የኛ ትረካ ፤ ግጥም እና የ መፅሐፍት PDF
رفتن به کانال در Telegram
የተለያያዩ አጫጭር እና ረጅም ትረካዎች እና Pdf መፃሕፍት እዚህ ያገኛሉ አዋቂ ለመሆን መጀመሪያ አዋቂ እንዳልሆኑ ይገንዘቡ **አላዋቂ መሆኔን በማወቄ ብልህ ነኝ። ** -Socrates
نمایش بیشتر2 183
مشترکین
-424 ساعت
+67 روز
+2830 روز
آرشیو پست ها
📚ርዕስ:- ድብቅ አእምሮን መግለጥ (The Power of your Subconscious Mind)
📝ደራሲ:- Dr. JOSEPH MURPHY (Ph .D.D.D..)
👤ትርጉም:- ሱራፌል ግርማ
📜ዘውግ:- ምክረ አእምሮ
📆ዓ.ም:-
📑የገፅ ብዛት :- 200
💰ልጥፋ ዋጋ:- 150ብር
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
ርዕስ:- እንደሰው በምድር እንደሰው በባህር
ክፍል: #ሁለት
ደራሲ:- አሌክሳንድር ቤላይቭ
ትርጉም:- በካፋ ሃ/እየሱስ
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
ርዕስ:- እንደሰው በምድር እንደሰው በባህር
ክፍል: #አንድ
ደራሲ:- አሌክሳንድር ቤላይቭ
ትርጉም:- በካፋ ሃ/እየሱስ
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
ራሴን ልመልከት ምረትን እያሰብኩ
ይሁዳ ሸጦታል ፤
ጴጥሮስም ክዶታል።
ትንሳኤን ጠብቀው ይህን ይነግሩኛል
ካህናት በሙሉ፤
በምክር በግ አይሆንም የተኩላ አመሉ ።
እና ይገርመኛል ሲነገረኝ እኔ ፤
ሰውፊት ስቆም ስታይ ንፁ ፃድቅ መሳይ ግን ነበርኩ ወመኔ።
እና እነሱ ላይ እንጠለጠላለሁ አምላኩን የካደው ፤
እያልኩ ጠዋት ማታ አምላኩን የሸጠው ።
ዳሩ ረስቼው ያ ክፉ አመሌን ፤
ማን ይንገረኝ እስኪ የልብ ጉድፌን።
ባምሳያ የፈጠርከው የሰው ልጅ በሙሉ ፣
ክርስቶስን መሳይ አምሳያው ነውና ፣
ገንዘብ አስበልጬ ሰውን የሸጥኩ እኔ ዩዳን ተክቻለሁ ፤
ሰውን የካድኩ እኔ በተዘዋዋሪ አንተን ክጄሀለሁ ፤ ጴጥሮስን ሆኛለሁ ።
ታዲያ ለምን እዛ እነሱን አስጠራኝ ካዱት ጌታን ብዬ
ሸጡ አንተን ብዬ ፤
ሰቀሉት አይሁዶች ገረፉትም ብዬ ።
ሀጢያት እየሰራው ሰባ አንደኛውን እሾህ የምወጋ ፤
ፍፁም ያልተረዳው የአምላክነትህን ከቶ ያንተን ዋጋ ።
በሰው ላይ ለመፍረድ የምሮጥ እሩጫ ፤
ኮናኝ ባሎንኩበት ሰውን ለመኮነን የምዘል ቁንጫ ።
እኔ ሀጣኗ ነኝ ዳግማዊ ይሁዳ ፤
ጴጥሮስንን አልልም ባፍ አሞግሼ በልቤ ምከዳ ።
እኔ ነኝ ሚገባኝ
ህይ ውርጅብኝ ሁሉ በይሁዳ ቦታ ፤
ከቶ ያላመንኩህ ተሳስቼ ላፍታ ።
ክርስቶስ ታውቃለ ህ ፤
ልብና ኩላሊት ትመረምራለህ ! ።
ከነሱ ተግባር የኔ ሚዛን ደፍቷል ፤
የሀጢያቴ ብዛት እጅጉኑ ከብዷል ።
እውነት ነው አምላኬ እፊት እንዳይኖረኝ አድርጎኛል ሞገስ ፤
ለሰው አይምሰል እንጂ
ነጠላ ለብሼ ቤት ስመላለስ ።
የዘወትር ሀጢያቴ ሶስቴ የካደህን የጴጥሮስን በልጧል ፤
አንተን የሸጥኩበት ጊዜም ይሁን ገንዘብ ከይሁዳ አልፏል ።
እኔ ነኝ ሚገባኝ በይሁዳ ቦታ ዘወትር መኮነን፤
እኔ ነኝ ሚገባኝ ውርጅብኝ መገፋት መወገር በድንጋይ ።
እኔ ያቺ አጣኗ ክፉ ዋ ባሪያህ ነኝ ፤
በተገረፍ ከው ልክ መገረፍ ሚገባኝ ፤
በቆሰልከው መጠን በተንከራተትከው፤
ለኔ ለዛች ሀጣን በመሰቀል የዋልከው ።
ስቃይ ህ ህመምህ ሞት ለኔ ነበር ፤
አንተ ይቅርባይ ግን የምህረት አምላክ መቼ ትጠፋለህ ዘወትር ከኔ በር ።
በበደልኩ መጠን መቼ አንተ እራከኝ ፤
ባስከፋውክ መጠን መቼ አሳዘንከኝ ፤
እንደበደሌ ኳ መቼ ተከፈለኝ።
✍በኅብስት መንገሻ/ሮሀዊት
@mitu2
@mitu2
@mitu2
@mitu2
✨ አባቱ የጠየቀው ጥያቄና ብልሁ ሰሎሞን የመለሰው መልስ
#ጥያቄ- የማስተዋል ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከአንጎል ውስጥ ነው።
#ጥያቄ- የእውነት ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከዓይን ነው።
#ጥያቄ- የሐሰት ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከጆሮ ነው።
#ጥያቄ- የደኅንነት ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከፊት ነው።
#ጥያቄ- የመውደድ ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከነፍስ ነው። (ኢሳ 42፣1)
#ጥያቄ- የትንፋሽ መውጫ ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከአፍንጫ ነው።
#ጥያቄ- የጥበብ ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከአንደበት ነው
#ጥያቄ- የማሰብና የመተከዝ ቦታቸው የት ነው?
#መልስ- ከደረት(ከልብ) ነው።
#ጥያቄ- የመንፈስ ቦታው የት ላይ ነው?
ከልብ ነው።
#ጥያቄ- ምክርን የማግኘት ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ነገርን ከልብ ከመረዳት ላይ ነው።
#ጥያቄ- የሳቅ(የደስታ) ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከልብ ውስጥ ነው።
#ጥያቄ- የትዕግስትና የቍጣ ቦታቸው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከልብ ነው።
#ጥያቄ- የቅናት የምቀኝነት ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከዓይንና ከሕሊና ነው። (ማቴ 20፣15)
#ጥያቄ- የነፍስ ጠላቷ ማን ነው?
#መልስ- ሥጋ ነው። (ገላ 5፣16)
#ጥያቄ-የመሰብሰብ (የመበተን) ቦታው የት ላይ ነው?
#መልስ- ከእጅ ነው።
#ጥያቄ- የሰውነት አቋማ የት ላይ ነው?
#መልስ- ከራስ ነው።
✨ አንገረ ፈላስፋ ✨
● የማበረታታት ቦታው የት ላይ ነው?
◉"ሼር" እና "ላይክ" ከማድረግ ነው።
48ቱ የሀይል ህጎች
ሕግ 2
በጓደኞችህ ላይ ብዙ እምነት አታሳድር ! ጠላትህን እንዴት እንደምትጠቀምበትም እወቅ!
ብያኔ
ጓደኞችህን ስጋ! ተጠንቀቅም! በፍጥነት ሊከዱህ ይችላሉና፣ በቀላሉ ለቅናት ስለሚጋለጡ፡፡ ሞልቃቃ፣ ባለጌና አምባገነንም ይሆናሉና፡፡ የቀድሞ ጠላትህን ቅጠረው ከጓደኞችህ የበለጠ ታማኝ ይሆናል፤ምክንያቱም ማረጋጋጥ አለበትና፡፡በእርግጥ ከጠላቶችህ ይበልጥ አጥብቀህ መፍራት ያለብህ ጓደኞችህን ነው፡፡ ጠላት ከሌለህም ጠላት የምታፈራበትን ዘዴ ፈልግ፡፡
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
#የአይኔ_አበባ
እውነተኛ ታሪክ
#ክፍል 17
እኔ ልቤ እየደለቀች ብዙም ትኩረት ሳልሰጠው ጥግ ይዤ አቆምኩና እንደ ሙሽራ እየተጀነንኩ እቅፍ አበባየን ይዤ ወደ ጊቢው በር ስጠጋ አንድ ነጠላቸውን በወጉ ያላጣፋ ሴትዮ ገበብ ብሎ የተከፈተውን የጊቢ በር አልፈው ለብቻቸው እያጉረመረሙ ሲወጡ ተመለከትኩ።
ጊቢው ውስጥ ያሉት ሴቶች ወጥ ሲሰሩ ይታዩኛል። አዕምሮየ ውስጥ ብዙ ሀሳቦች ተመላለሱ፡፡
ጊቢው ውስጥ የተያያዙ ሁለት ክፍል ቤት አለ። አንዱን ክፍል ሌላ ሰው የሚኖርበት ክፍል ሆኖ የነሱ ድግስ ይሆን? ስል አሰብኩ። አይ ምናልባት ያይኔ ልጅ ኖሯት ልደት ክርስትና ምናምን ይሆን?
የዘፈን ድምፅ ባይሰማኝም ምናልባት የአይኔ ሰርግ ደግሳ ሰርፕራይዝ ልታደርገኝ ይሆን? ሌላ ሰው ልታገባ ቢሆንና ለዛ ቢሆንስ እምቢ ያለችኝ? ሌላ ቃልኪዳን ይኖራት ይሆን? እንደገና ደግሞ ልቤ ክፉ ነገር ጠረጠረ፤ ምንም የአልቃሽ ድምፅ ባይሰማም ለቅሶም ሊሆን ይችላል።
አማተብኩኝ ሴትዮዋ አጠገቤ ደርሰው ሊያልፉ ሲሉ ልጠይቃቸው ወስኜ ' እእ..' ብየ ባሰብኩት ሀሳብ የምሰማውን መልስ ለመሸሽ ስል ዝምታን መረጥኩ።
ሴትየዋ ድምፅ የሰሙ መስሏቸው ገልመጥ አርገው ግርምት በሚመስል አይን ተመልክተውኝ በዝምታ አለፉኝ። ፀጥታው አስፈራኝ። ተመልሼ ዲያሬዋን በማንበብ እዉነታውን ለማወቅ መልሱን ፍለጋ ወደ መኪናየ መመለስ ጀመርኩ። ግን እግሮቼ በፈጠርኩት ክፉ ሀሳብ የተነሳ ብርክ ይዟቸው አልራመድ አሉኝ። ከእውነታው ከመሸሽ ይልቅ ለመጋፈጋፈጥ ወስኜ አበባየን በቀቢፀ ተስፋ ተሸክሜ መጀነኔ ቀርቶ እንደ ሰካራም እየተወላገድኩ የጊቢውን በር ዘልቄ ገባሁ። የልቤ ትርታ እየፈጠነ ጭንቀቴን አባብሶታል።
የሁሉም ሰው አይን ወደ እኔ እያፈጠጠ ነበር። ዳሱ ጋ ስደርስ ለቅሶ መሆኑን ተገነዘብኩኝ። ሁሉም አይኖች ወደኔ የተቀሰሩበት ምክንያት ገባኝ፤ እንዲ ለብሼ እንደዚህ አይነት ቦታ መገኝቴ ነውርእንደሆነ ተሰማኝና የአይኔ አበባን አጊኝቼ ይዣት ለመውጣት ተጣደፍኩኝ። የአይኔን ያየኋት መሰለኝ።
ማንንም ሰላም ሳልል ተጠግቼ ለማጣራት ወደሷ ተራመድኩ ራሷ ናት። 'የአይኔ አበባ' ብየ በለሆሳስ አይሉት ጩኸት ድምፅ ስሟን ተጣራሁ።
የዳሱ ቋሚ ላይ የተሰቀለው ፎቶ የያይኔ አበባ ነበር። ጭ..ው የሚል ስሜት ብቻ ይሰማኛል። ከዛ ለምን ያህል ጊዜ እንደሆነ ሳላውቅ መሬት ላይ ወድቄ ሰዎች ውሀ በደረቴና በግንባሬ እያደረጉ እንድነቃ ሲጣጣሩ አየሁ።
የት እንደሆንኩኝ ማስታወስ አቃተኝ ሁሉም ህልም መሰለኝ። ልብሴ በጭቃ ተለውሶ ወደ ጥቁርነት ተቀይሯል።ተነስቼ ስቆም ብትንትኑ የወጣው ይዤው የመጣሁት አበባ ያይኔን መሰለኝ።ሁለቱም ከአፈር ተደባቀዋል።አጠገቤ ከበውኝ ከነበሩት ሴቶች መሀል አንዳንዶቹ ማልቀስ ጀመሩ።ፊት ለፊቴ የያይኔ ፎቶ ግራፍ በፈገግታ ግስጥ ብሎ ከእውነታው አለም ደባለቀኝ።እሪ ብየ እየጮህኩ አለቀስኩኝ። ስቅስቅ ብየ አንጀቴ እስኪላወስ አነባሁኝ።
ፈገግታዋ አይኔን እየጋረደ ቁመናና ለዛዋ ሳቅና ጨዋታዋ በአይን በአይኔ እየሔደ እረፍት አጥቼ ተንሰቀሠኩ። ስትቃለደኝ፣
ስትጎነትለኝ፣ ስታጎርሰኝ፣ ቡና ስታፈላልኝ ትታየኝ ነበር። ውበቷ እንደ ጤዛ ረገፈ፤ ያ ሁሉ መከራዋ በሞቷ አለፈ። ሀዘኔን መቋቋም አቃተኝ። ዙሪያየን አማተርኩ ጥቂት ሰው ብቻ ነው ያለው፡፡ እንደ ቅርብ ሰው እግዜር ያጥናሽ የሚባሉትን አንድ ሴትዮ ብቻ ናቸው፡፡ 'ማናቸው?' ስል እሳቸው ላይ አተኮርኩበቸው፤ እሳቸውም ከተዘረጋው ፍራሽ ላይ ተነስተው አጠገቤ በመምጣት ከጎኔ ተቀመጡና 'አይዞህ ልጄ በርታ በል አሉኝ' የእናትነት ለዛ ባለው ቃና። ማን እንደሆኑ መገመት አልቸገረኝም። 'እትየ አስቴር ማለት እርስዎ ኖት?' አልኳቸው ያላቆመ እንባየን ከፊቴ ላይ በሶፍት እያባበስኩ። 'አዎ ልጄ እንዴት አወቅከኝ?' አሉኝ "ስለርስዎ ያይኔ አጫውታኝ ነበር" አልኳቸው፡፡ እንባቸው ከአይናቸው እርግፍ እያለ ወረደ እንዴት ያለች ልጅ የሆዷን በሆዷ እንደያዘች ማንም ሳይረዳት አለሁልሽ ሳይላት ስትሰቃይ ኖራ በመጨረሻ ወደማይቀርበት አለም ኮበለለች።' አሉኝ እዝን ብለዉ። ዝም ብየ ቆየሁና ሳግ እየተናነቀኝ "ለመሆኑ ምን ሆና ነው?" አልኳቸው፡፡ 'አይ ልጄ ብዙ የእንቅልፍ መድሀኒት ቅማ ነው አሉ ከትላንት ወዲያ አንድ ሰአት አካባቢ ነፍሷ ያለፈችው፡፡ '
አሉኝ 'ከትላንት ወዲያ?' ከትላንት ወዲያ የሷ ነፍስ በጣር ላይስትሆን ይሆን እኔንም ነፍስ ተጨንቃ ያለምክንያት ከንቅልፌ ቀስቅሶ ነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ እያሰቃየ ሲያስጨንቀኝ የነበረው? ስል አዛመድኩት። ምናልባት ሁለታችንም እስከዛሬ አፍቅረን ባለማወቃችን ልባችን እነደመንታልብ ተጣምሮ ይሆን ጣሯ ለኔም የተረፈኝ? እናም በጭንቀት ፋታ የነሳኝ ለዛ ይሆን? አላውቅም? ሊሆንም ላይሆንም ይችላል ታዲያ ፈጣሪ ለምን ሊለየን ወደደ? ውስጤ መልስ የሌላቸው ጥያቄዎች ተመላለሱብኝ።
"ማነው ስምህ?" አሉኝ ወ/ሮ አስቴር ረጋ ባለ አነጋገር። "ናቲ" ስል መለስኩ "ላንተ ነው ማለት ነው?" አሉኝና ካጠገቤ ተነስተው ተቀምጠውበት ወደነበረው ፍራሻቸው ሔደው ፍራሹን ገለጥ አድርገው የሆነ ፖስታ ይዘውልኝ ተመለሱና
" 'ካላረፈድክ እኔ በዝምታ አንተ ደግሞ አያለቀስክ ትሰናበተኛለህ' በሉልኝ አደራ ቃሉን ሳያዛንፋ ንገሩት' ብላኝ ማታውኑ ይህን ወረቀት ሰታኝ ጠዋት እንዲ ሆነችና አረፈችው፤ እኔን ልጄን! " አሉና ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፡፡ እኔም መልስ ሳልሰጣቸው በዝምታ እንባየን አፈሰስኩኝ። "መጀመሪያ የትልትሔጂ አስበሽ ነው? ብየ ጠየቄአት ነበር። መልሱን ያልነገረችኝ ለዚ ኖሯል ለካ! ተጣልታችሁ ነበር?" አሉኝ "አይ አልተጣላንም ይመስለኝ ነበር እኔ አንጃ አስቀይሜአት ይሆናል።" አልኳቸው ሳላውቅ ውስጤን ጥፋተኝነት እየተሰማኝና እንዲህ ያደረገችበት ምክንያት አጠራጥሮኝ። "መጨረሻ ላይ ስትሄድ 'በጣም እንደምወደውም ንገሩልኝ' ብላኝ ስለነበር ነው ይህን የጠየኩህ ምናልባት ፍቅረኛ ይዛ ተኳርፋችሁ ይሆናል ብየ አስቤ ነው" "እኔ እንጃ?" አልኳቸውና መልሱን ፍለጋ " ናቲ መቼም ከዲያሬው ጀርባ የፃፍኩትን ነገር ካነበብክእንደማታዝንብኝ ተስፋ አደርጋለሁ።...(ምክንያቷን ማንበብ ነበረብኝ አልኩና በዝምታ ማንበቤን ቀጠልኩ) ...ሳታረፍድ ደርሰክበቀብሬ ላይ ተገኝተህ ከሆነ ከምታስበው በላይ ነፍሴ የምትደሰት ይመስለኛል። ሳይሆን ቀርቶ እንደተለያየን ከቀረንም ወይም አንተ ሳትደርስ ስርአተ ቀብሬ ተፈፅሞ ከቆየህ ምን ያህል እንደማፈቅርህና ባንተ ምክንያት የብዙ ሰዎችን ህይወት ከጥፋት እንደታደክ አስበህ ተፅናና። ታውቃለህ አንተን በማግኘቴ መንገዴ ተስተካከለ በበቀል ተሞልቶ መስራት አቁሞ የነበረ ህሊናየ እንደ አዲስ ነቃ። በርግጥ የበቀል ጥሜን ባረካሁ ቁጥር እንዳሰብኩት ሰላም አላገኝም፤ እንቅልፌን ሳይቀር የምተኛው በእንቅል መድሀኒት ነበር። አሁን አሁን ግን በሰላም የማልተኛው ባንተ ምክንያት ብቻ ነው፤ ዲያሬው ላይ እንደፃፍኩልህ ፅንሴ ጨንግፎ ሀኪም ቤት ስገባ የኤች አይ ቪ ቫይረስ እንዳለብኝ ሲያረዱኝ በመደንገጥ ፋንታ
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
ጌቱ(አስተናጋጁ) ስለሀገሩ ሰዎች ስለአንዳንድ ባህላቸው፣ አስር አመት ሳይሞላቸው በሰርግ ስለሚዳሩት ወንድና ሴት ህፃናት ፣ ስለጀግንነታቸወዉ፣ ስለ ደግነታቸው ስለሚተኙበት 'ጀንዲ' ስለሚባል ከበሬ ቆዳ ስለሚሰራ የለፋ ቆዳ ሁሉ ያጫዉተኝ ነበር። ጎታ ስለሚባል ከጭቃ ስለሚሰራ የእህል ማከማቻ ጎተራ ሳይቀር ይተርክልኛል።
እኔ ግን ለይስሙላ አንገቴን ከፍ ዝቅ እያደረኩ የሰማሁት ለመምሰል እታገላለሁ እንጂ በፍፁም ቀልቤ ከሱ ጋር አልነበረም። የሆነ ሰዓት እንዳውም በጭራሽ አላስችል ስላለኝ በጥቁሩ ፌስታል ውስጥ ያለውን ነገር ለማየት ስዳብስ የልቤ አልደርስ ብሎ ከፍቼ ተመለከትኩት፤ ግን የባሰ ልቤ ተንጠለጠለ እንጂ አልረካሁም። ምግቡ ቀርቦ እንደነገሩ ቀማምሼ መታገስ ስላቃተኝ ይቅርታ ጠይቄው ሌላ ቀን በሰፊው እንደማገኝው ቃል ገብቼ አመሰገንኩትና ሒሳብ ከፍየ 'አንተ ቀስ ብለህ ውጣ እኔ ትንሽ ስለቸኮልኩ ነው' ብየ እተጣደፍኩ በተቀመጠበት ትቼው ወጣሁ፡፡ ልክ ባልሆንም ከዚ በላይ መቻል አቅቶኝ ነበር። ያይኔ አበባ ይህን እቃ እንዳገኝው ከፈለገችው ቀን ሁለት ያህል ቀናት አርፍጃለሁ። መኪናየ ውስጥ እንደገባሁ ወዴትም መንዳት ሳልጀምር ቅድም ያየሁትን ብልጭልጭ አራት መአዘን ቅርፅ ያለዉን እቃ ልቤ እንደነጋሪት እየደለቀ የተጠቀለለበትን የስጦታ ወረቀት ፈታሁት። መፅሐፍ መሆኑን ገና ስፈታው ነበር ያወኩት። ግን ተራ መፅሐፍ ሳይሆን የግል ታሪኳን የከተበችበት ዲያሬዋ መሆኑን ከላይ ባለችው ከነመክፈቻ ቁልፏ የተንጠለጠለችው ትንሽዬ ጋኗን ሳይ ነበርየተረዳሁት። ቁልፉን ከፍቼ የመጀመሪያ ገጹን ስገልጠው የራሴን
ፎቶ ተመለከትኩት። መቼ እንደወሰደቸው አስታወስኩ ምንያህል ለምናኝ እንደነበረ ትዝ አለኝ። ከጀርባው በኩል ስገለብጠው እንዲህ ይላል " ህይወቴን በአዲስ ጎዳና የመራ በአዲስ ቅኝት የቃኘኝና ያነገስኩት የልቤ ጀግና ይሄ ጉብል ነው!" የሚል ፅሁፍ ተከትቦበታል። ድብልቅልቅ ያለስሜት ተሰማኝ። ኩራትና ፍርሀት ውስጤን አራደው፡፡ ከዛም የዲያሬዋን የመጀመሪያ ገፅ ማንበብ ቀጠልኩ። "ናቲ በብዛት የነገርኩህና ያው ስለኔ የምታውቀው ታሪክ ነው፤ ግን ድፍረት አጥቼ ያልነገርኩህን ታሪክ እንደ ደብዳቤ ከጀርባ በኩል ፅፌልሀለሁ። በመጀመሪያ እሱን አንብበው" የሚል መግቢያ የሚመስል ሀተታ ተፅፎበታል። እኔም የመጨረሻ ገፁን ገለጥኩት። ሁለት ገፅ ነው፡፡ እንደ አረቦች ፅሁፍ ከቀኝ ወደ ግራ እየገለጥኩ ለማንበብ ጀመርኩት። "እባክህ ናቲ በምንም ነገር እንዳታዝንብኝ። በመጀመሪያ ከምንም በፊት ስላንተ ያለኝን ጥልቅ ስሜት ልነግርህ እፈልጋለሁ። አንተን በመጀመሪያ ያዋራውህ ቀን ልቤ በቀናነት ተመለከተህ። ስህተት እየሰራሁ እያለ በድንገት ልቤን ዘግተህ ያዝክብኝ። ስቀርብህ እንደማንኛውም ወንድ ፍላጎትህን ለማሳካትና ጭኔ ስር ለመንበርከክ አልንገበገብ በማለትህ ሁሌም በግርምት እደመምብህ ነበር። ተገናኝተን ባወራን ቁጥር ሁሌም አዲስ ነገር ታሳየኛለህ። ግን ከማንም የተለየህ አለመሆንህን ለልቤ በተደደጋጋሚ ብነግረውም ስላንተ የማስባቸው መልካም ነገሮች እየጎሉ ካንጀቴ ጠብ አልልሽ አለኝ። ይህ ነገር ፍቅር የሚባለው ይሆን ስል እንደ ጦር ፈራሁት፤ አንተን ሳላይህ ማደር እየከበደኝ ስለነበር በፈተና ጥየህ በገዛ ፍቃዴ ልጠላህ ፈለኩ። ይቅርታ አድርግልኝ ካንተ ለመራቅ በሞከርኩኝ ቁጥር ወደአንተ የሚስብ ነገሬን መከልከል አልቻልኩም። ስለዚህ እንደማንኛውም ወንዶች መሆንህን ለራሴ ለማሳየት በአንድ የቀልድ ቀጠሮህ እኔ የእውነት መጥቼ ልፈትንህ ታገልኩኝ። ግን በገዛ ፈተናየ ጣልከኝ። የባሰ ተሸነፍኩኝ። ያልነገርኩህን ነገሮች ሁሉ ልነግርህ ተገደድኩኝ። እኔ እስከነገርኩህ ድረስ ያለው ታሪኬ እኔ ምስኪን ተበዳይየሆንኩበትና ልጅነቴን የተነጠኩበት የቅዱስነት እድሜየ ነበረ። ብዙውን ነገር ማንበብ ካልሰለቸህ በቀር ዲያሬየ ላይ ታነበዋለህ። ዲያሬ መፃፍ የጀመርኩት እናቴ በህይወት ከተለየችኝ በኃላ ነው ብቸኝነት ሲሰማኝ ልክ ከእናቴ ጋር እንደማወራ ሁሉ አንድ በአንድ የደረሰብኝንና የሆነውን ነገር ሁሉ ቀን በቀን የምሞነጫጭረው፡፡ እና የቀረውን ታሪኬን ስቀጥልልህ አንድ ጊዜ ከሟች እንጀራ አባቴ አርግዤ እንደ ጨነገፈብኝ ነግሬህ ነበር። እና ሀኪም ቤት ስሔድ ልጅ ፀንሼ እንደነበረ ብቻ ሳይሆን ." እዚጋ አቆምኩና ገፁን ገለጥ አረደረኩት። "የቤቴ አድራሻ" የሚል የተፃፈበት ደማቅ ፅሁፍ ላይ አይኔ አረፈ። ጊዜ ሳላባክን መኪናየን አስነስቼ ቁልቁል በአርጌና ሰፈር እየከነፍኩ ወጣሁና ወደ መናህሪያው አካባቢ በመሔድ እሷን ሊያስደንቃት የሚችል አለባበስ ለመልበስ ነጭለሙሽራ የሚሆን በልኬ የተሰፋ የሚመስል ሱፍ ገዝቼ ለበስኩና እቅፍ አበባ ሸምቼ ቤቷ መሔድ እንደገና በመጣሁበት አቅጣጫ እየተመለስኩኝ የሰጠችኝን ምልክት በአይኖቼ ማሰስ ጀመርኩ፡፡ ከብዙ ድካም በኃላ ቤቷን አገኝሁት፡፡ ጊቢያቸው ውስጥ አነስተኛ ዳስ ተጥሎ ጥቂት ሰዎች ሸር ጉድ ይላሉ አንድ ህፃን ልጅ አገኝሁና ' አቡሽየ የነ ያያኔ አበባ ቤት ይሄ ነው?' ስል ለማረጋገጥ ጠየኩት። ' አዎ! ' አለኝ ልጁ ለወሬ እየጓጓ። እኔ ልቤ እየደለቀች ብዙም ትኩረት ሳልሰጠው ጥግ ይዤ አቆምኩና እንደ ሙሽራ እየተጀነንኩ እቅፍ አበባየን ይዤ ወደ ጊቢው በር ስጠጋ አንድ ነጠላቸውን
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
አይኖቼ ጎልጉየ ቀዩን አስተናጋጅ ፍለጋ ተቅበዘበዙ፤ ቁጭ ብየ በርጋታ መጠየቅ ስላቃተኝ በቀጥታ ወደ እንግዳ ተቀበዯ ሴት እየተንደረደርኩ ሔድኩኝ።" አባክህን ምን ልርዳህ አልጋ ፈልገህ ነው?" ስትል በሰለጠነ ትህትና ጠየቀችኝ። "አይደለም ቀዩን አስተናጋጅ ፈልጌ ነው" አልኳት ሳላቅማማ። "ብዙ ቀይአስተናጋጆች አሉን የትኛው ይሆን ስሙን ካወከው ብትነግረኝ?" "አይ ስሙን እንኳን አላውቀውም ቀይ፣ ረዘም ያለና ቀጠን ያለ እድሜው ከ30-35 የሚሆነው ይመስለኛል ፈገግ ሲል ጥርሱ ዘርዘር ያለ ነው ጉንጩ ላይ ተለቅ ያለ ማርያም የሳመችው ይሁን ንቅሳት ጥቁር ነገር አለበት።" አገላለፄን አፏን ከፍታ በዝምታ ስታደምጠኝ ቆየችና " አወኩት ይሄ ነው አይደል? " ብላ የሆነ ጉርድ ፎቶ አሳየችኝ "አዎ! አዎ ራሱ ነው!" አልኳት ስንት አመት ጠፍቶ የከረመ ወዳጄን አንዳገኝሁት ሁሉ በደስታ እየተፍነከነኩ። " እቃ ጠፍቶብህ ነው? ወይስ መልስ ተሳስቶብህ ነዉ?" "አይበሁለቱም አይደለም ለሌላ ጉዳይ ነው፤ እባክሽን እህት ዛሬ ተረኛ አይደለም እንዴ?" ስል ጠየኳት በአይኖቼ ስፈልገው ስላጣሁት። "አሁን ዘጠኝ ሰዓት ላይ ነው የወጣው ከትላንት ወዲያ ነው የገባው መውጣት የነበረበት ትላንት ነበረ የሌላ ሰው ሰአት ሸፍኖ እየሰራ ነው ያደረው ትንሽ ቀደም ብትል ታገኝው ነበር።ለትንሽ! " አለችኝ "እባክሽ ስልኩን ልትተባበሪኝ ትችያለሽ?" " ውይ ይቅርታ ይህን የቤታችን ህግ አይፈቅድም" "ኧረ እባክሽ ልለምንሽ ለመጥፎ ነገር አይደለም እሱጋ እቃ ስለነበረኝ ነው እባክሽ ተለመኚኝ!" እግሯ ላይ መውደቅ የቀረው ልመና ድምፄን አስተዛዝኜ ለመንኳት። " እባክህን አንዴ አረፍ ብለህ ጠብቀኝ እሺ ስልኩ ስለሌለኝ ከቢሮ ልፈልግልህ።" "አመሰግናለሁ እሺ እዛጋ አረፍ ብየ እጠብቅሻለሁ የኔ ቆንጆ" አልኳት። ቆንጆ በመባሏ ፊቷ ወገግ ብሎ በርቶ
እየተውረገረገች ባለሀምሳ ሳንቲም ፋርኖ ዳቦ የማታክል መቀመጫዋን ለማወዛወዝ ራሷን እያሰቃየች ወደ ቢሮው በርስታመራ እኔም እየታዘብኳት ወደ ወንበሩ ሔጄ ቁጭ ብየ ጠበኳት። እስካሁን ምንም እንዳልበላሁ ያወኩት አስተናጋጁ
እጆቹን አጣምሮ ' ምን ልታዘዝ? ' ሲለኝ ነበር። ቢሆንም ጠዋት ሲያስመልሰኝ የምግብ ፍላጎቴን አብሬ የተፋሁት ይመስል ምንም መብላት አላሠኘኝም ነበር። ባለ 1 ሊትር ዉሀ ካዘዝኩት በኃላ እንግዳ ተቀባዯና አስተናጋጁ ከተለያየ አቅጣጫ ባንድ ጊዜ ደረሱ። ስልክ ቁጥሩን ሰትሰጠኝ እኔም ዳጎስያለ ጉርሻ አስጨበጥኳትና አስተናጋጁንም መልሱን ያዘው ብየ እየተደሰትኩና ስልኩን እየሞከርኩኝ ሆቴሉን ለቅቄ ወጣሁ። ስልኩ ጠራ። ልክስልኩ ሲነሳ ያይኔአበባ ፊት ለፊቴ ከች ትል ይመስል እስከሚያነሳው ቸኮልኩኝ። "ሀሎ" አለኝ " ሰላም ወንድሜ እንዴት ዋልክ? ናቲ እባላለሁ፤ እባክህን አንተጋ የተቀመጠ መልዕክት ነበረኝ የት ላገኝህ እችላለሁ? የት ልምጣ?" ስል ጠየኩት " እንዴት ዋልክ? የቆንጅየዋ ፍቅረኛ ነህ? አዎ ልክ ሸፍት ተቀይሬ ልወጣ ስል መጥታ ሲመጣ ይሄንን ስጠው እባክህ በጣም ጥብቅ ሚስጥርነው ለሌላ ሰው እንዳትሰጠው አንተው በእጁ ስጥልኝ ብላ በጣም አጥብቃ አደራ ስላለችኝ በዛው ቀርቼ የሌላም ሰው ተራ ስሸፍን አድሬ አንተ ሳትመጣ ስለቀረህ ተስፋ ቆርጨ ገና ቅድም ነው የወጣሁት" አለኝ " መቼ ነበር የሰጠችህ?" " ትላንት ከሰአት! " ወይ አለመገጣጠም። ትላንት ማታ ከበሩ ላይ ደርሼ ያለእሷ ሆቴሉ እርቃን ሆኖብኝ ነበር ከደጅ ተመልሼ ሌላ ሆቴል የሔድኩት። ቆጨኝ።ጥፋተኝነት ተሰማኝ። " እና አሁን የት ነህ ወዴት ልምጣ?" " አሁን የአንድ ቀን ሙሉ ዕረፍት ስላለኝ ቤተሰብ ልጠይቅ በሚያሳዝ ሁኔታ ገጠር እየሔድኩ መኪና ውስጥ ነኝ" ተበሳጨሁ። በማን እንደሆነ ባይባኝም ተበሳጨሁ።እድሌን አማረርኩ። "እሺ! የትም ይሁን የሔድክበት ሀገር እመጣለሁ። የት ሀገር ነው የሄድከው?" _ ኧረ እባክህ ሩቅ ነው መንገዱም ምቹ አይደል ይመሻል። እኔ የጁቤ ከሚባል ሀገር ሁለተኛ መኪና ተሳፍሬ ኮርክ ወደሚባል ሀገር የሚሔድ መኪና ውስጥ ገብቼ እየሔድኩ ነው። ደሞ ኮርክ ከተማው ቢሆን ግድ የለም ግን እኔ ተመንገድ ቀርቼ 'የስበች' የሚባል 'ከየዳ ወንዝ' አለፍ ብሎ ያለ መንደር ስለምገባ በእግር የአንድ ሰዓት ጎዳና እጓዛለሁ። " ስልኩ መቆራረጥ እየጀመረ ነበር፤ በዛ ላይ ያለበት መንገድ ከባድ ፒስታ ለመሆኑ የመኪናው አካሎች ሲንጫጩ ከሱ ድምፅ ይልቅ ጎልቶ ይሰማኝ ነበረ። 'ግን አልቀርም' አልኩ ለራሴ። "አቅጣጫውን ብቻ ንገረኝ ሄሎ.." "አይ እስከዛሬ ከቆየኸው አይብስም ባሶሊበን ከመጣህ ማደርህ አይቀርም እንግዳ ተቀባዮች ነን የዚ የዚ ደግሞ እኔ ገስግሼ በበራሪው መኪና እደርሳለሁ ይቅርብህ አጉል ነው..." ከዚ በኃላ ኔትዎርክ ስላቋረጠን አትምጣ የሚል ስብከቱን ማድመጥ አቻልኩም ነበር። እስካሁን ሰምቻቸው የማለውቃቸው ሀገሮች ምን ብየ እንደምሔድ ቸገረኝ። በዛ ላይ ኔትዎርክ ካልሰራ እዛ ደርሼ የማን ያለህ ልል ነው፡፡ ያለኝ አማራጭ እስኪነጋ እሱን መጠበቅ ነው፡፡ ማታ ያን ያህልም ምግብ ሳይበላልኝ አልነጋ ብሎኝ እንዲሁ ስገላበጥ ጎህ ቀደደ። በጠዋት አስተነጋጁ ደወለልኝ።
የግርግዳ ሰዓቴ 1 ሰዓት ከ15 ይላል ትላንት በዚ ሰዓት እረፍት ያጣ አዕምሮየ ህመም ፈጥሮ እያሰቃየኝ ነበረ። አስተነጋጁ ቃሉን ጠብቆ በሌሊት ተነስቶ መምጣቱ ደስ አለኝ። በፍጥነት ተነስቼ ያለበት በመሄድ አገኝሁት። በእጁ ያንጠለጠለውን ጥቁር ፌስታል እንደ ሽልማት ከሰላምታ ጋርአስረከበኝ።
ለውለታው ባለዕዳ ብሆንም እንደተለመደው ጉርሻ በመስጠት ላለማስከፋትና ውለታውን ላለማጉደፍ ስል በወንድምነት ውለታውን ለመመለስ ስሙን ጠይቄ ጉጉቴን አምቄ አብረን ቁርስ እንድንበላ ጋበዝኩት እሱም ሳይግደረደር እሺ ብሎኝ ባቅራቢያችን ያለ ካፌ ጎራ አልን። ለኔ እያንዳንዷ ሰከንድ የአመት ያህል እየረዘመችብኝ ተቸገርኩ። ምግብ አዘን ከተቀመጥን ገና አምስት ያህል ደቂቃ እንኳን ሳይሞላ ትዕግስቴ ተሟጦ ያለወትሮየ አስተናጋጆቹ ላይ መነጫነጭ ጀመርኩ።
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
#የአይኔ_አበባ
...
እውነተኛ ታሪክ
#ክፍል 16
አንዳንዴ
'ምን ክፋ ነገር አጋጥሟት ይሆን?'
እያልኩ አስብ የነበረውን ክፉ ሀሳብ ሁሉ ትቼ ሰውነቴ በቁጣ ተንዘረዘረ፤ ፊቴ በትኩሳት ነደደ።
ቢያንስ አንዴ አንስታ ምናለበት ብታዋራኝ? አጥፍቼም ከሆነ ስህተቴን ብትነግረኝ።
ወጥቼ በደመ ነፍስ እያሽከረከርኩ የምሔድበት ግራ ገባኝና በቀጥታ ወደ ቤቴ አመራሁ።
ትክክለኛ ሰፈሯን ባለማወቄ በራሴ አዘንኩ። እንቅልፍ እንደተመኝሁት ቶሎ ባይወስደኝም አካሌ ዝሎ ስለነበር እኩለ ሌሊት አካባቢ ተኛሁ። ሲነጋ አንድ ሰአት አካባቢ ሆኗል። የሆነ ነገርነክቶ የቀሰቀሰኝ መሰለኝ፤ ሀይለኛ መሸበር ውስጤን አናወጠው። ልቤ ስንጥቅ አለብኝ። አቅለሸለሸኝና በፍጥነት ወደ መፀዳጃ ቤት ገብቼ አስመለሰኝ፤ ይሄ ነው የማይባል ጭንቀት ነፍሴን አሰቃያት። ከትንሽ ቆይታ በውሀላ አለፈልኝ። ቢሆንም ልቤ መጨነቁን ሊያቆም አልቻለም። ማታ ብዙ ይሆን እንዴ የጠጣሁት ስል አሰብኩ ግን ብዙም ከልክ ማለፌ ትዝ አልልህ አለኝ፤ ትንሽ ሞቅ ቢለኝም በጭራሽ አልሰከርኩም፤ ሁሉንም አስታውሳለሁ።
ስልኬ ጠራ አሁንም ከስራ ቦታ ሹፌሬ የእረፍት ጊዜው ስላለቀ አንድ ሁለት ቀናት ለመጨመር ፈልጎ መአት ምክንያት ሊደረድርልኝ
ነበር የደወለው። ለተጨማሪ አንድ ሳምንት ፈቀድኩለት። ወደራሴ እስከምመለስ ማንም አጠገቤ ሆኖ ስሜቴን
እንዲያጤንብኝ ስላልፈለኩ ነው ሀላፊነቱን ወስጄ ከጠየቀኝ በላይቀን ጨምሬ ያስደሰትኩት። የያይኔ አበባን ስልክ ሞከርኩኝ፤ አሁን ጭራሹን ዝግ ነው። ስልችት አለኝ። ስራ ቦታ ሔጄም ሰላሜን አጣሁ። ከሰዓት ማስረከብ ያለብኝን ፕሮጀክት መደምደሚያ ብቻ የቀረኝ ቢሆንም መጨረስ አቃተኝ። ብረር ብረር የሚል ስሜት ጨርቄን ሊያስጥለኝ ደረሰ። ምንም ስራ መስራት ስላልቻልኩ ገና አራት ሰአት አካባቢ ቢሮዬን ለቅቄ @MU::
ልቤ እርብሽ እርብሽ እያለ ተቸገርኩ ቤተሰቦቼ ጋር ደውየ ደህና መሆናቸውን አረጋገጥኩ።
ሁሉም ደህና ናቸው፡፡
ስለዚህ የያይኔ አበባ ናፍቆት መሆኑን አምኜ ተቀበልኩ ። ማታ ስልኳ እየሰራ ባለማንሳቷና እስካሁንም ባለመደወሏ ቢከፋኝም፣ ብናደድባትም ሳስባት ብቻ ግን እንዴት ጥምጥም ብየ አቅፌአት ሰላም እንደምላት ብቻ ነው የማሰላስለዉ።
ከንፈሬን ስትስመኝ ምላሽ ስላልሰጠኃትና በዝምታ ብቻ ስለተሳምኩ አዝናብኝ ይሆን እላለሁ። ወይስ እንዲሁ ሳልተነኩስ ስላሳደርኳት ወንድነቴን ንቃ ይሆን እላለሁ። ግን እንዴት እንዲ ላስብ እንደቻልኩ ሳስብ ደግሞ በልቤ ይቅርታ እጠይቃታለሁ። እንዴት ያን ሁሉ መከራ አሳልፋ በተራ ነገር እጠረጥራታለሁ? ያም ሆነ ይህ ቢያንስ አንዴ ላገኛት ይገባኛል።
እንዲ እያሰብኩኝ የት መሄድ እንዳለብኝ ዘንግቼው ኑሮ የበሀርዳርን መንገድ ይዤ ራሴን ወንቃ ጊወርጊስ አካባቢ ደረሼ አገኝሁት። ምን እየሆንበኩ ነው ብየ መኪናዋን ጥግ አሲዤ ትንሽ ከተረጋጋሁ በኃላ መኪናዋን አዙሬ ወደ ቤቴ መጓዝ ጀመርኩ። እንዴት ሰፈሯን አስሼ ላገኛት እንደምችል ሳወጣና ሳወርድ ቀድሞ ትማርበት የነበረው ት/ቤት የመሔድ ሀሳብ ብልጭ አለልኝ።
እዛ ቤታቸውን ሊያውቅ የሚችል አንድ ሰው እንደማገኝ አልተጠራጠርኩም። እስካሁን ባለማሰቤ ተናደድኩኝ።
በረጅሙ ተንፍሼ ከደብረ ማርቆስ ኤፍ ኤም ሬድዮ የሚፈሠውን ዘፈን እንደተለመደው ወደ ህይወቴ በመገልበጥ እያጣጣምኩ ፊቴን ወደ...ትምህርት ቤት አቀናሁ። ሬዲዮው ላይ ጎሳየ ተስፋዬ ነበር የሚያቀነቅነው "ሸጋ ልጅ ባሳቤ ድንገት ልቤ ገብታ ትመስላለች ቀን ማታ(2) ቀን ማታ(2) ሀሳብ ገባው ልቤን እረፍት የለው ፋታ ዛሬ ነገሳትይ ካለሽበት ቦታ (ደራርበሽ ነይልኝ የፍቅርሽን ኩታ) በአካል ድሸረሽልኝ በትዝታሽ ፋንታ(2) አዝማች እ ...ሄ..ኔ እንዳለሁ አለሁ ዛሬም በትዝታ(2) አመ.ኸ..ል ልምድ ሆኖብኝ እሄዳለሁ ቀን ማታ (2) ሰው ፈልጎ አያጣኝ ወይኔ ካገኝሁሽ ቦታ ብትን ሀሳቤ ይሰበሰባል እኔ እስኪለኝ ቆንጅዬ አይኔም እንቅልፉን ያኔ ያሸልባል እኔ እስኪለኝ ቆንጅዬ አንዴ ብቅ በይ አደቤን ልግዛ እኔ እስኪለኝ ቆንጅዬ አያድርስ ነው ኧረ እዳው በዛ እኔ እስኪለኝ ቆንጅዬ ወደው የጓጉትን የሽጋ ልጅ ገላ ቢመጠጥ አይጠግቡት እንደከረሜላ የትነሽ ነው የሚለው የወደደሽ ፍቅሬ ጣፍጦ አለማለቅን አሳይው ለልቤ አዝማች ማነ..ው ሰው ልመድ የሚለኝ ለኔ ካንቺ ሌላ ለኔ ካንቺ ሌላ ሲሆን አይደለም ወይ እየየም ሲደላ አታንሺው መቼም የኔን ሰቀቀን ምነው ባየሽው መተሽ ላንድ ቀን...." ኡፍ! ሙሉ ግጥምና ዜማውን እኔ ፅፌ የሰጠሁት መሠለኝ። ከራሴ ጋር አብጠርጥሬ አዋሀድኩት። እኛ ሰዎች ፍቅር የሚይዘን ለጥቂት ጊዜ ብቻ ሳይሆን ለዘለዓለም ላገኘው እችላለሁ ብለን ከምናስበው ሰው ብቻ እንጂ መልካቸውን ወይንም አመለካከታቸውን ከምንወደው ብቻ አይደለም፤ብንወደውም እንኳን አብረውን እንደማይኖሩ በጭራሽ ተስፋ ካላደረግን መውደድ እንጂ ፍቅር አይዘንም። እንዲያ ባይሆን ኑሮ በቴሌቪዥን የምንመለከታቸውን መልከ መልካምና ፀባየ ሰናይ የምንላቸውን ከአገር ውስጥ እስከ አገር ውጪ ያየናቸውን ታዋቂ ሰዎች ሁሉ አፈቀርኩ ብለን በተጃጃልን ነበር። አንድ የሬዲዮ ጣቢያ ላይ ደውላ 'ክርስቲያኖ ሮናልዶን አፈቅረዋለሁ' እንዳለችው ኢትዮጵያዊት ሴት 'ንክ' በተባልን ነበር። ግን ፍቅር እውር የሚያደረገን ልባችን መጀመሪያ አስተውሎ ባመነበትን ነገርስለሚወስን ይመስለኛል። እንዲህ እየተፈላሠፍኩ ትምህርት ቤቱጋ ደረስኩ። ጊቢው ጭር ብሏል። ገብቼ ጥበቃውን አናገርኩት። 'እኔ እዚ ከተቀጠርኩኝ ገና ስድስት ወር አልሞላኝም የምትላቸውን አስተማሪዎች አላውቃቸውም፡፡ ዛሬ እንደምታየው ግቢ ማንም የለም ስብሰባ ተብለው አስተማሪዎች በሙሉ ወተዋል' የሚል ምላሽ ሰጠኝ። እስከ ነገ መታገስ አልቻልኩም ዛሬ ላገኛት ይገባል። "በትምህርት ቀን የምናባታቸው ስብሰባ ነው? አርፈው አያስተምሩም፡፡ ትምህርት በሌለበት ቀን እሁድና ቅዳሜ አይሰበሰቡም!?" ስል ዘበኛው ላይ አምባረኩበት። በሱ ፍቃድ የወጡ ይመስል በድንጋጤ አይኑ ፈጦ ይመለከተኝ ጀመር። እኔም ትቼው ወደ ቤቴ አቀናሁ። ቤት ገብቼ መረጋጋት አልቻልኩም እቃዎችን ሰባበርኩ ከአልጋየ ላይ ፍራሹን አሽቀንጥሬ ጣልኩት። ግን ፍራሹ ሲነሳ ችፑዱ ስር በራስጌ በኩል የተጣጠፈች ቁራጭወረቀት አይቼ አነሳሁና አነበብኳት። "ናቲ ራት የምንበላበት ቤት ዕቃ አስቀምጥልሀለሁ። ነገ ማታ ነው የማስቀምጥልህ አንተ ግን ይህን ወረቀት ቀድመህ ካነበብከው እባክህ ከዛ በፊት አትፈልገኝ። ብዙ ጊዜ ለሚያስተናግደን ለቀዩ አስተናጋጅ እሰጠዋለሁ። ይህን ወረቀት ትራስህ ስር ያደረኩት ማታ ስትተኛ እንድታገኝው ስለፈለኩ ነው፡፡ የፃፍኩልህ ጠብቂኝ ብለኸኝ የወጣህ ሰዓት ላይ ነው መቼም ለማግኘት እንደማይረፍድብህ ተስፋ አደርጋለሁ በጣም እንደምወድህ እወቅ ሁሌም እወድሀለው እስከዛው ደና ሁንልኝ ያይኔ አበባ።" የሚል አጭር መልዕክት የተፃፈበት ወረቀት ነበር። ደነገጥኩ፤ 'ወይኔ!' አልኩኝ። 'ምን ወደታች አንሽራተተው? ለምን ስተኛ ልብ አላልኩትም?' ስል ተፀፀትኩ። በሀሳብ እየናወዝኩና ስለሷ አንዴ እያዘንኩላት አንዴ እያዘንኩባት መተኛት አቅቶኝ ስገላላበጥ እኔ ገፍቼው መንሸራተቱን ገመትኩ። ድሮስ ማ ሊሆን ይችላል? የዛሬው መናደዴ ለበጎ ነበር። ፍራሹን ባልወረውረው ኖሮ ወደ ያይኔ የሚመራ ምን አይነት ፍንጭ ላገኝ እችል ነበር? ዛሬ አንድ
ቀን አርፍጃለሁ ቢሆንም ከዚ በላይም ባለማርፈዴ ተፅናናሁ። ወጥቼ ወደ ተባልኩት ቦታ አቀናሁ። ወደ ሆቴሉ ስገባ በችኮላ
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
ከዛም ለመጨረሻ ጊዜ ቻው ስትለኝ እኔ ጣት ላይየነበረውን የብር ቀለበት አውልቃ ለሷ ወሰደችና የገዛሁላትን የወርቅ ቀለበት ከጄ ላይ ወስዳ ትንሿ ጣቴ ላይ ሰክታልኝ ከንፈሬን ስማ ተሰናብታኝ ወጣች። ለምንድነው እንደዚህ ግራ የምታጋባኝ?
ከወደደችኝ ምናለበት እሺ ብትለኝ? ወይስ ልታምነኝ ስላልቻለች ይሆን? ወይስ እንደሌሎች ሴቶች እየተግደረደረች ይሆን?
እስካሁን ምንም ነገር ከኔ የደበቀችኝ አልመሠለኝም፤ አሁን ግን ግልፅነቷ ጠፋብኝ። ቅኔ ሆነችብኝ። እምቢ ለማለት ብዙ በቂ አሳማኝ ምክንያት እንዳላት ባውቅም ምናልባት አንድ እድል ለመስጠት ብትሞክር ምን ነበረበት? ጥላኝ ብትወጣም ካልሸኝሁሽ ብየ አስቸገርኳት ሳትፈልግ በግድ አስፖልት ድረስ በእግራችን ሸኝኃት። ለነገሩ ሽኝት ለማለት ይከብዳል፤ ሁለታችንም በዝምታ ተውጠን ስለነበር ተከተልኳት ብል ይቀለኛል። ባጃጅ አሳፍሬአት ስመለስ አይኗ ላይ ያየሁት ሀዘን ልቤን እያሸበረው ፋታ ነሳኝ።የተሳ ፈረችው ወደ ሰፈራ እንዳልሆነ ምንም እንኳን ሰፈሯን ባላውቀውም ሌላ ቦታ መሆኑ ያስታውቅ ነበር ። ምናልባት አጠያየቄ ፍፁም ባልጠበቀችው መልኩ ይሆን ስል አሰብኩ። እንደወንድም ስላሰበችኝ ተቀይማኝ ይሆን? ታዲያ ለምን ከንፈሬን ሳመችኝ? መቼም እንደዚህ አይነት የወንድምነት መሳም የለም፡፡ ይህን ሳስብ ግን ውስጤን የሆነ ጭላንጭል ተስፋ ያረሰርሰው ጀመር። ምናልባትም ነገ ከነገ ወዲያ ብዙ ካሰበችበት በኃላ አንድ እድል ትሰጠኝ ይሆናል ማን ያውቃል? ስል ከንፈሬን በሳመችኝ ብቻ ከአህጉር የሰፋ የተስፋ ብርሀን ሰነኩኝ። ሲመሽ መተኛት አቃተኝ እንቅልፍ አልወስድህ አለኝ። ከመገላበጥ በስተቀር የእንቅልፍ
ሀገር ናፈቀኝ። ስለ ያይኔ ማሰብ ማቆም አልቻልኩም። 'ልደውል
አልደውል' ስል ተወዛገብኩ ሰዓቱ ወደሌሊት ቢጠጋም አንዳንዴ ተደዋውለን እስከዚህ ሰአት ድረስ አውርተን ስለምናውቅ ለመደወል ስልኬን አነሳሁ። ግን ስልኳ አይሰራም። ደጋግሜ ሞከርኩኝ ያው ተመሳሳይ 'አሁን ማግኘት አይችሉም' የሚል አሰልቺ ድምፅ ብቻ ነው የሚሰማኝ። በጣም ብዙ ሳወጣና ሳወርድ ቆይቼ ሊነጋጋ ሲል እንቅልፍ ወሰደኝ። ከእንቅልፌ ስነቃ መጀመሪያ የፈተሽኩት ስልኬን ነበረ፤ የተደወለ ምልክት ሳይ የአይኔ መሆኗን ሳልጠራጠርተንሰፍስፌ መልሼ ለመደወል ቁጥሩን ሳጣራ ከስራ ቦታ ነበር። ስራ መሔጃ ሰዓት በጣም ረፍዶ ነበር። ያለ ወትሮየ የሆነ ሰው ቁርስ ሰርቶ ቀስቅሶኝ 'ኧረ ስራ ረፈደብህ' የሚል የያይኔ አበባን አይነት ድምፅ እንዲያሰማኝ ናፈኩ። ወደስራ መሔድ ያልፈለኩኝ ቢሆንም በግድ መሔድ ስለነበረብኝ ብቻ ራስ ምታት እያሰቃየኝ ተነሳሁና ተጣጥቤ ወጣሁ። መንገድ ላይ ስልኳን ደጋግሜ ሞከርኩት አይሰራም። መልዕክት አስቀመጥኩላት፤ በጭራሽ አትመልስም። ስራ ቦታ ደርሼ እንደወትሮው ስራየን በአግባቡ መከወን አቃተኝ። ስልኬ መጥሪያው የማይሰማ እየመሰለኝ አስሬ እያነሳሁ አስቀምጠዋለሁ። ምናልባት ከስልኬ ከሆነ እያልኩ በባልደረቦቼ ስልክ በቢሮ ስልክ እሞክርላታለሁ፡፡ ግን ያንኑ አሰልቺ ድምፅ ብቻ እኔም በቃሌ እስከምሸመድደው ድረስ ደጋግሜ እሰማዋለሁ። ተነጫናጭ ሆኜ ዋልኩ። አለቃየን ሳይቀርተነጫነጭኩበት። ባልደረቦቼ በተጨዋችነቴ ቢያውቁኝም እንኳን ላዋራቸው ቀርቶ እነሱም የሚያወሩት እጅ እጅ አለኝ። ኬው መግባባት አቅቶኝ ዋልኩ። ይህ ቀን እንደምንም መሸልኝ። ቤት ገብቼ መቀመጥ አልቻልኩም። ወጣሁና ሁሌም ካሁን በፊት ራት እንበላበት የነበረ ሆቴል አቀናሁ። በር ላይ ስደርስ ግን ወደ ውስጥ መግባባት አልቻልኩም። ዝም ብየ አለፍኩትና ሌላ ቦታ ሄድኩኝ። እሷ ኖራበት አሁን የሌለችበት ቦታ ሁሉ የመቃብር ቦታ ያህል የሚያስጨንቅ ስሜት አለው፡፡ ራት በልቼ አንድ ሁለት ማለት ጀመርኩኝ። እንደ ትላንቱ እንቅልፍ እንዳያስቸግረኝ እያልኩ ደጋገምኩኝ። በያንዳንዱ ብርጭቆ ውስጥ እሷን አያታለሁ። ፍቅርበያዘኝ ብየ ፀልዮ አውቃለሁ። 'ፍቅር የማይዘኝ ለምን ይሆን?'
እያልኩ ብዙ አማርሬአለሁ። አሁን ደግሞ ምላሴን በቆረጠው ልል ምንም አልቀረኝም። እንዲ ከሆነ ባፍንጫየ ይውጣ ለማለት ዳዳኝ። የፍቅር ጣዕም ማጣፈጫ ቅመሙ ምናልባትም ስቃዩ ይሆናል። ቅናት፣ናፍቆት፣መለያየት ፣ መኮራረፍ፣አጉል የሆነ ጭንቀት፣ አንዱ ላንደኛው የሚከፍለው የጊዜ የገንዘብ የቤተሰብ ጫና የጓደኞች ትችትን ጨምሮ መስዋዕትነት የሚከፍሉለት የጣፋጭ ስቃዮች ጭማቂ ይሆን የእውነተኛ ፍቅር ገፅ? ያለሁበት ሆቴል ውስጥ የሙሉቀን መለሰ ዘፈን ይንቆረቆራል። አሁን አሁን ሁሉንም ዘፈን ስሰማ ወደራሴ ህይወት መተርጎም ጀምሬአለሁ። የሞኝ ፍቅር ይዞ የስከዛሬውን ሊወጣብኝ የዛተ ይመስለኛል።ሙሉቀን መለሰ " ልጅነቷ(3) እንዲያው ልጅነቷ አንቺ ለኔ(3) ሁኚልኝ የግሌ ይቀኙለት ቅኔ ይዘረፍ ይዘራ(2) በፈጠራት ፍጡር ይደነቅ ያብ ስራ ገና ህፃን ልጅ ናት ለጋ ያልበሰለች(2) ስጋየን ጨርሳ ካጥንቴ ተጋባች...." ዘፈኑን ከላይ እስከታች ከሷ ጋር ሳጣጥም በድንገት የማያቋርጥ ሙከራየ ተሳክቶ ስልኳ ጠራ፤ የላኩላት መልዕክት ከሀያ ሊበልጥ እንደሚችል መገመት የቻልኩት አሁን ነበር። ትንሽ እፍረት ተሰማኝ። ዳሩ ግን ስልኬን አታነሳም። ደጋገምኩት ይጠራል አታነሳም። ምን እየሆነች ነው? በጣም መናደድ ጀመርኩኝ። አንዳንዴ ምን አጋጥሟት ይሆን እያልኩ አስብ የነበረውን ክፉ ሀሳብ ሁሉ ትቼ ሰውነቴ በቁጣ ተንዘረዘረ፤ ፊቴ በትኩሳት ነደደ። ቢያንስ አንዴ አንስታ ምናለበት ብታዋራኝ? አጥፍቼም ከሆነ ስህተቴን ብትነግረኝ። ወጥቼ በደመ ነፍስ እያሽከረከርኩ
ክፍል 16 ይቀጥላል
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
ሰውለጉድ እስከሚመለከተን ድረስ ሁሉንም እየጣስን አደባባዪን ዞረን ዳሽን ባንኩ ጋ ስደርስ በፍጥነት ወርጄ የኤቲኤም (ATM) ካርዴን ተጠቅሜ ገንዘብ ሳወጣ ደረሰብኝ።
በንዴት ጦፎ "ግባና አሁኑኑ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ንዳዉ!" አለኝ አይኑ በርበሬ መስሏል። 'እሺ' ብየው አሁንም ወደፊት ነዳኃት " ወዴት ነው ምትሔደው?" አለኝ ሸጉጡን እየነካካ እኔ ግን እንደ ዛሬው በህይወቴ ደፋር ሆኜ አላውቅም መስታወቴን ዝቅ አድርጌ 'ሰውየ ሰላማዊ ዜጋ ልታሽብርበት ነው እንዴ መንግስት ያስታጠቀህ?' አልኩት መኪናዋን በዝግታ እያሽከረከርኩ እሱም ከጎን ከጎኔ እየተከተለኝ። "እሱን አትነግረኝም ትዞራለህ አትዞርም!?' አለኝ ሽጉጡን ከሰገባው እየመዠረጠ። ተናደድኩበት እንጂ በጭራሽ አልፈራሁትም። ወይእምየ ሀገሬ! የያዟት ስልጣን ትንሽም ሆነች ትልቅ ብትሆን ሰውነታቸውን ታስረሳቸዋለች። ከስልጣን የተነሱለት ብቻ ተራ ሰው እንደነበሩ በስልጣናቸውም ምንም ፋይዳ ያለው ነገርአለመስራታቸውና የሰሩት ግፍም መዘዙ ትዝ ስለሚላቸው ስልጣናቸውን ለማስከበር አጉል ጀብደኛ እንሁን የሚሉባት ሀገር። ምን እንደዚ ያስደነፋዋል? ባንድ ጊዜ ውስጥ ለምን ተፈታተንከኝ ስልጣኔን ለምን ተዳፈርከኝ ብሎ እንደ አባቱ ገዳይ ያየኛል እንዴ!? 'እሺ መጀመሪያ መድሀኒቱን ልግዛ ከዛ ውጪ ግን ሰው ስገል ወይም ስሰርቅህ አልያዝከኝም በቂ ምክንያት ካለህ ተኩስ!' ብየው ወደፊት ነዳኃት። ምን እንደታየው እንጃ እየተናደደና እየዛተ ታርጋየን ፅፎ ተመልሶ ሔደ። 'እፎይ' አልኩ፤ ግን ታዲያ እስካሁን ታርጋየ አልነበብ ብሎት ነው? አዘንኩላቸው ለሹፌሮች!ጣና ገበያ ከመድረሴ በፊት አንድ ወርቅ ቤት አየሁና መኪናየን አቁሜ ዘው ብየ ገባሁ፡፡ አሁን ትራፊክ ፖሊሱ ቢያየኝ ኑሮ ምን ይለኝ ይሆን?
ለነገሩ እሱ አላስጨነቀኝም።'የሆነ የራሴ የምለው የግል ነገር ሳይኖረኝማ አላገባም' እል የነበርኩት ልጅ ዛሬ ቀለበት ለመግዛት ወርቅ ቤት ተገኝሁ። ሰው ያሰበውን የሚኖረው ከስንት አንዴ ነው። አሁን ያለኝ ነገር ትዳር ለመያዝ በቂ ነገር እንደሆነ የገባኝ አሁን ነው። ሰው ደስተኛ ለመሆን ከፈለገ ያለውን ነገር አስተውሎ ፈጣሪውን ማመስገን ነው እንጂ ያለበት ፍላጎቱ ገደብ የለውም። ሳስተውል ብዙ ነገር አለኝ፤ ግን ያጣሁትና የጎደለኝ ይመስለኝ የነበረው ነገር ዛሬ ፍንትው ብሎ ታየኝ። የጎደለኝ ፍቅር ነበር! ፍቅርከጎደለ ደግሞ ሙሉ የሚባል ነገር የለም። ፍቅር ከሌለ ደስታና ሰላም ጥግ ይዘው ስቃይና መከራ ሀዘንና ጭንቀት እየተፈራረቁ ሲቦርቁ በትዝብት ተመልካች ይሆናሉ። ገና ከመግባቴ አይኔ ያረፈበትን የቀለበት ዲዛይን ለሷ በሚሆናት ልክ ገዝቼ እየተጣደፍኩ ወደ ቤቴ በረርኩኝ። ፊቴ ጥርስ በጥርስ ሆኗል። ከቤት ከወጣሁ አርባ አምስት ያህል ደቂቃ ሆኖኝ ነበር። ወርጄ ወደ ጊቢ እየተጣደፍኩ ስገባ የአይኔ አበባ ለመሔድ በሬን እየቆለፈች ደረስኩባት። 'መጥቻለሁ መጥቻለሁ!' አልኳት። ዞር ብላ ተመለከተችኝና "ጊዜየ አብቅቷል" አለችኝ ግንባሯን ቅጭም አርጋ። 'የምን ጊዜ! ይቅርታ በናትሽ ለምን እንደዚ ትቸኩያለሽ? አንዴ ለደቂቃዎች ብቻ!' ከቅድሙ የበለጠ ለምኜ ወደቤት አስገባኃት። አከራየ 'ወይጉድ' እያሉ ሲመለከቱኝ አይቻለሁ፤ የራሳቸው ጉዳይ! ትንሽ አረፍ እንዳልን ወሬ እንዴት እንደምጀምር መላው ጠፍቶኝ 'የት ሔጄ የመጣሁ ይመስልሻል?' ስል ጠየኳት። "ስራ ቦታ፤ ብዙ ጊዜ አስተውየሀለሁ ከሁሉም ነገር ስራህን ታስቀድማለህ" አለችኝ ኩርፊያዋ ሳይለቃት እንደህፃን ልጅ ሙጥሙጥ ብላ። ኩርፊያ እሷጋ ሌላ ውበት ነው ይሄን ውበት ለማየት ስል ወደ ፊት በቀን ሁለት ወይም ሶስት ጊዜ ሳላስኮርፋት አልቀርም ስል አሰብኩ። ቅፅበታዊ በሆነ መልኩ እግሯ ስር ተንበረከኩና 'የኔ ቆንጆ እኔ ልብሽን ልጠግንልሽ ባልችልም እባክሽን እንዳክምልሽ ፍቀጂልኝ እንደንግስት አንቀባርሬ ላኖርሽ ባልችል እንኳን እስከለተሞቴ ታማኝ ባሪያሽ ልሁንልሽ፤ ሰዎች ልብሽ ውስጥ ያዳፈኑትን እሳት ባላጠፋልሽም እባክሽን በፍቅር እንዳቀዘቅዘው ፍቀጂልኝ፤ ጥቂት ሰዎች ውስጥሽን በጭለማ የጋረዱብሽን ሙሉ ለሙሉ በብርሃን ላፈካው ባልችልም እንኳን ጭላንጭል የተስፋ ወጋገን ላብራበት፤ የኔ ማር እባክሽ ትንሽ ብቻ ከወደድሽኝ ይበቃኛል እኔ የምሰጥሽ ፍቅር ለሁለታችንም ለዝንተዓለም የሚበቃን ይሆናል። አንቺ ያልወደድሽውን ምንም ነገር ላላደርግ፤ ልታመንልሽና ቃሌን ልጠብቅልሽ በፈጣሪ ስም እምላለሁ። ታገቢኛለሽ!?> ስል በተማፅኖ አይን አይኗን እየተመለከትኩ ጠየኳት። ከአይኖቿ የወረዱ የእንባ ዘለላዎች ግንባሬ ላይ ተንጠባጠቡ። ሀዘን ይሁን ደስታ መለየት አቃተኝ። ጣቷን ወደ ያዝኩት ቀለበት አላስጠጋ አለችኝ። በፀጥታ ትርንጎ ትርንጎ የሚያካክል እንባ ካረገፈች በውሀላ "አንተ ጥሩ ሰው እንደሆንክ መጀመሪያም አምኜብህ ነበር። በታማኝነት ሳታስቸግረኝ እንደ ወንድም አቅፈህ ያሳደርከኝ ብቸኛው ወንድ አንተ ነህ። እኔ ስስምህ ሳትስገበገብ መልሰህ ያልሳምከኝ ብቸኛው ሰው አንተ ነህ፤ ማታ አንገቴ ስር ስትስመኝ እንቅልፌን ሙሉበሙሉ አልተኛሁም ሰምቼሀለው። እንደሌሎቹ ታስቸግረኝ ይሆን ስል ደንግጬ ነበር፤ ግን ያንተ መሳም እንደ ሌሎች አልነበረም በጣም እወድሃለሁ! አከብርሀለሁ! ግን ላገባህ አልችልም! እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ በፍፁም ላገባህ አልችልም!" እንባዋ አንደጎርፍ ይፈስ ነበር። የወደደችኝ መስሎኝ ስለነበር ይሁን እንጃ መልሷ ፍፁም ያልጠበኩት ሆነብኝና እኔም ሳላዝበት እንባየ በጉንጮቼ እየተንከባለለ ወረደ። በህይወትቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ያነባሁላት ሴት ነበረች።
እንባዎቼን ጠራረገችልኝና እኔ እንደተንበረከኩ እሷም ወንበሩ ላይእንደተቀመጠች ጭንቅላቴን ሳብ አድርጋ ግንባሬን ደረቷ ላይልጥፍ አደረገችና እናት ህፃን ልጇን እንደምታባብል አይነት ፀጉሬን
እያሻሸችኝ ሁለታችንም ተላቀስን። እኔ እንቢ ስላለችኝ ሰማይምድሩ ዞሮብኝ እንዴት ክፉ ትዝታዋን አጥፍቼላት እንዴት ህመሟን አሽሬላት እሺ እንድትለኝ ማድረግ እንደምችል ቸገረኝ። በጣም ለመንኳት ግን መቼም መሆን እንደማይቻል አስረግጣ እምቢ አለችኝ።
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
#የአይኔ_አበባ
እውነተኛ ታሪክ
#ክፍል 15
ልብሴን በፍጥነት ቀያየርኩኝ። ዛሬ በጭራሽ አላፈርኳትም እንዳውም ብዙ አመት የማውቃት ያህል ዘና ብየ ነበር። አዎ! እስከ ዛሬ እንደእሷ በግልፅነት ያወኳት ሴት የለችም። ሁሉም በህይወቴ ያጋጠሙኝ ሴቶች የሌላቸውን አለን ያልሆኑትን ነን ያላወቁትን እናውቃለን የሚሉና ልባቸውና አፋቸው ፈፅሞ ያልተገጣጠሙ አስመሳዮች ናቸው፡፡ ገላቸንው ለውሸታቸው ማስተባበያ እንጂ ለፍቅር ብለው የማያቀርቡ ርካሽና ተራ የፍቅር ደላላዎች ነበሩ። ወይም 'የግሌ አደረኳት' ስል 'ስለወደድኩህ ካንተ ጋ ላይፍ(life) ማሳለፍ ብቻ ፈልጌ ነው' ብለው ሀሳቤንና ልቤን ከመስበርየማይቦዝኑ ተራ ሴቶች ነበሩ ህይወቴን ሞልተው የማግባት ፍላጎቴን ቀርቶ ቋሚ ፍቅረኛ የመያዝ ምኞቴንም የሰለቡት። እኔም እንደነሱ ላይፌን አጣጥሜ ሲበቃኝና ደሞ ልጅ ሲያምረኝ የመውለድንና ልጅ የመሳምን ስሜት ለማጣጣም ስል ብቻ የማገባ ይመስለኝ ነበር። አሁን ግን አለመገጣጠም መሆኑ ወለል ብሎ ተገለጠልኝ። አንዱ ሲያፈቅር አንደኛው እያላገጠ በአንደኛው ንፁህ ልብ አንደኛው እያፌዘ ብዙ ንፁህ ልቦች በጥቂት ክፉ ልቦች ምክንያት እየተመረዙ ሰው እምነት በማጣቱ ምክንያት ፍቅር የለም እየተባለ እንደመዝሙር ማዜም ተጀመረ። ግን ሰው ልብ ካለው ደም መርጨቱ አይቀርም። ደሙ በስርዓት ከረጨ ደግሞ በህይወት መኖሩ አይቀርም፤ በህይወት ከነጤነኛ ልቡ ካለ ደግሞ ማፍቀሩ ከፈጣሪ የተሰጠው ፀጋ በመሆኑ ያፈቅራል። እኔም የማፍቀር ፀጋዬ ተገልጦልኝ ያይኔ አበባን አፈቀርኳት። በውበቷ ብቻ ሳይሆን
እሷነቷን ስለተቀበልኩት የነፍሴን ያህል ሳሳሁላት። ፍቅር ባይኖርኖሮ ወይም ሁሉንም ሰው የማይዘው ቢሆን ኑሮ እንደኔ የማይያዝ ልበ ደንዳና ባልኖረ ነበር። ያይኔ አበባ ልመናየ አሳዘናት መሰል ሳቅ ብላ "የምትሔድበትን ከነገርከኝ እጠብቅሀለሁ ካለበለዚያ ግን ከ2ዐ ደቂቃ በላይ አልታገስህም እሺ!" አለችኝ ' እሺ ቶሎ እመለሳለሁ የምሔድበትን ስመለስ እነግርሻለሁ አሁን ጊዜ የለኝም ቻው ' ብያት ስወጣ "ናታን ቆይ፤ አንዴ ቆይ!" አለችና ወደ ቤት ውስጥ አስመለሰችኝ። ' አቤት ' አልኳት ፊት ለፊቷ ቆሜ። አተኩራ ተመለከተችኝና አንገቴን እቅፍ አርጋ ጉንጬን ሳመችኝ። እንደ አጥር እንጨት ደርቄ ቀረሁ። እሷ ግን ሳታቋርጥ ሌላኛውን ጉንጬንና ግንባሬን ከሳመችኝ በውኃላ የቀኝ እጄን መዳፍ በሁለት እጆቿ ጥብቅ አርጋ ይዛ ሳመችውና እጄን ደረቷ ላይ ልጥፍ አድርጋ ያዘችው። ልቧ በሀይል ሲደልቅ ተሰማኝ፤ ዳሩ የኔም ትርታ ከመፍጠኑ የተነሳ ልቤ ወደውጪ ለመውጣት እየታገለችኝ ነበር። እስከዛሬ በወሲብ ካገኘሁት ደስታ ይልቅ ዛሬ ጉንጬን ብቻ ተስሜ ያገኝሁትን እርካታ ወደር አጣሁለት። ነፍሴ በሀሴት ጮቤ ረገጠች፤ ልቤ እስክትወርድ ድረስ ዳንኪራ ረገጠች። ያይኔ አበባን ስመለከታት በአይኖቿ 'ወድጄሀለሁ' ያለችኝ መሠለኝ። "በቃ ቸኩለሀል አደል መሄድ ትችላለህ ምናልባት ከዘገየህና ካልተገናኝን ብየ ነው" ስትለኝ ወደራሴ ተመለስኩ። ለመቅረት ከጅሎኝ ነበር፤ ግና መሔድ ያለብኝ ለሁለታችንም የሚጠቅም ቦታ እንጂ ለስራ ጉዳይ ስላልነበረ መሔዴ የግድ መስሎ ታየኝና መኪናየን አስነስቼ ነፍሷ እስኪጠፋ ጋለብኳት። ትዕግስት በማጣቴ የማይደረብ ቦታ ስደርብ ትራፊክ ፓሊሰ አስቆመኝ። ' ምን እየሆንክ ነው ናታን ' አልኩኝ ለራሴ ምን ያህል እየተንቀለቀልኩ እንደነበር ገብቶኝ። "እስኪ መንጃ ፍቃድህን አሳየኝ" አለኝ ፖሊሱ ገና አጠገቤ ከመድረሱ፡፡ ' ይሄው ጋሼ ' አልኩት መጀመሪያም ሰዓት ለመቆጠብ ስል አስቀድሜ ተዘጋጅቼ መንጃ ፍቃዴን በእጄ ይዤ እየጠበኩት ስለነበር በፍጥነት እያቀበልኩት። "እዚጋ የሚደረብበት ቦታ ነው?"
' ኧረ በፍፁም አይደለም ጋሼ በጣም ስለቸኮልኩ ነው ይቅርታ አድርግልኝ እባክህ አያቴ ታማ ዶክተሩ በፍጥነት መድሀኒት ገዝተህ ካልመጣህ ትሞትብሀለች ስላለኝ ለዛ ነው ያጠፋሁት በጣም ይቅርታ ' አልኩት በሆዴ ራሴን 'አቤት ውሸት' እያልኩኝ። እሱ ግን ምንም ርህራሔ አላሳየኝም። በርግጥም ሰበቤ የእውነት ቢሆንም ኖሮ እንኳን ልክ ነው አያቴን ለማዳን እኔ መሞት የለብኝም ነበር። የባጥ የቆጡን እያወራ ሰዓቴን ሲገልብኝ ትዕግስቴ ነጠፈ። ከመኪናየ ወረድኩና ለመንኩት ብር ፈልጎ ከሆነ ብየ ለመስጠት ሞከርኩኝ ግን ሰዎች በአካባቢያችን እያዩን መሆኑን ጭራሽ ዘንግቼው ኖሮ የተለመደውን ጥንቃቄ ስላላደረኩለት በሙስና እንደሚከሰኝ ዛተብኝ። ሆን ብሎ ጊዜየን በማባከን ተፈታተነኝ ስለመማይመለከተው ነገር ሁሉ እየደሰኮረ አበሳጨኝ ምን እንደሚፈልግ አልገባህ አለኝ። የግል ቂም ያለበትና የግል ፀብ የሚፈልግ መሠለኝ። ከዚ በፊት የማውቀው ቢሆን በሀሳቤ እርግጠኛ በሆንኩኝ ነበር፤ ቁጥት ብየ እጄን እየዘረጋሁለት ' እሺ ቶሎ በል ፃፍብኝና የክስ ወረቀቱን ስጠኝ ' አልኩት። "አንተ ነህ ስራየን እንዴት እንደምሰራ የምትነግረኝ?" ብሎ አፈጠጠብኝ። እኔም አያቶቼን በህይወት ስሌሉ ነው እንጂ የምር ቢሆን እንዲ እታገሰው ነበር? ብየ ሳስብ ደሜ እየተንተከተከ ገነፈለብኝ፡፡ ' ወረቀትህን ብላው! ' አልኩትና መንጃ ፍቃዴን ከእጁ ላይ መንትፌ መኪናየ ውስጥ ገባሁና ከመጀመሪያየ በባሰ ፍጥነት አበረርኳት፤ እሱም ሞተር ሳይክሉን አስነስቶ ተከተለኝ። ምንም ጥያቄ የለውም ጥፋተኛ ነኝ። ግን ትራፊክ ፖሊሶቻችን ከማስተማርና ተገቢውን ቅጣት በአግባቡ ከመቅጣት ይልቅ ማን እንደሆኑና ምን ማድረግ እንደሚችሉ ስልጣናቸውን ለማሳየት እየጣሩ ወይም ለራሳቸው ጥቅም ብቻ ቅድሚያ እየሰጡ ብዙ ሹፌሮችን በማበሳጨት ከቀልባቸው ሆነው እንዳያሽከረክሩ በማድረግ የአደጋ መንስኤ ይሆናሉ። እኔን ካጋጠሙኝ ትራፍሪክ ፖሊሶች ውስጥ ሙስና ሊቀበለኝ ያልሞከረው አንድ ፖሊስ ብቻ ነው እሱም የሰፈሬ ልጅና አብሮ አደጌ በመሆኑ ነው። በስፖኪዬ (በኃላ መመልከቻ መስታት) ስመለከተው የአሜሪካ ፊልም እንደምንቀረፅ ሁሉ እኔ ላይ ለመድረስ ይከንፋል።
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
አዲስ ትረካ ነገም ሌላ ቀን ነው ክፍል 30 ምርጥ ትረካ ከቻግኒ ሚዲያ
🍿#ሼር #ሼር #በማረግ_ተባበሩን
Share" @Mesac_tireka "
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
