civic ሆነ የሚባለውስ መች ነው? ሕገ-መንግስታዊ መብቶችን ከፓርላማ ውጪ ያሉ ተቋማት መገደብ የጀመሩት ከመች ወዲህ ነው? We have a question ! @MohammadamminKassaw

ኢዜማ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የራሱን ፖሊሲ ሲያስፈጽም መቆየቱን ገለጸ! - ሀሩን ሚዲያ፥ ታህሳስ 8/2018 ዓ.ል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ ያለማንም ጣልቃ ገብነት የራሱን የፓርቲ ፖሊሲ ሲያስፈጽም መቆየቱን በይፋ አስታውቋል። ፓርቲው ማክሰኞ ታኅሣሥ 7 ቀን 2018 ዓ.ል ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ፤ የፓርቲው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ሚኒስትር ሆነው በተሾሙባቸው ባለፉት አራት ዓመታት የኢዜማን የትምህርት ፖሊሲ ተግባራዊ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጿል። የፓርቲው ብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ኢዮብ መሣፍንት እንደተናገሩት፤ ሚኒስትሩ "ያመኑበትን ሲሰሩ ነው የቆዩት" ያሉ ሲሆን፣ ይህም ለቀጣዩ ምርጫ ቅስቀሳ የሚጠቀሙበት ትልቅ ስኬታቸው መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የኢዜማ ይፋዊ መግለጫ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ስጋትና ጥያቄን ቀስቅሷል። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ሚኒስቴሩን በመሩባቸው የእነዚህ ዓመታት ጊዜያት በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዲሁም ኒቃብ እንዳይለብሱ ተከልክለዋል። ከዚህም በተጨማሪ ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸው ላይ እያሉ ሰላት እንዳይሰግዱ/የሰላት ስነ-ስርዓት እንዳያከናውኑ/ በመከልከላቸው ከትምህርት ገበታቸው የተሰናበቱና ለእንግልት የተዳረጉ በርካታ ናቸው። በአዲስ አበባ እና በሌሎች ክልሎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የእምነቱ ተከታዮች "ለእምነታችን ነጻነት ይከበር" በማለታቸው የአካልና የሞራል ጥቃት ደርሶባቸዋል። ፓርቲው "ያለማንም ጣልቃ ገብነት የራሳችንን ፖሊሲ አስፈጽመናል" ማለቱ፤ ባለፉት ዓመታት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ሲፈጸም የነበረው አድልዎ እና የሀይማኖት ነጻነት መገፈፍ የፓርቲው እቅድ አካል ነበርን? የሚል መሠረታዊ ጥያቄ አስነስቷል። ኢዜማ በምርጫ 2018 እንደሚሳተፍና እነዚህን ስራዎቹን ለቅስቀሳ እንደሚጠቀምባቸው ቢገልጽም፤ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ግን ይህ "የፓርቲ ፖሊሲ" የተባለው አካሄድ የእምነት ነጻነትን የሚጋፋና ዜጎችን ከትምህርት ገበታ የሚያፈናቅል መሆኑን በተደጋጋሚ ሲያመለክት ቆይቷል። ባለፉት ዓመታት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የደረሰው የሂጃብ እና የሰላት እገዳ ከፓርቲው እቅድ ጋር ስለመያያዙ የገለጸው ነገር የለም! © ሀሩን ሚዲያ