የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት
الذهاب إلى القناة على Telegram
1 888
المشتركون
-324 ساعات
+107 أيام
+2930 أيام
أرشيف المشاركات
+5
ወደ ተቋሙ ለተቀላቀሉ አዲስ ቅጥር ሠራተኞች የቅድመ-ሥራ ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ
የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታ እና ማማከር ድርጅት ወደ ተቋሙ ለተቀላቀሉ አዳዲስ ሠራተኞች ያዘጋጀውን የቅድመ-ሥራ ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡
ሥልጠናው በሰው ሀብት ልማትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት፣ በውስጥ ኦዲት ቡድን እና በሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት በጋራ የተዘጋጀ ሲሆን፤ አዳዲስ ሠራተኞች የድርጅቱን አሠራር፣ ሕግና ደንብ ተረድተው ወደ ሥራ እንዲገቡ ለማስቻል ያለመ ነው።
በሥልጠናውም የንብረት አመዘጋገብ እና ቁጥጥር አሠራር በድርጅቱ የውስጥ ኦዲት ቡድን መሪ በወ/ሮ ኤልሳ ተክለሥላሴ ሰፊ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ የድርጅቱን ንብረት በአግባቡ የመጠበቅ፣ የመመዝገብና የመቆጣጠር ሥርዓትን በተመለከተ ገለጻ ተደርጓል።
በመቀጠልም በሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ ያሬድ በሪሁን አማካኝነት በተሰጠው ሥልጠና የተቋሙ ዋና ዋና የሥነ-ምግባር እሴቶች፣ በኮንስትራክሽን ዘርፉ በሚታዩ የሥነ-ምግባር ስጋቶችና ጥሰቶች፣ የሥነ-ምግባር መመሪያ ጥሰት የሚያስከትላቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎችና የወንጀል ተጠያቂነቶች ላይ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል።
በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ በተዘጋጀው ሰነድ ዙሪያ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሥልጠና ሰጪዎቹ አማካኝነት በቂ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት መርሃ-ግብሩ በስኬት ተጠናቋል።
የቢዝነስ ዴቨሎኘመንት ዳይሬክቶሬት
ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
በኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት ስራ ተቋራጭነት፤ በገላን ጉራ ሳይት በፍጥነትና በጥራት እየተገነቡ የሚገኙት የሁለት ብሎኮች (ብሎክ 16 እና17) የB+G+12 የመኖሪያ ቤቶች አፓርትመንቶች የህንፃ ግንባታ፣ የሁለቱም ብሎኮች ጣራ የማዋቀር ስራዎች ተሰርተው መጠናቀቃቸውን የሚያሳዩ ምስሎች።
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
የሚዲያ ጥቆማ
የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት በስራ ተቋራጭነት በመርካቶ ቅጠል ተራና በአፍንጮ በር የግንባታ ሳይቶች በመገንባት ላይ የሚገኙ የፕሮጀክት ስራዎች አፈፃፀምን እንዲሁም በዲዛይንና ማማከር ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን አስመልክቶ የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ /AMN/ ቴሌቪዥን ጣቢያ በአፋን ኦሮሞ የሰራውን ዘገባ “አባ ሚሶማ /Abbaa Misoomaa/” ፕሮግራም ላይ ማክሰኞ ምሽት ከ3፡30 ሰዓት ጀምሮ የሚያስተላለፍ በመሆኑ እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም
ትጋት ያሸልማል!
በ2018 በጀት ዓመት የህዝባችንን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎችን በመስራት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቢሮዎች፣ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች እውቅናና ሽልማት አበርክተናል።
በዚሁም መሰረት፦
የካቢኔ አባል ከሆኑ ቢሮዎች፦(መኪና ተሸላሚዎች)
1ኛ. ሰላምና ፀጥታ ቢሮ
2ኛ. ጤና ቢሮ
3ኛ. ገቢዎች ቢሮ እና ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ
4ኛ. ትምህርት ቢሮ
5ኛ. ልዩ ተሸላሚ የሆነው :-ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል
ከክፍለ ከተሞች፦ (መኪና ተሸላሚዎች)
1ኛ. ቦሌ ክፍለ ከተማ
2ኛ. ለሚኩራ ክፍለ ከተማ
3ኛ. አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ
የካቢኔ አባል ካልሆኑ ተቋማት፦ (መኪና ተሸላሚዎች)
1ኛ. ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
2ኛ. መንገዶች ባለስልጣን
3ኛ. ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን
4ኛ. አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለስልጣን
5ኛ. ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ሲሆን
በተጨማሪም 33 ወረዳዎች፣ ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከእያንዳንዱ ወረዳ ከአንድ እስከ ሶስት የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው ተሸላሚ ሆነዋል።
የካቢኔ አባል ከሆኑ ቢሮዎች፦የሰርተፍኬት ተሸላሚዎች
1. ፋይናንስ ቢሮ
2. ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
3. ኮሙኒኬሽን ቢሮ
4. ንግድ ቢሮና
5. ፍትሕ ቢሮ
የካቢኔ አባል ካልሆኑ ተቋማት፦(የሰርተፍኬት ተሸላሚዎች)
1. ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት
2. የመስሪያ ቦታዎች ልማት አስተዳደር
3. አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ
ከክፍለ ከተሞች:-
(የሰርተፍኬት ተሸላሚዎች)
1. ኮልፌ ክፍለ ከተማ
2. ልደታ ክፍለ ከተማና የካ ክፍለ ከተማ ናቸው።
ዛሬ የተሰጠነው እውቅናና ሽልማት የሁሉም አመራር፣ በየደረጃው ያሉ ባለሞያዎች፣ የባለድርሻ አካላት እና አብሮን ለሰራው ህዝባችን ለጋራ የቅንጅት ስራ የተሰጠ ሲሆን ይህም ይበልጥ ሰርተን የህዝባችንን የመልማት ፍላጎት የምናሳካበት፣ የውድድር መንፈስን የምንፈጥርበት፣ ወደኋላ የቀሩት ራሳቸውን ፈትሸው ወደፊት የሚመጡበት እንጂ የሚያዘናጋን አይደለም።
በመሆኑም፤ እውቅናው በቀጣይ በጀት ዓመት አልቀን በመስራት የህዝባችንን ተጠቃሚነት እንድናረጋግጥ፣ የአገልግሎት ተደራሽነትን አልቀን እንድንሰራ ከትልቅ አደራም ጭምር ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን አብዝቶ ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በመርካቶ የቅጠል ተራ ሳይት የG+7 የበጎ ፍቃድ ሁለት ብሎኮች የመኖሪያ ቤቶች የህንፃ ግንባታ የፕሮጀክት ስራዎች በጊዜና በጥራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ።
ሃምሌ 11/2018 ዓ.ም፡- የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት በመርካቶ የቅጠል ተራ ሳይት በበጎ ፍቃድ እየገነባቸው ከሚገኙት ህንፃዎች መካከል፣ የብሎክ A የG+7 የመኖሪያ ቤት ህንፃ በፍጥነትና በጥራት በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡
የብሎክ A የግንባታ ስራ አሁን ላይ፤ የግንባታ ግብዓቶችን ከመሬት ወደ ላይኞቹ የህንፃው ወለሎች ለማጓጓዝ የሚረዱ የዊንች መግጠም ስራና የሊፍት ክሬን ስራዎች ተጠናቀው አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ የህንፃው የተለያዩ ክፍሎች የውስጥ ልስን ስራም እንዲሁ ተጠናቋል፡፡
በዚሁ የግንባታ ሳይት በመሰራት ላይ የሚገኘው ሌላው የብሎክ I የG+7 የመኖሪያ ቤት ህንፃ ግንባታ በተመለከተ ደግሞ የግሬድ ቢም /አግድም ብረት/ የአርማታ ሙሌት ስራ ተጠናቆ የሃርድ ኮር ስራ /የተከሰከሰ ድንጋይ/ እና የኮንክሪት ሙሌት ስራዎችን ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ከሳይቱ የፕሮጀክት ማኔጀርና ከሳይት ኢንጂነሮች የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
በመርካቶ የቅጠል ተራ ሳይት፣ የሁለት ብሎኮች የG+7 የበጎ ፍቃድ የመኖሪያ ቤቶች የህንፃ ግንባታ የፕሮጀክት ስራዎች በጊዜና በጥራት በመከናወን ላይ መሆናቸው ተገለፀ።
ሃምሌ 8/2018 ዓ.ም፡- የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት ካለፉት የበጀት ዓመታት ጀምሮ የከተማውን ህብረተሰብ ተጠቃሚነት ባረጋገጡ በተለያዩ የበጎ ፍቃድ የግንባታ ስራዎች ላይ በስራ ተቋራጭነት በመሳተፍ የራሱን አሻራ ያኖረ ሲሆን፣አሁንም በተለያዩ ሳይቶች በከፍተኛ ተነሳሽነት በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
ከእነዚህ የበጎ ፍቃድ የግንባታ ስራዎች ውስጥም በመርካቶ የቅጠል ተራ ሳይት በተለያዩ ስራ ተቋራጮች እየተገነቡ ከሚገኙት ከ9 የበጎ ፍቃድ የG+7 የመኖሪያ ቤቶች የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክቶች፤ ድርጅቱ በስራ ተቋራጭነት በመሳተፍ የሁለት ብሎኮች /ብሎክ A እና ብሎክ I/ የG+7 የመኖሪያ ቤቶች ህንፃዎችን በፍጥነትና በጥራት በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡
ይህ ፕሮጀክት በድርጅቱ ከፍተኛ አመራር የቅርብ ከትትልና ድጋፍ እንዲሁም በሳይቱ የግንባታ ባለሙያዎች የስራ ትጋት በልዩ ትኩረት እየተገነባ የሚገኘው የብሎክ A የግንባታ ስራ አሁን ላይ፤ የህንፃው የብሎኬትና የስትራክቸር ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል፡፡
የዚህ ብሎክ /ብሎክ A/ ህንፃ የውስጥ ልስን ስራም በመጠናቀቅ ላይ ያለ ሲሆን፤ የኤሌክትሪክና የሳኒተሪ መስመር ዝርጋታ ስራዎችም በመሰራት ላይ ከመገኘታቸው በተጨማሪ የህንፃውን የውጭ ልስን ስራዎችንም ለመጀመር የዊንች ገጠማ በመሰራት ላይ ይገኛሉ፡፡
በተመሳሳይ በዚሁ የቅጠል ተራ የፕሮጀክት ሳይት የብሎክ I የG+7 የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ስራ አሁን ላይ፣ የፉቲንግ ፓድ፣ የባክ ፊል እና የማሶነሪ ግንብ ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን የሊን ኮንክሪት ስራዎችንም በማጠናቀቅ ግሬድ ቢም ኮንክሪት ለመሙላት የብረትና የፎርም ወርክ ስራዎች በመሰራት ላይ እንደሚገኝ የሳይቱ የፕሮጀክት ማኔጀር ገልፀዋል፡፡
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
በመርካቶ የቅጠል ተራ ሳይት፣ የሁለት ብሎኮች የG+7 የበጎ ፍቃድ የመኖሪያ ቤቶች የህንፃ ግንባታ የፕሮጀክት ስራዎች በጊዜና በጥራት በመከናወን ላይ መሆናቸው ተገለፀ።
ሃምሌ 8/2018 ዓ.ም፡- የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት ካለፉት የበጀት ዓመታት ጀምሮ የከተማውን ህብረተሰብ ተጠቃሚነት ባረጋገጡ በተለያዩ የበጎ ፍቃድ የግንባታ ስራዎች ላይ በስራ ተቋራጭነት በመሳተፍ የራሱን አሻራ ያኖረ ሲሆን፣አሁንም በተለያዩ ሳይቶች በከፍተኛ ተነሳሽነት በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
ከእነዚህ የበጎ ፍቃድ የግንባታ ስራዎች ውስጥም በመርካቶ የቅጠል ተራ ሳይት በተለያዩ ስራ ተቋራጮች እየተገነቡ ከሚገኙት ከ9 የበጎ ፍቃድ የG+7 የመኖሪያ ቤቶች የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክቶች፤ ድርጅቱ በስራ ተቋራጭነት በመሳተፍ የሁለት ብሎኮች /ብሎክ A እና ብሎክ I/ የG+7 የመኖሪያ ቤቶች ህንፃዎችን በፍጥነትና በጥራት በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡
ይህ ፕሮጀክት በድርጅቱ ከፍተኛ አመራር የቅርብ ከትትልና ድጋፍ እንዲሁም በሳይቱ የግንባታ ባለሙያዎች የስራ ትጋት በልዩ ትኩረት እየተገነባ የሚገኘው የብሎክ A የግንባታ ስራ አሁን ላይ፤ የህንፃው የብሎኬትና የስትራክቸር ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል፡፡
የዚህ ብሎክ /ብሎክ A/ ህንፃ የውስጥ ልስን ስራም በመጠናቀቅ ላይ ያለ ሲሆን፤ የኤሌክትሪክና የሳኒተሪ መስመር ዝርጋታ ስራዎችም በመሰራት ላይ ከመገኘታቸው በተጨማሪ የህንፃውን የውጭ ልስን ስራዎችንም ለመጀመር የዊንች ገጠማ በመሰራት ላይ ይገኛሉ፡፡
በተመሳሳይ በዚሁ የቅጠል ተራ የፕሮጀክት ሳይት የብሎክ I የG+7 የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ስራ አሁን ላይ፣ የፉቲንግ ፓድ፣ የባክ ፊል እና የማሶነሪ ግንብ ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን የሊን ኮንክሪት ስራዎችንም በማጠናቀቅ ግሬድ ቢም ኮንክሪት ለመሙላት የብረትና የፎርም ወርክ ስራዎች በመሰራት ላይ እንደሚገኝ የሳይቱ የፕሮጀክት ማኔጀር ገልፀዋል፡፡
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
የመርካቶ የቅጠል ተራ ሳይት፣ የሁለት ብሎኮች የG+7 የበጎ ፍቃድ የመኖሪያ ቤቶች የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት ስራዎች
በፒያሳ ገዳም ሰፈር ሳይት የአንድ ብሎክ የB+G+8 የበጎ ፍቃድ መኖሪያ ቤቶች የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም፡- በአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 5 አስተዳደር ክልል ውስጥ ልዩ ቦታው ፒያሳ ገዳም ሰፈር ሳይት፣ ባለቤትነታቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ የሆኑ ሶስት ብሎኮች የበጎ ፍቃድ የB+G+8 የመኖሪያ ቤቶች የህንፃ ግንባታ ስራዎች በተለያዩ ስራ ተቋራጮች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡
በዚህ ሳይት እየተገነቡ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች ውስጥም የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት በስራ ተቋራጭነት አንድ ብሎክ የB+G+8 የመኖሪያ ቤቶች ህንፃን ለመገንባት ከባለቤቱ ተረክቦ የግንባታ ስራውን በፍጥነትና በጥራት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
400 ካሬ ሜትር በሚሸፍን ቦታ ላይ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የግንባታ ስራውን የጀመረው ይህ ፕሮጀክት አሁን ላይ፤ የአፈር ቁፋሮ ስራዎች፣ የፓድ ኮንክሪት ስራዎች እንዲሁም የፋውንዴሽን ኮለም ስራዎች ተሰርተው የተጠናቀቁ ሲሆን፤ በቀጣይ ጊዜያት ደግሞ የባክ ፊል ስራዎችን ለመስራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ከሳይቱ የፕሮጀክት ማኔጀር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
በፒያሳ ገዳም ሰፈር ሳይት የአንድ ብሎክ የB+G+8 የበጎ ፍቃድ መኖሪያ ቤቶች የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት አፈጻጸም
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የG+4 ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት በጊዜና በጥራት በመሰራት ላይ ይገኛል፡፡
ሃምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት በስራ ተቋራጭነት እየገነባቸው ከሚገኙት የፕሮጀክት ስራዎች ውስጥ ለተለያዩ አገልግሎቶች /Mixed Use Building/ እንዲውል ታስቦ እየተገነባ የሚገኘውና ባለቤትነቱ የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የሆነው የG+4 የህንፃ ግንባታ ስራ ይገኝበታል፡፡
ይህ የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅትን የፕሮጀክት የመፈፀም አቅምን በጉልህ የሚያሳየውን የግንባታ ስራ፣በተያዘለት ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለባለቤቱ ለማስረከብም በፍጥነት እና በጥራት እየተሰራ ይገኛል፡፡
የዚህ የግንባታ ስራ አሁን ላይ፤ የህንፃው የ3ኛው ወለል የስትራክቸር ስራዎች ተሰርተው የተጠናቀቁ ሲሆን፣የ4ኛው ወለል የፎርም ወርክና የብረት ስራዎች እንዲሁም የግራውንድ ወለል የብሎኬት ስራዎች በመሰራት ላይ ይገኛሉ፡፡
ከዚሁ ፕሮጀክት ጋር በተያያዘ በባለስልጣኑ ግቢ ውስጥ በሚገኘው በጋራዡ የውጨኛው ቦታ ላይ የፓርኪንግ ስራ ተጠናቆ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን፤ በተጨማሪ በዚሁ ቦታ ላይ በነዳጅ ማደያው ዙሪያ በመሰራት ላይ የሚገኘውን የሪጅድ ፔቭመንትን ደግሞ በኮንክሪት ለመሙላት ዝግጅት እየተደረገ የሚገኝ መሆኑን ከሳይቱ የኮንስትራክሽን መሃንዲስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
