አፋብን ጎጠግ በላይ ዕዝ
رفتن به کانال در Telegram
የአማራ ህዝብ እያደረገ ያለው የህልውና ትግል የሚዘገብበት የትግል ቻናል ነው። ለማንኛውም ጥያቄ @Heaven11111ያግኙን
نمایش بیشتر5 807
مشترکین
-424 ساعت
-267 روز
-10730 روز
آرشیو پست ها
5 807
የቀጠለ...
ይህ እየታገልነው ያለው ጨፍጫፊ ስርዓት የአማራ ልዩ ሐይልን በበተነበት ሰዓት ስናይፕር ይዞ በመውጣትና ትግሉን በመቀላቀል ተወልዶ ባደገበት ምዕራብ ደንቢያ፤ ጉራንዲ ወንበባና አካባቢው ወጣቱን በማደራጀት አንጫጫው ሻለቃን በመመስረት ትግሉን ከለኮሱት ጓዶቹና የትግል አባቱ እራ ደረጀ በላይ ጋር በመናበብ ትግል ጀምሯል።
ከጯት ከተማ በቅርብ እርቀት ራሱ በመሰረተው አንጫጫው ሻለቃ እየተንቀሳቀሰ ጯሒት የነበረን የስርዓቱ ሐየል በማፈራረስ ቁጥር አንድ አፈፃፀም ነበረው።
እየቆየ ሲሔድ፤ የአመራር ብቃቱ፣የወታደር ሙያው፣ የተገራ ስነ-ምግባሩና የአላማ ፅናቱ ወደ ሌላ ሐላፊነት እንዲታጭ ምክንያት ሆኖት የግዙፉ ናደው ብርጌድ ዋና አዛዥ በመሆን አንድ አመት በላይ አግልግሏል።
በብርጌድ አመራርነቱም የነበረው ወታደራዊ ልምድ በተፈጥሮ ከተቸረው የአመራር ብቃት ጋር ተዳምሮ ብርጌዷን ጠላት በስሟ ብቻ እንዲናድ አድርጎ በመስራት ብዙ የጠላትን ቅስም የሰበሩ ጀብዶችን ፈፅሟል።
ሙያውና የአፈፃፀም ብቃቱ ከገራገር ባህሪው ጋር ተዳምሮ የሰራዊቱ ልብ ውስጥ የገባው አርበኛ ታድሎ ወርቄ(ጠቅል) የበጌምድር ሰራዊት በስስት የሚወደው ደፋር ታጋይ በመሆኑ የክፍለጦር ዘመቻ መሪ እንዲሆን ተመረጦ እስከተሰዋበት ሰዓት ድረስ ግዙፉን በጌምድር ክፍለጦር በዘመቻ መሪነት በብቃትና በጀግንነት መርቷል።
አርበኛው በ1987 ዓ/ም ከላይ በተጠቀሰው ቦታ የተወለደ ሲሆን ባለትዳርና የሶስት ልጆች አባት ነበር።
በትናትናው ዕለት ማለትም በ08/2018 ዓ/ም በጭልጋና ጣቁሳ ወረዳ አዋሳኝ የሚገኝ ጨውድባና ወርቅድባ በተባለ ቦታ ላይ ከቀኑ 9:00 ገደማ በተጀመረውና እስከ ምሽቱ 2:00 በዘለቀው እልህ አስጨራሽ ትንቅን ከሚመራው ሰራዊት ጋር የጠላትን ሐይል በከፍተኛ ሁኔታ ከደመሰሱ በኋላ በክብርና በጀግንነት ተሰውቷል።
ሽዎችን መርቶ፤ አስተምሮ፤ በአምሳሉ ቀርፆ የተሰዋው ግዙፉ አርበኛ ታድሎ ወረቄ በመስዕዋትነቱ አዲሰ የትግል ምዕራፍ ለኩሶ አርፏል። ውዱ ጓዳችን የተሰዋለት ውዱ ትግል በአምሳሉ በቀረፃቸው ጓዶቹ ተጧጡፎ ይቀጥላል።
"ሐዘናችን በእለቅሶ ሳይሆን በዘመቻ እንወጣለን"
"አናለቅስም ጓዴ"!
እንደ እሸቴ ሞገስ እንደ ሸዋው ጀግና፣
የአብራኩ ክፋይ ይታገስ ሞቶበት
"አላለቅስ" ብሎ በቃሉ እንደፀና፣
እቅድክን ሳንጨር
እኛም አናለቅስም ቃል አለብን እና።
"አናለቅስም ጓዴ"✊
በሰላም ዕረፍ!
የአፋብን ጎጠግ ዕዝ!
5 807
ከአፋብን ጎጠግ ዕዝ የተሰጠ የሐዘን መግለጫ፦
የአማራን ህዝብ ህልውና ለማረጋገጥ በሚደረገው ተጋድሎ ጀግኖች በደም ቀለም ደማቅ ታሪክ እየፃፉ እያለፉ ይገኛሉ።
ትውልድን ለማረሰቀጠልና ለብዙኃኑ ህልውና ሲባል ጀግኖችን መገብር የግድ በሆነበት በህልውና ትግላችን ለቃላቸው የታመኑ ጀግኖች ከጠላት ጋር ጉርንቦ ለጉርንቦ ተናንቀው መሰዕዋትነት እየከፈሉ ይገኛሉ።
ትግሉን በደሙ ከለኮሰው አርበኛ አይሸሽም ዮሐንስ ጀምሮ በሶስት አመት ቆይታ ውስጥ ብዙ የትውልዱ ፈርጦችን ገብረናል።
በጎንደር ቀጠና ከሚጠቀሱት ቀደምት ክፍለጦሮች ተርታ የሚመደበው ግዙፉ በጌምድር ክፍለጦር ከጎንደር ከተማ እስከ አርማጭሆ፤መተማ፤ገንደዋ፣መሸሐ፣ላስታ ሽመለጋራ በርሐወች፤ እንዲሁም ከአዘዞ አየር ማርፊያ ጀምሮ ደንቢያ፣ጣቁሳ፣አለፋ፣ቋራ፣ደለጎ፣ሽንፋ ዱባባ፣ቱመት፣ፎድሮዶ፣መንዶካ፣ ሻሽየና በዙሪያው ያሉ በርሐማ ቦታወች በሙሉ ያልተዋጋበትና ጠላት ያላረገፈበት ቀጠና የለም።
ክፍለጦሩ በእነዚህ ሁሉ ቀጠናወች በሚያደርገው ተጋድሎ እንቁ ጀግኖችን ገብሯል።
ይህ መራር መስዕዋትነ ዛሬም የቀጠለ ሲሆን አርበኛ ታድሎ ወርቄ( አባ ጠቅል)፤ አዲሱ ትውልድ እየመነዘረ ሊጠቀምባቸው የሚችሉ ጀብዶችን ሲፈፅም ኖሮ በትናትናው ዕለት ማለትም የካቲት 08/2018 ዓ/ም ጠላትን ሲረፈርፍ ውሎ በጀግንነት ተሰውቷል።
አርበኛ ታድሎ ወርቄ(አባ ጠቅል) አስከ አስረኛ ክፍል ከተማረ በኋላ ገና በለጋ እድሜዎ ወደ ውትድርና ህይወት የገባ ሲሆን የአማራ ልዩ ሐይልን በመቀላቀል የሚወደውን ህዝብ ያገለገለ የልዩ ሐይል ኮማንዶ ነበር።
5 807
#መረጃ
መንገድ ላይ የነበረ የጠላት ጦር ተደመሠሠ።
ትናት ማለትም በቀን 08//06/2018 መነሻውን ከጭልጋ ወረዳ ጫንድባ ከተማ አድርጎ ወደ ጣቁሳ ደልጊ አቅጣጫ ጉዞ ያደረገ ሐይል ተደመሰሰ።
በአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በጌምድር ክፍለጦር እና ዞብል ጃኖ ክፍለጦር ጥምር ሀይል መንገድ ላይ ተቆርጦ የተከበበው የጠላት ሐይል በከፍተኛ ሁኔታ የተደመሰሰ ሲሆን አብዛኛው ሐይል የመንገድ እራት ሆኖ መንገድ ላይ ቀርቷል።
በጭልጋና ጣቁሳ ወረዳ አዋሳኝ የሚገኝ ጨውድባና ወርቅድባ በተባለ ቦታ ላይ ከቀኑ 9:00 ገደማ በተጀመረውና እስከ ምሽቱ 2:00 በዘለቀው እልህ አስጨራሽ ትንቅን ከፍተኛ ተጋድሎ የተደረገ ሲሆን ጠላት ጭኖት ይንቀሳቀስ የነበረ አብዛኛው ጓዝ ከነ ሰራዊቱ ጭቃ ሆኖል።
የጠላት ሻለቃ አመራርን ጨምሮ መቶ አለቃና ትይዩ ሐላፊነት ያላቸውን አመራሮች እንዲሁም በመቶዎች የሚቆጠር መስመራዊ መኮንኖችና ሌሎች የስርዓቱ የፀጥታ ሐይሎች ተደምስሰዋል።
አብዛኛው የጠላት ቁሳቁስ በነበረው የተኩስ ልውውጥ የጋየ፤ በቁጥር ከ150 በላይ ሙትና ቁስለኛ ያስተናገደ ሲሆን የጓዝ መጫኛ የነበሩ የተሽከርካሪዎች ገልብጠው ሙትና ቁስለኛ ማመላለሻ ሆነው አምሽተዋል። በወገን በኩል ሁለት ጓዶች በክብር ተሰውተዋል።
ከዚሁ ትናት ውጊ ከተደረገበት ቦታ ላይ በ12 ቀን ልዩነት ውስጥ የትናቱ ውጊያ ለአራኛ ጊዜ ሲሆን የትናቱን ጨምሮ 2 ሻለቃ ፤ 5 መቶ አለቃና ሁለት ሎጅስቲክ መምሪያዎች፤በድምሩ 9 የጠላት ሐይል አመራሮች ከ250 በላይ ሙትና ቁስለኛ ከ150 በላይ የመሳሪያ ምርኮና ከ25ሽ በላይ ቅይጥ ተተኳሽ ገቢ ሆኗል።
በአሁኑ ሰዓት የጠላት ሐይል ቁሰለኞቹን ከወረዳ ወረዳ አንቀሳቅሶ ማሳከም እንዳይችል መንገዱ ሁሉ በቆረጣ የተዘጋ ሲሆን የኤሊኮፍተር አመራጭን እንደ የመጨረሻ አማራጭ እየተጠቀመ ይገኛል።
ስለ ተሰውት ጓዶች ተጋድሎና ስለሰሩት ጀብድ እንመለሳለን።
ድል ለአማራ ፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!
አፋብን ጎጠግ ዕዝ ግንኙነት መምሪያ!
የካቲት 9/2018 ዓ/ም
Fb:https://www.facebook.com/share/p/1AeyFcLR82/
5 807
ከላይ የቀጠለ...
የድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ መወለድ ያስገኘው የአንድነት መንፈስ ለተገኙ ወታደራዊ ድሎች ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። የድላችን ምስጢር ያለው አንድነታችን ላይ መሆኑም በተግባር ተረጋግጧል። ድርጅታዊ አንድነታችንን በጠበቀ መልኩ ከኢትዮጵያዊያን እና ከቀጠናው ኃይሎች ጋር የሚደረግ ትብብር አገዛዙን ሙሉ በሙሉ ለማስወገድ ወሳኝ ሂደት መሆኑ ግልፅ ነው። ህዝባዊ ዓላማችንን የተጋራን ጋር በመርህ የምናደርገው ትብብር እና አንድነት የአረመኔውን አገዛዝ እድሜ ለማሳጠር ትልቅ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው።
ይህንን ተከትሎ ባቀረብነው ወገናዊ ጥሪ በርካታ የአገዛዙ አገልጋይ የነበረ ምሊሻ፣ አድማ ብተና እና የመከላከያ ኃይል የወገንን ኃይል እየተቀላቀለ ይገኛል።
ስለሆነም ዛሬም አገዛዙን በማገልገል ላይ ለምትገኙ የምሊሻ፣ የአድማ ብተና፣ የመደበኛ ፖሊስ፣ መከላከያ እና በሌሎች የአገዛዙ ታጣቂ አደረጃጀቶች ውስጥ ላላችሁ ተመሳሳይ ጥሪወችን እናስተላልፋለን።
ይህንን ጥሪ ያስተላለፈው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ስራ አመራር በጉዳዩ ላይ በዝርዝር ተወያይቶ ጥሪዉን በመቀበል ወገናቸውን ለመካስ ለሚፈልጉ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት እና የካድሬ መዋቅር የምህረት አዋጅ አውጇል።
ለ) የምህረት አዋጁ የተላለፈላቸው የአገዛዙ መዋቅር አካላት:-
፩) በየደረጃው የሚገኙ የብልፅግና አመራር አባላት
፪) ምሊሻ፣ ሰላም አስከባሪ እና በሌላም ስያሜ ብልፅግና ያደራጃቸው ታጣቂወች
፫) የክልል አድማ ብተና እና መደበኛ ፖሊስ አባላት
፬) በሀገር መከላከያ ሰራዊት ስም በየቀጠናው የተሰማሩ እግረኞች እና የአገዛዙ መኮንኖች
ሐ) የምህረት አዋጁን ማውጣት ያስፈለገበት ምክንያት
ሶስት ዓመታትን ሊደፍን ጥቂት ጊዜ በቀረው የጦርነት ሂደት በግልፅ መገንዘብ እንደሚቻለው የብልፅግና መዋቅር በአማራ ህዝብ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ድቀት ላይ ስልጣኑን ከማራዘም ያለፈ ለአማራ ህዝብ የሚጠቅም አንድም አጀንዳ የሌለው በመሆኑ የአማራ ህዝብ እንደ ህዝብ በተለያዬ ጎራ የተሰለፍን የአማራ ልጆችም እንደ የአንድ እናት ልጆች በመቀናጀት የህዝባችንን ህልዉና ማስጠበቅ ከእኛ የሚጠበቅ ተግባር ነው።
በመሆኑም:-
፩) ለአማራ ህዝብ ሁለንተናዊ መብት እና ነፃነት እንጅ ለአብይ አህመድ ወንበር መፅናት የሚወድቅ የአማራ ወጣት መኖር ስለሌለበት፤
፪) ህዝባችንን በጅምላ ለሚጨፈጭፍ አገዛዝ በማገልገል የዘቀጠ ታሪክ ውስጥ ራስን ከማግኘት ይልቅ ለነፃነቱ የሚዋደቅን ኃይል በመቀላቀል ደማቅ ታሪክ መፃፍ ታሪክ የጣለብን ግዴታ በመሆኑ፤
፫) ህዝብን ታግሎ ያሸነፈ አገዛዝ እንደሌለው ሁሉ አብይ አህመድም የአማራን ህዝብ ማሸነፍ ስለማይችል እና በተሸናፊነት ለሚያጠናቅቀው ብልፅግና በመላላክ እና በራስ ወገን ላይ በመተኮስ የታሪክ፣ የህሊና እና የፍትህ ተጠያቂነትን ከማስተናገድ ለመዳን ሲባል፤
፬) አገዛዙን በጋራ ታግለን በማሸነፍ ለህዝባችን ሰላም ማምጣት የትውልዱ ግዴታ በመሆኑ፤
፭) እንዲሁም የምንታገለው ለአማራ ህዝብ ህልውናና መዳን እንደመሆኑ መጠን የፋኖ ትግልም የአማራ ህዝብ ትግል ስለሆነ በሁሉም ጎራ ላሉ አማራዊ ወንድሞች ጥሪ ማድረግ እና ማታገል የድርጅታችን ተልዕኮ በመሆኑ፤
ይህንን የምህረት አዋጅ በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ስራ አመራር ውሳኔ መሰረት ለህዝብ ይፋ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
መ) የምህረት አዋጁ አተገባበር
፩) የምህረት አዋጁ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ካላይ በተራ ቁጥር "ለ" ስር የተዘረዘሩት የምሊሻ፣ አድማ ብተና፣ መከላከያ እና ሌሎች የታጠቁ የብልፅግና ኃይሎች እንዲሁም በየደረጃው ያሉ አመራሮች በየአካባቢያቸው ላለው የድርጅታችን መዋቅር እና ለዚህ ጉዳይ በተቋቋመው ግዜያዊ ግብረ ኃይል በአካል ቀርበው ሪፖርት ያደርጋሉ።
፪) ምህረት ጠይቀው ወገናቸውን ለመካስ የሚመጡ ግለሰቦች የአካል ደህንነት ዋስትና ይሰጣቸዋል። በተዘጋጀላቸው ማረፊያ የተሃድሶ ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋል።
፫) ለትግል አገልግሎት ከሚዉል የጦር መሳሪያን ጨምሮ ማንኛውም የምህረት ጠያቂወች ንብረት በባለቤቶች እጅ ይቆያል።
፬) ምህረት የተደረገላቸው ግለሰቦች ድርጅቱ ባዘጋጀው ፎርም መሠረት ለአማራ ህዝብ ነፃነት ሊሰሩ ካልተቻለም ከጠላት ወገን ላይሰለፉ ቃለ-መሃላ ይፈፅማሉ።
፭) አቅሙ እና ፍላጎቱ ያላቸው የምህረት ተጠቃሚወች የወገንን ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር ተቀላቅለው ለህልዉና ተጋድሎው የበኩላቸውን ድርሻ ይወጡ ዘንድ በሌላ ማናቸውም ለህዝብ ጠቃሚ በሚሆኑ ተልዕኮወች ላይ ይሰማሩ ዘንድ ድርጅቱ ሁኔታወችን ያመቻቻል።
፮) ይህ የምህረት አዋጅ ከዛሬ የካቲት 04 ቀ 2018 ዓ.ም ላሉት ተከታታይ 15(አስራ አምስት ቀናት) ብቻ ተፈፃሚ ይሆናል።
ሠ) የምህረት አዋጁን በማስፈፀም የሰራዊታችን እና የድርጅታችን አመራር ግዴታ
፩) የምህረት አዋጁን አፈፃፀም ለመከታተል በማዕከል የተቋቋመው ግብረ ኃይል የመመሪያዉን አተገባበር ይከታተላል፤ መረጃወችን ይሰጣል፤ መፍትሔ ያስቀምጣል።
፪) የድርጅቱ መዋቅር አመራር እና ሰራዊቱ ለምህረት ጠያቂወቹ የአካል ዋስትና መስጠትን ጨምሮ በእንክብካቤ በማስተናገድ በፍፁም ጨዋነት አዋጁን ይተገብራል።
፫)በአፈፃፀም ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ወዲያውኑ ለግብረኃይይሉ ያሳውቃል፣ የተሰጠዉን የመፍትሔ አቅጣጫ ይተገብራል።
፬ በግል ቂም ቁርሾ ወይም በሌላ ግላዊ እና ቡድናዊ ፍላጎቶች ምክንያት ከዚህ አዋጅ በተቃረነ መንገድ በማንኛውም ምህረት ጠያቂ ላይ አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ማድረስ ወይም ንብረት መቀማት ፍፁም የተከለከለ ተግባር ነው።
፭) የዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌወችን እና መርሆወችን እንዲሁም ዓለም አቀፍ የጦር ህግጋትን የተከተለ አሰራር ይተገበራል።
፮) ይህንን አዋጅ ጥሶ የተገኘ ማንኛውም የድርጅቱ አመራር እና አባል ወይም ሌላ አካል ከባድ ቅጣት ይጠብቀዋል።
ረ) የሕዝቡ፣ የሀገር ሽማግሌወች እና የኃይማኖት አባቶች ሚና
በየቀጠናው ያለው ህዝብ፣ የሀገር ሽማግሌወች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ ምሁራን እና ሌሎች ተሰሚነት ያላቸው ግለሰቦች በጠላት የፀጥታ እና የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ያሉ ግለሰቦች በዚህ አዋጅ መሰረት አፈሙዛቸውን ወደ ዋናው ጠላት እንዲያዞሩ ካልሆነም ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲኖሩ እና የአማራው ኃይል ፍፁም ህብረት እንዲኖር የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ይጠበቃል።
በመጨረሻም የአማራ ልጆች በጋራ ተባብረን ህዝባችንን ሊያጠፋ የተነሳውን ጠላት እናስወግድ ዘንድ አንድነት እና ህብረት ያስፈልገናል እና ወደ አማራ የምንተኩሰው ጥይት እንዳይኖር እና አንድ ጠላት ላይ ብቻ አነጣጥረን እናሸንፍ ዘንድ ኑ እንላለን።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ
Telegram:https://t.me/AmharaFanoGonderCommand
Fb1:https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0s54YscqQoboSLWxuNoBgMaPZBU3vbMYioaCakfTfQtR15V3iTWXNh6hkZ7DEcAtsl&id=61577361273153&mibextid=ZbWKwL
Fb2:https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid027yTfCyCggt6GcqSo2mx69LNvT1s67h5m8TumUBCanrzXobwAx2Vx3dY5pkwtboVnl&id=61558523728158&mibextid=ZbWKwL
Fb3: https://www.facebook.com/share/p/1C3PvZqYiZ/
5 807
+1
ኑ ጠላትን በጋራ ታግለን የአማራን ህዝብ ሕልውና እናረጋግጥ!
የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተላለፈ የምህረት አዋጅ
ሀ) መግቢያ:
አረመኔው የብልፅግና አገዛዝ የአማራን ህዝብ ህልውና አደጋ ላይ ለመጣል የጀመረውን ጦርነት ለማሳካት ይችል ዘንድ በርካታ አረመኔያዊ ተግባራትን ሲፈፅም መቆየቱ ይታወቃል።
የአማራን ህዝብ ያለ ልዩነት ለመፍጀት አቅሙ የፈቀደውን ሁሉ እየተጠቀመ ያለው አገዛዝ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ጂኦ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎቶችን በማገልገል በፈጠረው የማውደም አቅም ተማምኖ በከፈተው ጦርነት ራሱ እየተለበለበበት ይገኛል።
የአማራን ህዝብ ለማጥፋት ከሚጠቀምባቸው ስልቶች መካከል ነባሩን የብአዴን መዋቅር በመጠቀም ባሰባሰበው የምሊሻ እና የአድማ ብተና ኃይል ከፋኖ ጋር እንዲዋጋ እና ህዝባችን በሁለት ጎራ ተሰልፎ እንዲጠፋፋ የሞከረበት መንገድ አንደኛው ነው።
በአንድ ህዝብ መካከል እና በኢትዮጵያዊያን መካከል እንዲሁም ቀጠናዊ ጦርነቶችን በማስነሳት ለአፍሪካ ቀንድ የቀውስ ዘበኛ የሆነውን አገዛዝ በወንድማማችነት እና በጥበብ በማስወገድ የጋራ መንግስት መመስረት እንደሚገባን በተደጋጋሚ ጥሪወች ስናስተላልፍ የቆዬን መሆኑ ይታወቃል።
በተለይም ከሰሞኑ ደግሞ ጠላት በአንድ በኩል የህዝብ መገናኛ መስመሮችን በመዝጋት ንፁሃን ላይ ጭፍጨፋ እያደረገ በሌላ በኩል ደግሞ ብሔራዊ አጀንዳ ያለው እና ለሀገር ብሔራዊ ተልዕኮ የተሰለፈ በመምሰል የሚያደርገውን የማደናገሪያ ስልት በንቃት በመከታተል የፋኖ ሰራዊት በወሰዳቸው እርምጃወች ወራሪው የብልፅግና ኃይል ከፍተኛ ትርምስ ውስጥ ገብቷል።
5 807
ከላይ የቀጠለ...
የድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ መወለድ ያስገኘው የአንድነት መንፈስ ለተገኙ ወታደራዊ ድሎች ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። የድላችን ምስጢር ያለው አንድነታችን ላይ መሆኑም በተግባር ተረጋግጧል። ድርጅታዊ አንድነታችንን በጠበቀ መልኩ ከኢትዮጵያዊያን እና ከቀጠናው ኃይሎች ጋር የሚደረግ ትብብር አገዛዙን ሙሉ በሙሉ ለማስወገድ ወሳኝ ሂደት መሆኑ ግልፅ ነው። ህዝባዊ ዓላማችንን የተጋራን ጋር በመርህ የምናደርገው ትብብር እና አንድነት የአረመኔውን አገዛዝ እድሜ ለማሳጠር ትልቅ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው።
ይህንን ተከትሎ ባቀረብነው ወገናዊ ጥሪ በርካታ የአገዛዙ አገልጋይ የነበረ ምሊሻ፣ አድማ ብተና እና የመከላከያ ኃይል የወገንን ኃይል እየተቀላቀለ ይገኛል።
ስለሆነም ዛሬም አገዛዙን በማገልገል ላይ ለምትገኙ የምሊሻ፣ የአድማ ብተና፣ የመደበኛ ፖሊስ፣ መከላከያ እና በሌሎች የአገዛዙ ታጣቂ አደረጃጀቶች ውስጥ ላላችሁ ተመሳሳይ ጥሪወችን እናስተላልፋለን።
ይህንን ጥሪ ያስተላለፈው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ስራ አመራር በጉዳዩ ላይ በዝርዝር ተወያይቶ ጥሪዉን በመቀበል ወገናቸውን ለመካስ ለሚፈልጉ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት እና የካድሬ መዋቅር የምህረት አዋጅ አውጇል።
ለ) የምህረት አዋጁ የተላለፈላቸው የአገዛዙ መዋቅር አካላት:-
፩) በየደረጃው የሚገኙ የብልፅግና አመራር አባላት
፪) ምሊሻ፣ ሰላም አስከባሪ እና በሌላም ስያሜ ብልፅግና ያደራጃቸው ታጣቂወች
፫) የክልል አድማ ብተና እና መደበኛ ፖሊስ አባላት
፬) በሀገር መከላከያ ሰራዊት ስም በየቀጠናው የተሰማሩ እግረኞች እና የአገዛዙ መኮንኖች
ሐ) የምህረት አዋጁን ማውጣት ያስፈለገበት ምክንያት
ሶስት ዓመታትን ሊደፍን ጥቂት ጊዜ በቀረው የጦርነት ሂደት በግልፅ መገንዘብ እንደሚቻለው የብልፅግና መዋቅር በአማራ ህዝብ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ድቀት ላይ ስልጣኑን ከማራዘም ያለፈ ለአማራ ህዝብ የሚጠቅም አንድም አጀንዳ የሌለው በመሆኑ የአማራ ህዝብ እንደ ህዝብ በተለያዬ ጎራ የተሰለፍን የአማራ ልጆችም እንደ የአንድ እናት ልጆች በመቀናጀት የህዝባችንን ህልዉና ማስጠበቅ ከእኛ የሚጠበቅ ተግባር ነው።
በመሆኑም:-
፩) ለአማራ ህዝብ ሁለንተናዊ መብት እና ነፃነት እንጅ ለአብይ አህመድ ወንበር መፅናት የሚወድቅ የአማራ ወጣት መኖር ስለሌለበት፤
፪) ህዝባችንን በጅምላ ለሚጨፈጭፍ አገዛዝ በማገልገል የዘቀጠ ታሪክ ውስጥ ራስን ከማግኘት ይልቅ ለነፃነቱ የሚዋደቅን ኃይል በመቀላቀል ደማቅ ታሪክ መፃፍ ታሪክ የጣለብን ግዴታ በመሆኑ፤
፫) ህዝብን ታግሎ ያሸነፈ አገዛዝ እንደሌለው ሁሉ አብይ አህመድም የአማራን ህዝብ ማሸነፍ ስለማይችል እና በተሸናፊነት ለሚያጠናቅቀው ብልፅግና በመላላክ እና በራስ ወገን ላይ በመተኮስ የታሪክ፣ የህሊና እና የፍትህ ተጠያቂነትን ከማስተናገድ ለመዳን ሲባል፤
፬) አገዛዙን በጋራ ታግለን በማሸነፍ ለህዝባችን ሰላም ማምጣት የትውልዱ ግዴታ በመሆኑ፤
፭) እንዲሁም የምንታገለው ለአማራ ህዝብ ህልውናና መዳን እንደመሆኑ መጠን የፋኖ ትግልም የአማራ ህዝብ ትግል ስለሆነ በሁሉም ጎራ ላሉ አማራዊ ወንድሞች ጥሪ ማድረግ እና ማታገል የድርጅታችን ተልዕኮ በመሆኑ፤
ይህንን የምህረት አዋጅ በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ስራ አመራር ውሳኔ መሰረት ለህዝብ ይፋ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
መ) የምህረት አዋጁ አተገባበር
፩) የምህረት አዋጁ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ካላይ በተራ ቁጥር "ለ" ስር የተዘረዘሩት የምሊሻ፣ አድማ ብተና፣ መከላከያ እና ሌሎች የታጠቁ የብልፅግና ኃይሎች እንዲሁም በየደረጃው ያሉ አመራሮች በየአካባቢያቸው ላለው የድርጅታችን መዋቅር እና ለዚህ ጉዳይ በተቋቋመው ግዜያዊ ግብረ ኃይል በአካል ቀርበው ሪፖርት ያደርጋሉ።
፪) ምህረት ጠይቀው ወገናቸውን ለመካስ የሚመጡ ግለሰቦች የአካል ደህንነት ዋስትና ይሰጣቸዋል። በተዘጋጀላቸው ማረፊያ የተሃድሶ ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋል።
፫) ለትግል አገልግሎት ከሚዉል የጦር መሳሪያን ጨምሮ ማንኛውም የምህረት ጠያቂወች ንብረት በባለቤቶች እጅ ይቆያል።
፬) ምህረት የተደረገላቸው ግለሰቦች ድርጅቱ ባዘጋጀው ፎርም መሠረት ለአማራ ህዝብ ነፃነት ሊሰሩ ካልተቻለም ከጠላት ወገን ላይሰለፉ ቃለ-መሃላ ይፈፅማሉ።
፭) አቅሙ እና ፍላጎቱ ያላቸው የምህረት ተጠቃሚወች የወገንን ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር ተቀላቅለው ለህልዉና ተጋድሎው የበኩላቸውን ድርሻ ይወጡ ዘንድ በሌላ ማናቸውም ለህዝብ ጠቃሚ በሚሆኑ ተልዕኮወች ላይ ይሰማሩ ዘንድ ድርጅቱ ሁኔታወችን ያመቻቻል።
፮) ይህ የምህረት አዋጅ ከዛሬ የካቲት 04 ቀ 2018 ዓ.ም ላሉት ተከታታይ 15(አስራ አምስት ቀናት) ብቻ ተፈፃሚ ይሆናል።
ሠ) የምህረት አዋጁን በማስፈፀም የሰራዊታችን እና የድርጅታችን አመራር ግዴታ
፩) የምህረት አዋጁን አፈፃፀም ለመከታተል በማዕከል የተቋቋመው ግብረ ኃይል የመመሪያዉን አተገባበር ይከታተላል፤ መረጃወችን ይሰጣል፤ መፍትሔ ያስቀምጣል።
፪) የድርጅቱ መዋቅር አመራር እና ሰራዊቱ ለምህረት ጠያቂወቹ የአካል ዋስትና መስጠትን ጨምሮ በእንክብካቤ በማስተናገድ በፍፁም ጨዋነት አዋጁን ይተገብራል።
፫)በአፈፃፀም ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ወዲያውኑ ለግብረኃይይሉ ያሳውቃል፣ የተሰጠዉን የመፍትሔ አቅጣጫ ይተገብራል።
፬ በግል ቂም ቁርሾ ወይም በሌላ ግላዊ እና ቡድናዊ ፍላጎቶች ምክንያት ከዚህ አዋጅ በተቃረነ መንገድ በማንኛውም ምህረት ጠያቂ ላይ አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ማድረስ ወይም ንብረት መቀማት ፍፁም የተከለከለ ተግባር ነው።
፭) የዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌወችን እና መርሆወችን እንዲሁም ዓለም አቀፍ የጦር ህግጋትን የተከተለ አሰራር ይተገበራል።
፮) ይህንን አዋጅ ጥሶ የተገኘ ማንኛውም የድርጅቱ አመራር እና አባል ወይም ሌላ አካል ከባድ ቅጣት ይጠብቀዋል።
ረ) የሕዝቡ፣ የሀገር ሽማግሌወች እና የኃይማኖት አባቶች ሚና
በየቀጠናው ያለው ህዝብ፣ የሀገር ሽማግሌወች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ ምሁራን እና ሌሎች ተሰሚነት ያላቸው ግለሰቦች በጠላት የፀጥታ እና የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ያሉ ግለሰቦች በዚህ አዋጅ መሰረት አፈሙዛቸውን ወደ ዋናው ጠላት እንዲያዞሩ ካልሆነም ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲኖሩ እና የአማራው ኃይል ፍፁም ህብረት እንዲኖር የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ይጠበቃል።
በመጨረሻም የአማራ ልጆች በጋራ ተባብረን ህዝባችንን ሊያጠፋ የተነሳውን ጠላት እናስወግድ ዘንድ አንድነት እና ህብረት ያስፈልገናል እና ወደ አማራ የምንተኩሰው ጥይት እንዳይኖር እና አንድ ጠላት ላይ ብቻ አነጣጥረን እናሸንፍ ዘንድ ኑ እንላለን።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ
Telegram:https://t.me/AmharaFanoGonderCommand
5 807
ከላይ የቀጠለ...
ከዚህ በተጨማሪ ለሚኒሻ ደመወዝና ለመከላከያ ድጎማ የሚል ድርብርብ ወጭ ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተዳምሮ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ ሲያስተናግዱ የኖሩ አካባቢዎች ናቸው። ይህ ህጋዊና ህገወጥ ሌቦች ሲመዘብሩት የኖረ ማህበረሰብ፤ እንደ ገጠሩ ማህበረሰብ እና ፋኖ እንደተቆቆጣጠራቸው ከተሞች ነፃነቱን አግኝቶ የሚኖርበትን ቀን ሲናፍቅ የቆየ ማህበረሰብ ነው።
በመሆኑም ወደ ከተማው የሚንቀሳቀስ የፋኖ ኃይል በሙሉ የሚያደርገው እንቅስቃሴ፤ የተጠና እና የማህበረሰብ ልጅነትን ግምት ውስጥ ያስገባ ሊሆን ግድ ይላል። በመሆኑም ከተሞችን በምንይዝበት ወቅት፤ መተግበር ያለባቸው መመሪያዎችና ጥሪዎች እንደሚከተለው ይቀርባል፦
1/ እነደሚታወቀው ቀጠናው ከ2008 ዓ.ም ሃምሌ ወር ጀምሮ ለተከታታይ አስር ዓመታት ያለ ዕረፍት በጦርነት እየወደመ የሚገኝ አካባቢ ነው። በመሆኑም ለፋኖ መገልገያ የሚውል የስርዓቱ ሐብት ካለ በተቋምና በበላይ አመራር ይሁንታ መሰረት መጠቀም የማይከለከል ሆኖ፤ ከዚህ በዘለለ ተገቢ ባልሆነ ሁኔታ በእሳት ማቃጠል፣ማውደምና መዝረፍ ግን ፍፁም ለመንግስትነት ከሚታገል ኃይል የማይጠበቅ ተግባር መሆኑ ታውቆ፤ አንድም ንብረት በቃጠሎና በዘረፋ እንዳይወድም።
2/ በግል ቂም ተነሳስቶ ያለ ተቋም እና የበላይ ኃላፊ እውቅና፤ ማህበረሰብን አስሮ ማንገላታት ፍፁም የተከለከለ ነው። የተለየ የግል ጉዳይ ያለው አባል ካለ እንደማንኛውም ማህበረሰብ ክስ መስርቶ አስፈርዶ በተቋሙ ማስቀጣት ይቻላል።
3/ ተቋምና የበላይ አካል በማያውቀው መልኩ፤ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰብ መርሐግብር (አስገድዶም ሆነ በፈቃደኝነትም ቢሆን) ገቢ መሰብሰብ ፍፁም የተከለከለ ነው። አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘና ከታመነበት፤ አስቻይነቱ በተቋም ተገምግሞ ህጋዊነቱን ጠብቆ መፈፀም ይቻላል።
4/ ለግዳጅ ወይም ለሌላ የግል ስራ በተቋምና በበላይ ኃላፊ የተፈቀደለት አካል ካልሆነ በስተቀር፤ ከተማ በማንኛውም ሰዓት ገብቶ መዝረክረክ ፍፁም የተከለከለ ነው። እንደ አስፈላጊነቱ ከከተማ ቅርብ እርቀት ተንቀሳቃሽ ካምፕ አዘጋጅቶ መቀመጥ ይቻላል።
5/ ሥርዓቱ የለቀቃቸው ከተሞች ላይ የድሮን ጥቃት ሊኖር ስለሚችል፤ ማህበረሰቡም አባሉም ባለመሰባሰብ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ።
6/ለሥርዓቱ አገልጋዮች በሙሉ ለሚሊሻ፣ ለአድማ ብተና፣ ለመከላከያ ሰራዊት አባላትና በየደረጃው ላላችሁ የሲቪል አመራሮች በሙሉ፤ አስኪ በቃን ተገዳድለናል፤ በየቀኑ ዓላማ ቢስ ሞት ሞታችኋል፤ በእርግጠኝነት ለመማር ዝግጁ ከሆናችሁ እስካሁን በበቂ ሁኔታ ተምራችኋል፤ በመሆኑም ከእንግዲህ ወዲህ መገዳደል አቁመን በጋራ እንድንታገል የተለመደ ጥሪያችን እያቀረብን፤ መታገል ለሚፈልግ በፍላጎቱ እንዲታገል ለማይፈልግ ደግሞ መደበኛ ኑሮውን እንዲኖር እንደምንፈቅድ ማሳስብ እንወዳለን።
7/ለማህበረሰቡ በሙሉ በፋኖ ስም ለሚንቀሳቀስ አባላችን በሙሉ የተለመደውን ትብብር ማድረግ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ አላስፈላጊ የሆነ ድርጊት የሚፈፅም አባል ሲኖር ግን አስፈላጊውን ጥቆማ በመስጠት እንድትተባበሩ እና ወንጀልን በጋራ እንድንከላከል ማሳሰብ እንወዳለን።
8/ከበላይ ዕዝ ጋር የጋራ ኮሚቴ በማዋቀር ስራችን የጋራ በማድረግ የምንስራ ይሆናል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት እዝ
የካቲት 02 ቀን 2018 ዓ.ም
ጎንደር-አማራ- ኢትዮጵያ
5 807
+1
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የተሰጠ መግለጫ፦
ለሁለት ዓመት ከሰባት ወር ገደማ በአማራ ፋኖ ብርቱ ክንድ ሲቀጠቀጥ የከረመኔው አረመኔ ስርዓት፤ የፋኖን ሀይል ‹‹አዳክሜያለው›› እያለ የከሰረ ፕሮፓጋንዳ ሲሰራ ቢከርምም፤ ሰሞኑን በሁሉም የአማራ ቀጠናዎች በከፍተኛ ሁኔታ እየተመታ ይገኛል።
ነጣጥለህ ምታው በሚል መርህ ሰሞኑን በሸዋ ወንድሞቻችን ላይ የተደራጀና የተጠናከረ ውጊያ ከፍቶ ንጹሀንን ዒላማ ያደረገ ጭፍጨፋ ቢፈጽምም፤ አይበገሬዎቹ የሸዋ አናብስቶች የስርዓቱን ኃይል እንደ ዘላን ላም ማርከው እየነዱ አሳይተውናል።
በተመሳሳይ መልኩ በጎንደር፣ በጎጃም እና በወሎ ቤተ አማራም ከፍተኛ መነቃቃትና ድርብርብ ጀብድ እየተሰራ የአረመኔው ስርዓት ዘቦች እየተገረፉ ይገኛሉ። ከዚህ በተጨማሪም፤ የፋኖ ብርቱ ክንድ የበረታበት ሥርዓት፤ ሰሞኑን በጎንደር ጠቅላይ ግዛት በሚደረገው ውጊያ፤ አንዳንድ ከተሞችን በውጊያ የተወሰኑትን ደግሞ ያለ ውጊያ እየለቀቃቸው ይገኛል።
ለምን ከተሞችን እየለቀቃቸው እንደሚወጣ ግልጽ የሆነ ነገር ባይኖርም፤ የተለያዩ መላምቶች ግን እየተሰጡ ይገኛሉ። የስርዓቱ ኃይል እየለቀቀ የሚወጣበት ምክንያት ተደርጎ እየተነገረ ያለው፤ በዋናነት የህውሐትና የሻዕቢያ ጥምር ሐኃል በሰሜን ምዕራብ አማራ በኩል ተከዜን ተሻግረው ለወረራ ሊመጡ ነው የሚል እንደሆነ መረጃዎች ያመላክታሉ።
በምንም ይሁን በምን፤ እየተለቀቁ ያሉ ከተሞች እጣ ፋንታ ጉዳይ በአማራ ፋኖ እጅ ሆኗል። እነዚህ አሁን የስርዓቱ ኃይል እየለቀቃቸው ያሉ ከተሞች ስርዓቱ ይዞ በሚያስተዳድርበት ወቅት ከፍተኛ የሆነ ስርቆት፣ ዘረፋ፣ ግድያ፣ አስገድዶ መደፈር፣ ሙስና እና ሌሎች ብልሹ አሰራሮች በስርዓቱ ጋሻ ጃግረዎች ሲፈፀምባቸው የከረሙ ከተሞች ናቸው።
5 807
#ጎንደር#ደንቢያ ቀጠና ውጊው ቀጥሏል።
የአፋብን ጎጠግ ዕዝ በጌምድር ክ/ጦር አይሸሽም ብርጌድ ደንቢያ ሰቀልት(መቋሙያ ማርያም) ከንጋት 12:00 ጀምሮ ከፍተኛ ትንቅንቅ እያደረገ ነው።
ቀደም ሲል ባጋራሁት መረጃ መሰረት የአይሸሽም ብርጌድ ተወርዋሪ ሐይል ጣቁሳ ምድር ኦፕሬሽን መስራቱን መዘገባችን ይታወሳል። የዚሁ ብርጋድ አካል ሌሎች አሐዶች ደግሞ ደንቢያ ሰቀልት መቋሚያ ማርያም ታሪክ እየሰሩ ነው።
ከንጋት 12:00 ሰዓት ጀምረው ባደረጉት ትንቅንቅ ከፍተኛ ምት ያስተናገደው ሐይል መውጫ አጥቶ እየተወቀጠ ሲሆን የገባው ሐይሕ መቋቋም ስላልቻለ ተጨማሪ ሐይል ከሰንበት ደብርና ከጎንደር ካንፖች እየተላከለት ይገኛል።
አናብስቶች እሳክሁኑ ሰዓት እያጫወቱት ነው።
ድል ለአማራ ፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!
የአፋብን ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
5 807
#መረጃ
የካቲት 01/2018 ዓ/ም
ምሽግ ተሰብሯል ጠላት ነቅሎ ወጧል።
ጣቁሳ ወረዳ ጨውድባ ከተማ ውስጥ መሸጎ የነበረ የጠላት ጥምር ጦር በከፍተኛ ምት ተመቶ፤ ምሽጉ ተሰብሮ፤ ከተማውን ለቆ ወጧል።
የአፋብን ጎጠግ ዕዝ በጌምድር ክ/ጦር አይሸሽም ብርጌ አናብስቶች ሌሊት በሰሩት ኦፕሬሽን የጠላት ጦር ክፉኛ ተመቶ ሲፈረጥጥ አድሯል።
ተወርዋሪዎቹ የአይሸሽም ብርጌድ አባላት በክ/ጦሩ ዋና አዛዥ አርበኛ ክንዱ ግርማ እየተመሩ በሰሩት የተሳካ ኦፕሬሽን ድንብርብሩ የወጣው ጥምር ሐይል ጓዙን ሳይሸክፍ እያዝረበረበው ወደ ጭልጋ ወረዳ ጫንድባ ከተማ ፈርጥጣል።
ቀጠና የማይገድባቸው የበጌምድር አካል የሆኑት አይሸሽም ብርጌዱች በሰቀልት(አይንባ)፣በአርመጭሆ፣በመተማ፣በቋራ፤በጣቁሳ እየተዘዋወሩ የጠላትን ቅስም የሚሰባብሩ ሲሆን በዛሬው እለትም ይህ ፈርጣማ እጃቸው ጨውድባ ላይ አርፏል።
በኦፕሬሽኑ የተደረሰውን ሰባዊና ቁሳዊ ኪሳራ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
ድል ለአማራ ህዝብ!
ድል ለአማራ ፋኖ!
የአፋብን ጎጠግ ዕዝ ግንኙነት መምሪያ!
Fb1:https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0s54YscqQoboSLWxuNoBgMaPZBU3vbMYioaCakfTfQtR15V3iTWXNh6hkZ7DEcAtsl&id=61577361273153&mibextid=ZbWKwL
Fb2:https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid027yTfCyCggt6GcqSo2mx69LNvT1s67h5m8TumUBCanrzXobwAx2Vx3dY5pkwtboVnl&id=61558523728158&mibextid=ZbWKwL
Fb3: https://www.facebook.com/share/p/1C3PvZqYiZ/
5 807
#መረጃ
የካቲት 01/2018 ዓ/ም
ምሽግ ተሰብሯል ጠላት ነቅሎ ወጧል።
ጣቁሳ ወረዳ ጨውድባ ከተማ ውስጥ መሸጎ የነበረ የጠላት ጥምር ጦር በከፍተኛ ምት ተመቶ፤ ምሽጉ ተሰብሮ፤ ከተማውን ለቆ ወጧል።
የአፋብን ጎጠግ ዕዝ በጌምድር ክ/ጦር አይሸሽም ብርጌ አናብስቶች ሌሊት በሰሩት ኦፕሬሽን የጠላት ጦር ክፉኛ ተመቶ ሲፈረጥጥ አድሯል።
ተወርዋሪዎቹ የአይሸሽም ብርጌድ አባላት በክ/ጦሩ ዋና አዛዥ አርበኛ ክንዱ ግርማ እየተመሩ በሰሩት የተሳካ ኦፕሬሽን ድንብርብሩ የወጣው ጥምር ሐይል ጓዙን ሳይሸክፍ እያዝረበረበው ወደ ጭልጋ ወረዳ ጫንድባ ከተማ ፈርጥጣል።
ቀጠና የማይገድባቸው የበጌምድር አካል የሆኑት አይሸሽም ብርጌዱች በሰቀልት(አይንባ)፣በአርመጭሆ፣በመተማ፣በቋራ፤በጣቁሳ እየተዘዋወሩ የጠላትን ቅስም የሚሰባብሩ ሲሆን በዛሬው እለትም ይህ ፈርጣማ እጃቸው ጨውድባ ላይ አርፏል።
በኦፕሬሽኑ የተደረሰውን ሰባዊና ቁሳዊ ኪሳራ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
ድል ለአማራ ህዝብ!
ድል ለአማራ ፋኖ!
የአፋብን ጎጠግ ዕዝ ግንኙነት መምሪያ!
Fb1:https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0s54YscqQoboSLWxuNoBgMaPZBU3vbMYioaCakfTfQtR15V3iTWXNh6hkZ7DEcAtsl&id=61577361273153&mibextid=ZbWKwL
Fb2:https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid027yTfCyCggt6GcqSo2mx69LNvT1s67h5m8TumUBCanrzXobwAx2Vx3dY5pkwtboVnl&id=61558523728158&mibextid=ZbWKwL
Fb3: https://www.facebook.com/share/p/1C3PvZqYiZ/
5 807
#መረጃ
#Update
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጣቁሳ ወረዳ ጨውድባ ከተማ ላይ ከሌሊቱ 5:30 የተጀመረው ኦፕሬሽን አድማሱን አስፍቶ ወደ ጭልጋ ወረዳ ጫንድባ ከተማ ደርሷል።
በአፋብን ጎጠግ ዕዝ በጌምድር ክ/ጦር እና በስርዓቱ ጥምር ጦር መካከል የሚደረገው ውጊያ እንደቀጠለ ሲሆን የስርዓቱ ሐይል ይዟቸው የነበሩ ቦታወችን እየለቀቀ እየፈረጠጠ ይገኛል።
የስርዓቱ ጥምር ጦር ሌሊት ላይ ጨውድባ በነበረው ኦፕሬሽን ፈርጥጦ ወደ ጨውድባ የመሸገ ቢሆንም የፋኖ ሐይል ይዞታውን በማስፋፊት ከበባ በመፈፀም እየለበለበው ይገኛል።
ውጊያውን በበጌምድር አናብስቶች በጥበብ እየተመራ ነው፤ሙሉ ዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን።
ጥር 27/2018 ዓ/ም
የአፋብን ጎጠግ ዕዝ ግንኙነት መምሪያ!
#መረጃ
#Update
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጣቁሳ ወረዳ ጨውድባ ከተማ ላይ ከሌሊቱ 5:30 የተጀመረው ኦፕሬሽን አድማሱን አስፍቶ ወደ ጭልጋ ወረዳ ጫንድባ ከተማ ደርሷል።
በአፋብን ጎጠግ ዕዝ በጌምድር ክ/ጦር እና በስርዓቱ ጥምር ጦር መካከል የሚደረገው ውጊያ እንደቀጠለ ሲሆን የስርዓቱ ሐይል ይዟቸው የነበሩ ቦታወችን እየለቀቀ እየፈረጠጠ ይገኛል።
የስርዓቱ ጥምር ጦር ሌሊት ላይ ጨውድባ በነበረው ኦፕሬሽን ፈርጥጦ ወደ ጨውድባ የመሸገ ቢሆንም የፋኖ ሐይል ይዞታውን በማስፋፊት ከበባ በመፈፀም እየለበለበው ይገኛል።
ውጊያውን በበጌምድር አናብስቶች በጥበብ እየተመራ ነው፤ሙሉ ዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን።
ጥር 27/2018 ዓ/ም
የአፋብን ጎጠግ ዕዝ ግንኙነት መምሪያ!
Fb1:https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0s54YscqQoboSLWxuNoBgMaPZBU3vbMYioaCakfTfQtR15V3iTWXNh6hkZ7DEcAtsl&id=61577361273153&mibextid=ZbWKwL
Fb2:https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid027yTfCyCggt6GcqSo2mx69LNvT1s67h5m8TumUBCanrzXobwAx2Vx3dY5pkwtboVnl&id=61558523728158&mibextid=ZbWKwL
Fb3: https://www.facebook.com/share/p/1C3PvZqYiZ/
5 807
+2
#መረጃ #ጎንደር
ጠላት በጨለማ ኦፕረሽን ምሽጉ ተሰበረ።
በጣቁሳ ወረዳ ጨውድባ ከተማ ከሌሊቱ አምስት ሰዓት ተኩል በተሰራ ኦፕሬሽ ከተመው ውስጥ መሽጎ የነበረ የጠላት ጥምር ጦር በከፍተኛ ሁኔታ ተመቷል።
በአፋብን ጎጠግ ዕዝ በጌምድር ክ/ጦር ናደው ብርጌድና ፋሲለደስ ብርጌድ ጥምር ጦር በተሰራ ኦፕሬሽ ጠላት ክፋኛ የተመታ ሲሆን ይዞት የነበረውን ምሽግ ሙሉ በሙሉ ተሰብሯል።
የወገንን ብትር መቋቋም ያቃተው አራዊት ለአምስት ደቂቃ የዘለቀ ውጊያ ማድረግ ያልቻለ ሲሆን በጨለማው እግሬ አውጭ ብሎ ሲፈረጥጥ አድሯል።
ኦፕሬሽኑ የተመራው በበጌምድር ክፍለጦር ዘመቻ መሪ አርበኛ ታድሎ ወርቄ እና በፋሲለደስ ብርጌድ ዋና አዛዥ ሻለቃ ደመቀና በናደው ብርጌድ ምክትል አዛዥ ሻለቃ ውባንተ መልኬ አማካኝነት ነው።
5 807
የቀጠለ.....
10. አርበኛ ነጋ ሆነልኝ------- የሰው ኃይል ኃላፊ
11.አርበኛ ሻለቃ ታዴ አለባቸው ------------ሎጅስቲክስና ኦርዲናስ ኃላፊ ሆኖ ተደራጂቷል።
ስለሆነም ማህበረሰባችንም ሆነ የትግል ጓዶቻችን ትግላችን የህልውና ነውና በግለሰቦች ፍላጎትና ጥቅም ላይ የተመሰረተ ባለመሆኑ የህዝባችንን ህልውና ሳናረጋግጥ እሚዝል ክንድ እሚደክም ጉልበት አልተላበስንምና ከእንደዚህ ቀደሙ በእልህና በቁጭት የምንታገል መሆኑን ጭምር መግለጽ እንፈልጋለን።
ድል ለአማራ ፋኖ!!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!!
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር!!!
ጥር 19 / 2018 ዓ.ም
5 807
#መረጃ
የመዋቅር ግንባታና ተሐድሶ ተጠናክሮ ቀጥሏል
ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ 206ኛ ከፉያለው ደሴ ኮር ዛሬም በጠራ የአደራጃጀት መዋቅር ብቅ ብሏል!!!
ትግል ቅብብሎሽ ነው። በትግል ውስጥ መሰዋት፣ ጉዳትና መክዳት ያሉና የነበሩ ናቸው። ሁሉም የየራሳቸው መገለጫ ቢኖራቸውም በኛ የትግል ምራፍ ደግሞ መክዳት ከማህበረሰባችን ወግና ባህል አንጻር ሲበዛ ሰላቶነት ፣ አቅመ ቢስነትና እና ወዶ ገብነት ነው።
ሰሞኑን የተራራው ራስ ጉና ክፍለ ጦር የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ የነበረ ለአገዛዙ ያደረ በመሆኑ ዳግም አደረጃጀቱን በማስተካከል በሚታወቅበት ጠላትን እረፍት የመንሳትና የህዝባችንን የህልውና አደጋ የመቀልበስ ትግል በአዲስ መንፈስ እራሱን አደራጅቷል።
ተራራው ራስ ጉና ክፍለ ጦር በግለሰቦች ስብዕናና ዝና ያልተመሰረተ በመሆኑ እንደ ከዚህ ቀደሙ አስደማሚ ግዳጅና ኦፕሬሽኖችን ለመስራት እራስን የማዘጋጀት ቅድመ ስራዎችን ጭምር አከናውኗል በመከወን ላይም ይገኛል ።
በመሆኑም ዛሬ ጥር 19/2018 ዓ.ም ክፍለ ጦሩ የሚከተለውን አዲስ አደረጃጀት አዋቅሮ ወደ ስራ ገብቷል።
1. አርበኛ ተመስገን አብርሀም------------ዋና ወታደራዊ አዛዥ
2. አርበኛ ያብባል ፈለቀ-------------ምክትል ወታደራዊ አዛዥ
3.አርበኛ ጌታቸው ሞገስ--------- ዋና ወታደራዊ ዘመቻ ኃላፊ
4.አርበኛ አያና ሆነ -------------ምክትል ወታደራዊ ዘመቻ ኃላፊ
5. አርበኛ ባይነሳኝ እንግዳው-------ፋይናስ ኃላፊ
6.አርበኛ ታደሰ አሰፋ-----------ምክትል ፋይናስ ኃላፊ
7. አርበኛ ባንቲደር እውነቱ ----------ቁጥር እና ኦዲት ኃላፊ
8.አርበኛ ጌትነት ስመኝ------------ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ
9.አርበኛ ገበየሁ አማረ--------ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
5 807
+1
#መረጃ ጎንደር
በአንድነቱ የተነሳሳው ሰራዊታችን ደፈጣውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
አፋብን ጎጠግ ዕዝ
ጥር 19/2018 ዓ/ም
በአፋብን ጎጠግ ዕዝ በጌምድር ክ/ጦር ናደው ብርጌድ የተሳከ ደፈጣ ፈፅሟል።
በማዕከላዊ ጎንደር ምዕራብ ደንቢያ ወረዳ ሁለት ቦታ ላይ የተሳካ ደፈጣ ተሰርቷል።
በጯሒትና ጎርጎራ መካከል በሚገኙ ሁለት የጠላት ካንምፖች መካከል ሰባት ዋርካ የሚባል ቦታና ከቆላድባና ጯሒት መካከል የመገኝ ፈንጃ የተባለ ቦታ ላይ በተሰራ ደፈጣ ከ20 በላይ ጥምር ጦር የተሸኘ ሲሆን ከ30 በላይ ቁስለኛ ታቅፎ ተመልሷል።
በወገን በኩል ታጋይ ታድጎኝ ደሴ የተባለ አባል ከምሽግ ምሽግ እየተረማመደ ብዙወችን ከረፈረፈ በኋላ እራሱን በራሱ በማጥፋት መሰዕዋትነት ከፍሏል።
ድል ለአፋብን ጎጠግ ዕዝ
ድል ለአመራ ህዝብ!
አፋብን ጎጠግ ዕዝ ህ/ግንኙነት ክፍል!
5 807
+1
#መረጃ # ጎንደር
የአፋብን ጎ/ጠ /ግ ዕዝ የአንበሳው ጋይት ክፍለ ጦር ክንዳለም ሻለቃ በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሷል።
ዛሬ ጥር 15/2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ እስከ 9:00 ሰዓት ከጥጥራ እስከ ዳሞት በእንቅስቃሴ ላይ ከነበረን የጠላት ኃይል ጋር ውጊያ ያደረገ ሲሆን፦
## 9 ሙት
## 15 ከባድና ቀላል ቁስለኛ
## 6 የነብሽ ወከፍ (ክላሽን ኮፕ) ከጠላት ማርኳል
በሌላኛው አውደ ውጊያ ከክምር ድንጋይ ወደ አጃ ሬሽን ጭኖ በእንቅስቃሴ ላይ የነበረ የብልጽግናው ወንበር አስጠባቂ ሚሊሻ፣መከላከያና ፖሊስ በተራራው ራስ ጉና ክፍለ ጦር አናብስቶች ውቅሮ መድሃኒያለም ላይ ከፍተኛ ሙትና ቁስል አስተናግዷል።
ጀግና እማያልቅበት ምድር በብዙ ፈተና ቢፈተንም አንገቱን ቀና የሚያደርጉ ልጆቹ እንዳሉ አስመስክሯል። ።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ግንኙነት መምሪያ!
5 807
#መረጃ ጎንደር
የደስታ መግለጫ ኦፕሬሽን ተሰራ።
ጣቁሳ ወረዳ ቻችና-አሉዋ ቀበሌ የጠላት ጥምር ጦር በከበባ ሲወቀጥ አድሯል።
በአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ በጌምድር ክ/ጦር ናደው ብርጌድ ተወርዋሪዎች ከበባ ውስጥ የገባው ሐይል ለጊዜው ቁጥሩን ያልታወቀ(ጨለማ ከመሆኑ አንፃር) ሐይል ከምሽጉ ውስጥ ጭቃ ሆኗል።
በአማራ ፋኖ አንድነት የተደሰቱት አናብስቶች የአንድነቱን የመጀመሪያ ጉዞ በድል "ሀ" ብለው ጀምረውታል።
ውጊያውን በበላይነት የመራው የናደው ብርጌድ ዘመቻ መሪ ወጣቱ ተወርዋሪ ነብር አርበኛ አወቀ የደስታ መግለጫ ዘመቻውን በብቃት መርቶታል።
ሙሉና ዝርዝር መረጃውን ይዘን እንመለሳለን።
5 807
+2
#መረጃ
አፋህድ ጎጠግ ዕዝ በደቡብ ጎንደርና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች የተሳካ ውጊያ አድርጓል።
በደቡብ ጎንደር የክንደ ነበልባሉ አርበኛ ከፉያለው ደሴ የእጅ ስራ የሆነው ግዙፉ ገብርዬ ክፍለ ጦር አጋጥ ሚካኤል ፣ፈረስ ሜዳ፣ ሚዳቂት እና ኤፍራታ ላይ በክፍለ ጦሩ ዋና ዘመቻ አዛዥ እና አባ ከንትር ሽፌ ብርጌድ ዋና ጦር አዛዥ ያለው ጥላሁን እና በክፍለ የጦሩ ምክትል ዘመቻ አዛዥ በአብራኩ ክፋይ ክንድ ሰው ከፌ አማካኝነት በጠላት ላይ ከፍተኛ ምት አርፎበታል። በነዚህ አውደ ውጊያዎች 13 የጠላት ጦር ወደ ማይቀረው ሲሸኝ 18 በላይ ቁስለኛ ሆነዋል።
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ከቆላድባ ከተማ ቅርብ እርቀት ጃንጓ ላይ በበጌምድር ክ/ጦር በናደው ብርጌድና በአይሸሽም ብርጌድ ጥምር ሐይል የጠላት ጥምር ጦር ተመቷል።
በዚህ ግንባር 5 ሚሊሻና 12 መከላከያ የሞተ ሲሆን ከ20 በላይ ቁስለኛ አስተናግዷል።
በተደረጉት ውጊያዎች የጠላት ጦር ወደ ነበረበት ተሰብስቦ እንዲቀመጥ የደረገ ሲሆን ቦታዎቹ በፋኖ ሐይል ቁጥጥር ውስጥ ይገኛሉ።
ድሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ድል ለአማራ ህዝብ!
አፋህድ ጎጠግ ዕዝ ግንኙነት መምሪያ!
