fa
Feedback
የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት

የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት

رفتن به کانال در Telegram

government development organization

نمایش بیشتر
1 875
مشترکین
-324 ساعت
-27 روز
+7530 روز
آرشیو پست ها
"የዘንድሮው ምርጫ ኢትዮጵያውያን ጽንፈኝነትን በተግባር ያሸነፉበት ነው" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ፣ የዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ በርካታ ትምህርቶች የተገነዘቡበት እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዘመናት የኖረውን ድልብ የሀገር ግንባታ ባሕል በተግባር ያረጋገጠበት ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ወቅት፣ ምርጫው ራሱ የጥቃት ዒላማ ተደርጎ የነበረ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን የተሰነዘረውን ጥቃት በጽናት መክቶ አሸናፊ መሆን መቻሉን አስታውቀዋል። "በዘንድሮው ምርጫ አይሳካም" የሚለው አፍራሽ ሐሳብ የብዙዎች ድምፅ ሆኖ በነበረበት ወቅት፣ ኢትዮጵያውያን በአንድነት በመቆም ጽንፈኝነትን በተግባር ውድቅ ማድረጋቸውንም አብራርተዋል። ለዚህም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከፍተኛ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። በምርጫው ሂደት ላይ የታየውን ሕዝባዊ ተሳትፎ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ አዛውንቶች፣ ታማሚዎች፣ ሐዘንተኞች እና እመጫቶች ጭምር በከፍተኛ ስሜት እና ቁርጠኝነት መሳተፋቸውን ጠቁመዋል። ይህ የታየው ከፍተኛ ድምፅ እጅግ ታላቅ መልዕክት ያዘለ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ መንግሥት ይህንን የሕዝብ ውሳኔና ድምፅ በግዴለሽነት እንደማይመለከተውና ከፍተኛ ክብርና ዋጋ እንደሚሰጠው በቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። "ይህንን የሕዝብ ታላቅ ድምፅ አቅልለን አንወስደውም፤ ትልቅ ክብር እንሰጣለን።" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጠናቀቀው ምክር ቤት ውስጥ ለነበራቸው ቆይታ የምክር ቤቱ አባላት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ላቅ ያለ ምሥጋና አቅርበዋል። አያይዘውም በቀጣዩ የሥራ ዘመን በምክር ቤቱ ውስጥ የማይቀጥሉትን አባላት ጨምሮ፣ ሁሉም ወገኖች ወደፊትም ለሀገር ግንባታና ለሕዝብ አገልግሎት የሚያደርጉትን ንቁ ተሳትፎና በጎ አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በ6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተነሡ ጥያቄዎች፦ * 👉 የወደብ የኅልውናችን ጉዳይ ነው፤ የወደብና የባህር በር ጉዳይ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ቢገልጹልን? 👉 የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሂደት በተያዘለት የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ተጠናቅቆ የታለመለትን ሀገራዊ ዓላማ እንዲያሳካ መንግሥት በቀጣይ ምን ዓይነት የሎጂስቲክስ፣ ፖለቲካዊና ተቋማዊ ድጋፍ ያደርጋል? 👉 ተጀምረው ላልተጠናቀቁ እና ታቅደው ላልተጀመሩ ፕሮጀክቶች ምን የታሰበ ነገር አለ? 👉 አነስተኛ ገቢ ላላቸው እና ለመንግሥት ሠራተኞች የኑሮ ጫናን ለመቋቋም ምን ታስቧል፤ ከሚመሠረተው አዲሱ መንግሥት ምን እንጠብቅ? 👉 የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ስለሆነ ለሁሉም ክልሎች አስገዳጅ ሆኖ ቢቀርብ? 👉 የመንግሥት መዋቅር ተጠቅሞ በዜጎች ላይ ምዝበራ የሚፈጽሙ አካላት ላይ ገዥው ፓርቲ መዋቅሩን የማጽዳት እና ተጠያቂነትን የማስፈኑን ጉዳይ እንዴት ሊያስተካክለው አስቧል? 👉 ከፀጥታ አኳያ እየተሻሻሉ ያሉ ጉዳይ ቢኖርም፣ አሁንም አንዳንድ ቦታዎች ችግሮች አሉ፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን መፍትሔ ለመስጠት ታስቧል? 👉 ከነዳጅ ጋር በተያያዘ፦ መንግሥት ለነዳጅ ድጎማ ቢያደርግም የነዳጅ ሽያጭ እና ስርጭት ከብልሹ አሠራር ሊድን አልቻለም። በዚህ ላይ መንግሥት የያዘው መፍትሔ ምንድን ነው? 👉 በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የትግራይ ሕዝብ የሰላም እንዲያገኝ በመንግሥት በኩል እየተደረገ ያለውን ጥረት ቢያሳውቁን?  👉 ሰላምን ወደ ዘላቂ መሠረት ለማሸጋገር ከምሁራን፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከህዝቡ ምን አይነት ንቁ ተሳትፎ ይጠበቃል? 👉 በትላልቅ ፕሮጀክቶች ምክንያት የሚነሡ ዜጎች መብት በአግባቡ እየተጠበቀ አይደለም የሚል ቅሬታ አለ። ፍትሐዊ የሆነ የካሳ አከፋፈል እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ምን ይደረጋል? 👉 የጠቅላይ ኦዲተር ሪፖርቶች ተደጋጋሚ የፋይናንስ ጉድለቶችን ቢያሳዩም፣ ተጠያቂነትን በማስፈን ረገድ ክፍተቶች አሉ። መንግሥት ተቋማትን ከሙስና እና ከመዝባሪ ኃይሎች ለማጽዳት ምን አዲስ አሠራር ይዘረጋል?

ከመመገብ ባሻገር!! በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ከመመገብ ባሻገር ማህበራዊ ፍትህን የምናነግስበት እና ለነዋሪዎቻችን  ፍቅርና ክብር ከሰጠንበት ስራዎች አንዱ  የሆነውን የተስፋ ብርሃን የምገባ ፕሮግራማችን ዛሬ 30ኛውን ማዕከል ገንብተን ስራ አስጀምረናል። በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ 4ኛ ቅርንጫፍ የሆነው ይህ 30ኛው የተስፉ ብርሃን የምገባ ማዕከል ከቂርቆስ፣ ከሸራተን ማስፋፊያ እና ከካሳንቺስ አካባቢ  ህጋዊ ቤት ሳይኖራቸው በጥገኝነትና በደባልነት ይኖሩ የነበሩ አቅመ ደካሞች ፣ ምንም ቋሚ ገቢ ያልነበራቸው ፣ አራብሳ  ቤት ሰርተን ያስገባናቸው አረጋዊያን እና ለተለያዩ ማህበራዊ ችግር የተጋለጡ ነዋሪዎቻችን የሚኖሩበት  አካባቢ በመሆኑ የምገባ ማዕከል በመጀመር ጊዜያዊ ችግራቸውን በማቃለልና  በዘላቂነት ቋሚ የሥራ እድል እንዲያገኙ የሚያስችል ስራም የጀመርንበት ማዕከል ነው። በከተማችን የገነባናቸው ተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከላት  ሰው ተኮርነታችን በተግባር የሚገለጥባቸው፣ ጊዜያዊ ችግሮችን የምንፈታባቸው ሲሆኑ በዘላቂነት ደግሞ ሌት ተቀን በመስራት  ሃገራችንን ለማበልፀግ ግባችንን ለማሳካት እንተጋለን። በከተማችን ማህበራዊ ሃላፊነትን  መወጣት እያደገ የመጣ ሲሆን፤ ዛሬም ካላችሁ  በማካፈል  አብራችሁን የሰራችሁ እንዲሁም በማዕከሉ በቋሚነት ለመመገብ ቃል የገባችሁ  በጎ አድራጊዎችን በተጠቃሚ ነዋሪዎቻችን ፣በከተማ አስተዳደራችንና በራሴ ስም አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

በእንጦጦ ተራራ «ተስፋን እንትከል» በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተካሄደ ሰኔ27/2018:-የአዲስ አበባ ከተማ  የመንግሥት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ባለፉት ዓመታት ሲያከናውን የቆየውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ቀጣይነት በማረጋገጥ፣ ዘንድሮም «ተስፋን እንትከል»በሚል መሪ ቃል በእንጦጦ ተራራ ላይ ደማቅ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሂዷል። በዕለቱ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ተጠሪ የልማት ድርጅቶች አመራሮች ሰራተኞች በተገኙበት በሺዎች የሚቆጠሩ የሀገር በቀል ዕፅዋት ችግኞች ተተክለዋል። የአዲስ አበባ የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተንኩዌይ ጆክ በወቅቱ እንደገለጹት፣ ይህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተቋሙ ለአካባቢ ጥበቃና ለቀጣይ ትውልድ ካለው አጋርነት ባሻገር፣ በየዓመቱ የሚተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ረገድ ያሳየውን ስኬት የሚያስቀጥል ነው። «ተስፋን እንትከል» የሚለው መሪ ቃልም ሀገራዊ የልማትና የዕድገት ጉዞን በአረንጓዴ ልማት ለማገዝ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል። የአካባቢ ጥበቃ ዘላቂነት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና የከተማዋን ተፈጥሯዊ ውበት ለመጠበቅ የድርሻውን መወጣት ደህንነትና እንክብካቤ ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች የደራሱበትን ደረጃ በመገምገም፣ የዘንድሮዎቹም በልዩ ሁኔታ ክትትልና እንክብካቤ እንደሚደረግላቸው ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለው ገልፀዋል። የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባወይ ዮሐንስ በበኩላቸው ተቋሙ በቀጣይም ከተከላው ባሻገር ችግኞቹ ሙሉ በሙሉ ጸድቀው ለአገልግሎት እስኪበቁ ድረስ አስፈላጊውን የባለቤትነትና የክትትል ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። መረጃው:-  የአ.አ.የመንግስት ልማት ድርጅቶች  አስ/ባለስልጣን ነው::

በኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት ስራ ተቋራጭነት፤ በአፍንጮ በር ሳይት የሚገኘው የ4B+G+15 የመኖሪያ ቤቶች አፓርትመንት የህንፃ ግንባታ ስራ የፕሮጀክት አፈፃፀም በምስል፡፡

ሰዉ አጠፋዉ፤ ሰዉ አለማዉ!! ፈጣሪ የሰጠንን ቀበና “ሰዉ “ አጠፋዉ ፤ ይህ የተፈጥሮ ስጦታ መጥፋት ቁጭት ያደረበት “ሰዉ “ ደግሞ ቀበናን ዳግም እንደ አዲስ እንዲወለድ አደረገዉ። የቀበና ወንዝ ለዘመናት በዘፈን እና በትዝታ ብቻ ስሙ ሲነሳና ሲወደስ ኖሮ ዛሬ ግን ዳግም እንዲወለድ አድርገን  አለማነዉ!! አርቲስት ፀሀዬ ዮሀንስ “ቢሻን ቀበና” እያለ ብዙዎች እየዋኙ ያደጉበትን የልጅነት ትዝታን ሲቀሰቅስ ፣የክብር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ “ቢሻን አዲስ አበባ “ እያለ ሲያደናንቅ በዘመናት ውስጥ ግን ትዝታን ብቻ ተሸክሞ የወንዙ ተፈጥሯዊ ማንነት ጠፍቶ ፣የፍሳሽ መዉረጃና የቆሻሻ መጣያ ሆኖ፣ ጠረኑ አላስጠጋ ብሎ ተረስቶ የኖረ ወንዝ ነበር ። እነሆ እነዚህ የብክለት ፣ የበሽታ ምንጭና የቆሻሻ ማጠራቀሚያ የነበሩትን ወንዞቻችንን  ዛሬ ላይ በትጋት እና በላብ እየታከሙ፣ ለነዋሪው ተስፋን ሀሴትን የሚለግሱ የደስታ ምንጭ እየሆኑ ነው፡፡ በአጭር ጊዜ የተገነባው ይህ ድንቅ ፕሮጀክት፣ ከሌሎች የከተማዋ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ጋር ተዳምሮ አዲስ አበባን የውበት ማማ አድርጓታል። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ከብልሹ አሰራር የፀዳ የግዥ ሥርዓት ለማስፈን ሥልጠና ሰጠ ሰኔ 20/2018 :-የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን
+5
የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ከብልሹ አሰራር የፀዳ የግዥ ሥርዓት ለማስፈን ሥልጠና ሰጠ ሰኔ 20/2018 :-የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን በልማት ድርጅቶች ውስጥ ግልጽ፣ ተጠያቂ፣ ውጤታማና ከብልሹ አሰራር የፀዳ የግዥ ሥርዓት እንዲገነባ ለተጠሪ የልማት ድርጅቶች አመራሮችና ዳይሬክተሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል። ሥልጠናው የግዥ ሂደቶች በሕግ፣ በግልጽነትና በተጠያቂነት እንዲፈጸሙ፣ የመንግስትና የሕዝብ ሀብት በአግባቡ እንዲጠበቅና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተንኩዌይ ጆክ እንደገለጹት የልማት ድርጅቶች ውጤታማነት የሚረጋገጠው ግልጽ፣ ፍትሃዊና ሕግን የተከተለ የግዥ ሥርዓት ሲገነባ መሆኑን ገልጸዋል። የመንግስትና የሕዝብ ሀብት በከፍተኛ ኃላፊነት ሊመራና ሊጠበቅ እንደሚገባ በማስገንዘብ፣ብልሹ አሰራርን በመከላከል ረገድ አመራሮችና ዳይሬክተሮች የራሳቸውን ኃላፊነት በብቃት ሊወጡ እንደሚገባ አቶ ተንኩዌይ አክለው ተናግረዋል። የሥልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በግዥ ሂደቶች ውስጥ የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች በመለየት፣ ዘላቂ መፍትሔዎችን በተግባር ለማዋልና የግዥ ሥርዓቱን ይበልጥ ግልጽ፣ ተጠያቂና ውጤታማ ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል። መረጃው:የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ነው::

በሙያ ደህንነትና ጤንነት ፖሊሲና ስትራቴጂ ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡   ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት፣ በሙያ ደህንነትና ጤንነት ፖሊሲና ስትራቴጂ፣በፖሊሲው መርሆዎችና ዋና ዋና ግቦች፣በሙያ ደህንነትና ጤንነት ተከታታይ ኮሚቴ ምንነት፣አመሰራረት፣ የኮሚቴው ተግባርና የአሰሪው ሃላፊነት በተሰኙ ርእሶች ዙሪያ ለድርጅቱ የሙያ ደህንነትና ጤንነት ተከታታይ ኮሚቴ አመራሮችና አባላት የተዘጋጀ የ1 ቀን የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ይህንን ስልጠና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የሙያ ደህንነትና የስልጠና ባለሙያ በሆኑት አቶ ስንታየሁ ለገሰ በኩል ተሰጥቷል፡፡  በዚህ ስልጠና የሙያ ደህንነትና ጤንነት ፖሊሲ ዋና መሰረቱ ሰራተኞችን ከስራ ቦታ ከሚከሰቱ አደጋዎች በመከላከል ደህንነትና ጤንነታቸውን ማረጋገጥ መሆኑን አቶ ስንታየሁ አፅንኦት በመስጠት ገልፀዋል፡፡ አቶ ስንታየሁ ማብራሪያቸውን በመቀጠል፣በአንድ ድርጅት ውስጥ የሙያ ደህንነትና ጤንነት መኖር በአሰሪና በሰራተኛ መካከል ጤናማና መልካም የስራ ግንኙነትን በማሳደግ የኢንዱስትሪ ሰላምን ማስፈን እንደሚቻል አስረድተው፤ ምቹ የስራ ቦታ እንዲፈጠር በማድረግም ድርጅቱ ምርትና ምርታማነቱ እንዲጨምርና የገበያ ተወዳዳሪነቱን በማሳደግም ትርፋማ እንዲሆን የሚያስችለው መሆኑን አክለዋል፡፡ በመጨረሻም ከስልጠናው ተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና ሃሳብ አስተያየቶች አቶ ስንታየሁ በቂ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተው ስልጠናው ተጠናቋል፡፡ የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት

ድርጅቱ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የኒቨርሲቲ ባዘጋጀው ዓመታዊ ዓውደ ርእይ ላይ በመሳተፍ ምርትና አገልግሎቶቹን አስተዋወቀ፡፡   ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት፣የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀውና ተመራቂ ተማሪዎች ወደ ስራ ዓለም ለመሰማራት ሲፈልጉ ቀጣሪ ድርጅቶችንና ካምፓኒዎችን እንዲያውቁ፣ ሙያቸውን እንዲያዳብሩና በቀጣይም ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል የሚል ታሳቢን ያደረገ ዓላማን ያነገበ አውደ-ርእይ በዩኒቨርሲቲው ኮሜርሻል ኮምፕሌክስ ህንፃ ውስጥ ለጎብኚዎች ክፍት ተደርጓል፡፡   በዚህ ለጎብኚዎች ክፍት በተደረገውና፣ “ከቀጣሪዎች ጋር ይገናኙ የስራ እድልዎን ያስፉ ትስስር ይፍጠሩ!” በሚል ርእስ እ.ኤ.አ በ2018/2019 በተጀመረውና ዘንድሮ ለ5ኛ ጊዜ በተካሄደውና የተለያዩ የግልና  መንግስታዊ የልማት ድርጅቶች በተሳተፉበት በዚህ ዓመታዊ አውደ ርእይ ላይ የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት በቦታው ተገኝቶ ምርትና አገልግሎቶቹን ለጎብኚዎች አስተዋውቋል፡፡   የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር አብርሃም ዲባባ በአውደ-ርእዩ  መዝጊያ ስነ ስርዓት ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ተመራቂ ተማሪዎች በኢንዱስትሪዎች ላይ እንዲገኙና ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር በመገናኘት በቀጣይ በሚሰሯቸው ስራዎች ግንዛቤ እንዲያገኙና እንዲተዋወቁ ይህ አውደ ርእይ መዘጋጀቱ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል፡፡   በመጨረሻም በአውደ ርእዩ ላይ ተሳታፊ ለሆኑ ድርጅቶች የተሳትፎ የምስክር ወረቀት በክብር እንግዳው የመስጠት ስነ-ስርዓት ተከናውኖ መርሃ ግብሩ ተጠናቋል፡፡   የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት