fa
Feedback
Ethiopian Educational Channel

Ethiopian Educational Channel

رفتن به کانال در Telegram

እንኳን ደና መጣችሁ በዚህ ቻናል ላይ የሚያገኙት 1. ትምህርታዊ መረጃ መስጠት 2.የሳይኮሎጂ አስተማሪ ምክሮችንና አነቃቂ ንግግሮች 3.መፃህፍቶች በpdf እና የእንግሊዝኛ ትምህርት ይለቀቃሉ! በዚህ ቻናል ሀይማኖታዊ እና ፓለቲካ ነክ አይለቀቅበትም ! የቴሌግራሙ ቻናል ሊንክ:👉https://t.me/EEC1227 Channel created by @BA1227

نمایش بیشتر
6 814
مشترکین
-424 ساعت
-157 روز
-3930 روز
آرشیو پست ها
🚨 #አስቸኳይ_ማስጠንቀቂያ!👇 🔥​ሰሞኑን በቴሌግራም ላይ እጅግ አደገኛ የሆነ የአካውንት ጠለፋ እና የማጭበርበር ድርጊት እየተፈጸመ ይገኛል። 🔥​በጣም ፀያፍ የሆኑ ምስሎችን እና ቪዲዮዎችን እንደ ሽፋን በመጠቀም፣ ከስራቸው ሊንክ (Link) ያያይዛሉ።ሊንኩ የሚላክላችሁ ከማታውቁት ሰው ብቻ ሳይሆን፣ አካውንታቸው በተጠለፈ የቅርብ ጓደኞቻችሁ ወይም ዘመዶቻችሁ ስም ሊሆን ይችላል። 🔥​ከዚያ ሊንኩን ልክ እንደነካችሁት የእናንተም የቴሌግራም አካውንት ወዲያውኑ በሰከንዶች ውስጥ ይጠቃል፣ ከቁጥጥራችሁ ውጪ ይሆናል። ከዚያም በእናንተ ስም ለሌሎች ሰዎች ተመሳሳይ ቫይረስ ይልካል። ​⚠️ስለዚህ ከማንኛውም ሰው (የምታውቁትም ይሁን የማታውቁት) የሚላክላችሁን ማናቸውንም አይነት ሊንክ በፍጹም አትንኩ! አትክፈቱ! ✅​እባካችሁ ይህንን መረጃ ለምትወዷቸው ሰዎች ሁሉ በማጋራት ከጠላፊዎች ይታደጓቸው። ሼርር በማድረግ ሰዎችን ከመጥፎ ነገር እንዲከላከሉ እርዷቸው🙏 Meles Shiferaw

6ኛ እና 8ኛ ክፍል ዝግጅ!!! ከቀጣይ ሳምንት ለፈተና ተቀማጭ ናችሁ!

📚 የተፈታኞች መብትና ግዴታ ✅ 📚 ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት  አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና   ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት። 📚 ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል። 📚 ተፈታኙ/ኟ የሰራበትን የመልስ ወረቀት ለፈታኙ በመስጠት  የጥያቄ ወረቀቱን ይዞ መውጣት ይችላል 📚 ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፎ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ 📚 የሚሠራባቸው የጥያቄና የመልስ መስጫ ወረቀቶች ለሌሎች ተፈታኞች ዕይታ የተጋለጡ እንዳይሆኑ ሸፍኖ መስራት ይኖርበታል 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት  የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ። 📚 እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ። 📚 ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ  ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው። 📚 ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም። 📚 ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት   እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። 📚 ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል። 📚 ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል። ለተፈታኞች የተፈቀዱ ✅ እርሳስ ✅ የተማሪዎች የደንብ ልብስ (UNIFORM) ✅ ADMISSION CARD ✅ ላጲስ፣ መቅረጫና ማስመሪያ ለተፈታኞች የተከለከሉ ❌ ስልክ ይዞ መግባት አይቻልም ❌ ካልኩሌተር ❌ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ❌ ሰዓት ❌ በሀኪም ከታዘዘ ውጪ የሆኑ መነጽሮች ❌ የሚነበቡ ጽሁፎች በሙሉ የፈተና ኦረንቴሽን ቀን √ ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል በ05/10/2018 ዓ.ም በፈተና ጣቢያችሁ። #ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ √ 6ኛ ክፍል ከሰኔ 8- 10 /2018 ዓ/ም √ 8ኛ ክፍል ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ/ም ይሆናል።

በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለከተማ ትምህርት ፅ/ቤት ስር የምትገኙ የግል እና የመንግስት አንደኛ ደረጃና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤቶች አርብ  በቀን 5/10/2018 ዓ.ም በተመደቡበት የፈተና ጣቢያ ትምህርት ቤት  ጠዋት 3:00 ሰዓት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ዙሪያ Orientation ይሰጣል ተብሏል::

የ2018_ዓ_ም_የፈተና_ጣቢያ_እና_ፈታኝ_ዝርዝር.xlsx0.84 KB

የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ ➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ❾ መልስ መስጫ ወረቀቱ ጥግ ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው፤ ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፣ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ ⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ማጥፊያ እና መቅረጫ አይለያችሁ። ⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፣ ሥዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። ⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀምበት ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን። ##ወላጆች እና ተማሪዎች ስለ 6ኛ ክፍል ፈተና ማወቅ ያለባቸው ተግባራት ⏩ ከፈተናው በፊት የሚጠበቁ ተግባራት 👉 መታወቂያ መያዝ፦ በፎቶግራፍ የተረጋገጠውንና የፈተና ቁጥራቸውን የያዘውን ካርድ መያዝ ይኖርባቸዋል። 👉 በሰዓቱ መገኘት፦ ፈተናው ከመጀመሩ ቢያንስ ከ30 ደቂቃ በፊት በፈተና ጣቢያው ተገኝቶ ቦታን መያዝ ያስፈልጋል። 👉 የመፈተኛ ቁሳቁሶችን ማዘጋጀት፦ እርሳስ (HB 2 Pencil)፣ ማጥፊያ እና መቅረጫ ብቻ ይዞ መገኘት። ⏩ በፈተና ወቅት የሚጠበቁ ተግባራት 👉 የፈታኞችን መመሪያ መስማት፦ የቃልም ሆነ የጽሑፍ መመሪያዎችን በትዕግስት ማዳመጥና መተግበር። 👉 የግል መረጃን በትክክል መሙላት፦ ስም፣ የፈተና ቁጥር እና ሌሎች መረጃዎችን በጥንቃቄ መጻፍ። 👉 ኩረጃን በፍጹም መራቅ፦ ከሌላ ተማሪ መቅዳት፣ የራስን መልስ ማሳየት ወይም መቅዳት የተከለከለ ነው። 👉 በራስ መተማመንና ጸጥታን መጠበቅ፦ ሙሉ ጸጥታን በመጠበቅ ፈተናውን በግል ጥረት ብቻ መሥራት። ⏩ በፈተና ክፍል ውስጥ የተከለከሉ ተግባራት 👉 ሞባይልና ኤሌክትሮኒክስ መያዝ የተከለከለ ነው፦ ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ወይም ሌላ መሳሪያ ይዞ መግባት አይፈቀድም። 👉 ያልተፈቀዱ ወረቀቶችን አለመያዝ፦ ማስታወሻ፣ መጽሐፍ ወይም የተጻፉ ወረቀቶች ይዞ መገኘት ከፈተና ያሳግዳል። 👉 ያለፈታኝ ፈቃድ አለመንቀሳቀስ፦ ፈተናው እስኪያልቅ ድረስ ያለ ፈቃድ ከወንበር መነሳት ወይም መውጣት አይቻልም። እነዚህን እና መሰል ህጎችን በአግባቡ በመተግበር የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንዲችሉ ይህን መሰጃ ቀድመን እናሳውቃለን ።

የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች፣ ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ
+1
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ ➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ ⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ ⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። ⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።

photo content
+1

"already dead"
"already dead"

በሰው ልጅ የዕለት ተዕለት ግንኙነት፣ በውስጣዊ ስብዕና ግንባታ እና በስኬታማ አመራር ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ወርቃማ መርህ ነው። ይህንን ሰፊ ሀሳብ በዋና ዋና ምሰሶዎች ከፋፍለን እንደሚከተለው ማየት እንችላለን፦ 1. የማስተዋል እና የማዳመጥ ጥበብ ለመናገር አለመፍጠን ማለት መናገር አለመቻል ወይም ዝምተኛ መሆን ማለት አይደለም፤ ይልቁኑ ከመናገር በፊት ለማዳመጥ እና ለማስተዋል ቅድሚያ መስጠት ማለት ነው። • የሰሚውን ፍላጎት መረዳት፦ አንድን ነገር ለመናገር ከመቸኮላችን በፊት ሌላው ሰው ምን እያለ እንደሆነ ሙሉ ትኩረት ሰጥቶ ማዳመጥ፣ የሃሳቡን ፍሬ ነገር በትክክል ለመረዳት ይረዳል። • ክብርን መግለጫ፦ ሰዎችን ሳያቋርጡ ሙሉ ሃሳባቸውን እስኪጨርሱ ድረስ በትዕግስት ማዳመጥ ለነሱ ያለንን ክብር ያሳያል። 2. የቃላት ጥንካሬ እና ክብደት ቃላት አንዴ ከአፍ ከወጡ በኋላ ተመልሰው ሊታጠፉ የማይችሉ ፍላጾች ናቸው። ለመናገር አለመቸኮል የቃላቶቻችንን ጥራት እና ክብደት ይጨምራል። • ስህተትን መቀነስ፦ በስሜት ወይም በችኮላ የሚሰነዘሩ ቃላት ብዙ ጊዜ ስህተት፣ አሳሳች ወይም ሰዎችን የሚያስቀይሙ ሊሆኑ ይችላሉ። ቆም ብሎ ማሰብ ግን ትክክለኛውን እና ገንቢ የሆነውን ቃላት ለመምረጥ ጊዜ ይሰጠናል። • የሃሳብ ብስለት፦ ሰከን ብሎ የሚናገር ሰው የሚሰጠው አስተያየት ወይም ውሳኔ በሚገባ የታሰበበት ስለሚሆን በሰሚዎች ዘንድ ተሰሚነቱና ተቀባይነቱ ከፍተኛ ነው። 3. ስሜትን መግታት ብዙውን ጊዜ ፈጥኖ የመናገር ፍላጎት የሚመጣው እንደ ቁጣ፣ መከላከል  ወይም ከመጠን ያለፈ ደስታ ካሉ ፈጣን ስሜቶች መነሻነት ነው። • የቁጣ ቁጥጥር፦ በአንድ ነገር ስንቆጣ ፈጥነን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ "ለመናገር መዘግየት" ቁጣችን በረድ እንዲል እና ነገሮችን በምክንያታዊነት እንድንፈታ ያደርገናል። • ግጭትን ማስወገድ፦ በትዳር፣ በስራ ቦታም ሆነ በማህበራዊ ህይወት ውስጥ የሚፈጠሩ አብዛኞቹ አላስፈላጊ ግጭቶች መነሻቸው ከመናገር በፊት አለማሰብ ነው። 4. በአመራር እና በማህበራዊ ህይወት ያለው ሚና በማንኛውም የአመራር እርከን ላይ ያለ ሰው ይህንን መርህ መተግበሩ በጣም ወሳኝ ነው። • የመሪነት ብቃት፦ አንድ መሪ ከመናገሩ በፊት ሁኔታዎችን በጥንቃቄ ሲመረምር፣ የቡድኑን አባላት ሃሳብ ሲያዳምጥ እና መረጃዎችን ሲያደራጅ የሚሰጠው መመሪያ ግልጽ እና ውጤታማ ይሆናል። • ታማኝነትን መገንባት፦ የማይቸኩል እና ሚዛናዊ ንግግር የሚያደርግ ሰው በሰዎች ዘንድ እንደ አስተማማኝ እና ባለራዕይ ተደርጎ ይወሰዳል። በአጠቃላይ "ለመናገር አትፍጠን" የሚለው መርህ የምላሳችንን ፍጥነት ከግንዛቤያችን እና ከማስተዋል አቅማችን ጋር እንድናስተካክል የሚመክር የህይወት መመሪያ ነው። ይህንን መርህ በህይወታችን በተገበርን ቁጥር ከስህተት እንጠበቃለን፣ ግንኙነቶቻችን ሰላማዊ ይሆናሉ፣ ንግግራችንም የሰዎችን ህይወት የሚገነባ ማር ይሆናል። #A #ሰናይ_አዳር

ለ3 ቀናት ቀን ትምህርት አይኖርም ተብሏል‼ ከ7ኛው ሐገራዊ ምርጫ ጋር በተገናኘ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በመጭው ነገ ሰኞ ግንቦት 24-ግንቦት26/2018ዓ.ም ድረስ የትምህርት ተቋማት ዝግ ይሆናሉ ብሏል። ይህ የምርጫ ቦርድ መግለጫ እንደተጠበቀ ሆኖ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘ ት/ቤቶች ለ3 ቀናት(ሰኞ: ማክሰኞና ረቡዕ) ትምህርት አለመኖሩን ለተማሪዎቻቸው አሳውቀዋል። ዋና ምክንያቱ መምህራን በሚኖሩበት አካባቢ የምርጫ ታዛቢ ሆነው ቢሰየሙ በተማሪዎች ዘንድ እንግልት እንዳይፈጠር በማሰብ የተደረገ ነው ተብሏል።

Teachers need more than subject knowledge. Effective teaching combines knowledge, skill, character, and continuous learning. Here are key things teachers should know: 1. Subject Knowledge A teacher must understand the subject deeply and accurately. Students trust teachers for correct information and guidance. 2. Teaching Methods Teachers should know: how to explain ideas clearly, how to ask effective questions, how to manage classroom activities, how to use learner-centered methods. Different students learn differently. 3. Child and Adolescent Psychology Teachers should understand: stages of growth and development, learners’ emotions and behavior, motivation, individual differences. This helps teachers teach with patience and understanding. 4. Classroom Management A teacher should know how to: maintain discipline respectfully, create a positive learning environment, handle conflicts calmly, encourage participation. Good classroom management supports learning. 5. Communication Skills Teachers need strong: speaking, listening, reading, writing skills. Clear communication reduces misunderstanding. 6. Assessment and Evaluation Teachers should know: how to prepare tests and assignments, how to assess fairly, how to give constructive feedback, how to monitor learners’ progress. Assessment should improve learning, not only measure it. 7. Educational Technology Modern teachers should know how to use: computers, projectors, educational apps, online learning platforms. Technology can make learning more interactive and effective. 8. Professional Ethics Teachers should practice: honesty, fairness, respect, confidentiality, responsibility. Teachers are role models in society. 9. Inclusive Education Teachers should understand that learners differ in: ability, language, background, learning pace. Every learner deserves equal opportunity. 10. Continuous Professional Development Education changes constantly. Teachers should continue: reading, researching, attending trainings, improving skills. A good teacher never stops learning. 11. The Purpose of Education Teachers should know that education is not only about passing exams. It is also about: building character, developing critical thinking, preparing responsible citizens, improving society. Short Conclusion A teacher must be: knowledgeable, patient, communicative, ethical, adaptable, and committed to lifelong learning. Teaching is not simply giving information; it is shaping minds and futures. Master Chimdessa ✍️

✅ AI (አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ)፡ ስጋት ወይስ መልካም አጋጣሚ? የቴክኖሎጂው ዓለም በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ ነው። ዛሬ ላይ "AI" ወይም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሚለውን ቃል በየቀኑ እንሰማለን። አንዳንዶች "የሰውን ልጅ ስራ ሊቀማ መጣ" ብለው በስጋት ሲያዩት፣ ሌሎች ደግሞ "ኑሯችንን እና ስራችንን ሊያቀልል የመጣ ታላቅ እድል ነው" ይላሉ። ለመሆኑ AI በእርግጥ ስጋት ነው ወይስ መልካም አጋጣሚ? እውነታውን በምሳሌዎች አስደግፈን በሰፊው እንየው። ✅1. መልካም አጋጣሚዎቹ (The Opportunities) AI በአግባቡ ከተጠቀምንበት በሁሉም ዘርፍ ምርታማነታችንን በብዙ እጥፍ የሚያሳድግ ታላቅ ረዳት ነው። ⏺ በትምህርት ዘርፍ (Education):    AI ለእያንዳንዱ ተማሪ እንደየአቅሙና ፍጥነቱ የሚያስተምር የግል አስተማሪ (Personal Tutor) መሆን ይችላል።    💎 ምሳሌ፦ አንድ ተማሪ አስቸጋሪ የሂሳብ ወይም የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ ፅንሰ-ሀሳብ ባይገባው፣ AI-ን "እባክህ ይህንን ህግ ለ6ኛ ክፍል ተማሪ እንደሚረዳው አድርገህ በምሳሌ አስረዳኝ" ቢለው፣ ልክ እንደ አፍቃሪ መምህር አውርዶ ሊያስረዳው ይችላል። ይህ የትምህርት ተደራሽነትን ያሰፋል። ⏺ በስራ እና ፈጠራ (Productivity & Creativity):    ቀደም ሲል ቀናትን ወይም ሳምንታትን ይወስዱ የነበሩ ስራዎችን AI በደቂቃዎች ውስጥ ያከናውናል።    💎 ምሳሌ፦ አንድ የሶፍትዌር ባለሙያ (Developer) ውስብስብ የሆኑ የዳታቤዝ ስራዎችን (ለምሳሌ SQL Triggers ወይም Functions) ለመጻፍ ሰዓታትን ሊፈጅበት ይችላል። አሁን ግን አጋዥ የAI መሳሪያዎችን በመጠቀም ኮዱን በጥራትና በፈጠነ መልኩ ማመንጨት ይችላል። ይህም ትኩረቱን ይበልጥ በትልልቅ የሲስተም ዲዛይኖች ላይ እንዲያደርግ ይረዳዋል። ⏺ በጤናው ዘርፍ (Healthcare):    AI የበሽታ ምልክቶችን በፍጥነት በመለየት ረገድ የዶክተሮችን ስራ ያግዛል። በሺዎች የሚቆጠሩ የኤክስሬይ ፎቶዎችን በሰከንዶች ውስጥ መርምሮ በሽታን ቀድሞ መለየት ይችላል። ✅ 2. ስጋቶቹ (The Risks) ልክ እንደማንኛውም የቴክኖሎጂ ግኝት፣ AI የራሱ የሆኑ ከባድ ስጋቶች አሉት። ⏺ የስራ እድል መጥፋት (Job Displacement):    መለማመጃና ደጋጋሚ የሆኑ ስራዎች (ለምሳሌ የዳታ ኤንትሪ፣ የተወሰኑ የደንበኞች አገልግሎት ስራዎች) በAI ሙሉ በሙሉ እየተተኩ ነው።    💎 ምሳሌ፦ ቀደም ሲል ለአንድ ድርጅት አርማ (Logo) ወይም የማስተዋወቂያ ምስል ለመስራት ግራፊክስ ዲዛይነር የግድ ያስፈልግ ነበር። ዛሬ ግን እንደ Midjourney ወይም DALL-E ያሉ የAI መሳሪያዎች በሰከንዶች ውስጥ አስገራሚ ምስሎችን ይሰራሉ። ራሳቸውን የማያድሱ ባለሙያዎች የመገለል ስጋት አለባቸው። 💎 የሀሰተኛ መረጃዎች መበራከት (Deepfakes & Misinformation):    AI የአንድን ሰው ድምፅ እና ምስል አስመስሎ የመስራት (Deepfake) አቅም አለው።    💎 ምሳሌ፦ አንድ ታዋቂ ሰው ወይም መሪ ያልተናገረውን ንግግር ድምፁንና ምስሉን 100% አስመስሎ በመስራት ህዝብን ማሳሳትና ግጭት መፍጠር ይቻላል። ይህ ለደህንነት ትልቅ ስጋት ነው። 💎 የሰነፍ ትውልድ መፈጠር (Over-dependence):    ሰዎች ሁሉንም ነገር AI እንዲያስብላቸውና እንዲጽፍላቸው ካደረጉ፣ የሰው ልጅ የማሰብ፣ የመመራመርና የፈጠራ ብቃት ሊወርድ ይችላል። ✅ ታዲያ መፍትሄው ምንድን ነው? AI-ን ልክ እንደ "ቀልጣፋ ረዳት" ማየት እንጂ እንደ "ምትክ" ማየት የለብንም። ቴክኖሎጂው ሰዎችን ከስራ አያባርርም፤ ነገር ግን AI-ን መጠቀም የሚችሉ ሰዎች AI-ን የማይጠቀሙትን ሰዎች መተካታቸው አይቀሬ ነው። ✅ ምን ማድረግ አለብን? 1. ክህሎትን ማሳደግ (Upskilling): የቴክኖሎጂውን አጠቃቀም መልመድና ከስራችን ጋር ማዋሃድ። 2. AI ሊተካቸው የማይችላቸውን ክህሎቶች ማዳበር፦ ስሜታዊ ብልህነት (Emotional Intelligence)፣ የሰዎች ግንኙነት፣ አመራር እና ስልታዊ አስተሳሰብ (Strategic Thinking) በAI አይተኩም። ✅ ማጠቃለያ ባጭሩ AI ስጋትም መልካም አጋጣሚም ሊሆን የሚችለው በአጠቃቀማችን ላይ ተመስርቶ ነው። ቢላዋ ምግብ ለመስራትም ሰውን ለመጉዳትም እንደሚያገለግለው ሁሉ ማለት ነው። ብልህነት የቴክኖሎጂው ተገዢ መሆን ሳይሆን፣ ቴክኖሎጂውን ተጠቅሞ ህይወትንና ስራን ማቃለል ነው።

ሰኞ ግንቦት 24 ሥራ ዝግ ነው። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ/ም በፌዴራል እና ክልል መንግሥታዊ ተቋማት እንዲሁም የግል ተቋማት ሥራ ዝግ ሆኖ ይውላል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄደውን የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል። ቦርዱ፦ - ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል። - ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል። - የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ እንዲያከነውኑ ፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት እንደማያስገድድ አሳውቋል። - የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ አረበታቷል። #NEBE ቲክቫህ ኢትዮጵያ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

እድሜዬ እየጨመረ በሄደ ቁጥር እየገቡኝ የሄዱ ነገሮች 1. ፦ ከሁሉ በላይ የአእምሮ ሰላም ትልቅ ሀብት እንደሆነ ተረዳሁ። አንዳንድ ጊዜ ክርክርን ከማሸነፍ ይልቅ ዝም ብሎ ማለፍ ሰላም ይሰጣል። 2. ፦ በጭንቅ ቀን ከጎንህ የሚቆሙትና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሚወዱህ የቤተሰብህ አባላት ብቻ መሆናቸውን አወቅኩ። 3. ፦ ትላንት ያለፈ ታሪክ ነው፤ ነገ ደግሞ ተስፋ። ዛሬን በአግባቡ መጠቀምና መኖር ብልህነት እንደሆነ ተረዳሁ። 4. ፦ ጤና ከሌለህ ምንም አይነት ቁሳዊ ሀብት ትርጉም እንደሌለውና ሰውነትን መንከባከብ ግዴታ እንደሆነ ገባኝ። 5. ፦ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጓደኞች ከመኖራቸው ይልቅ በችግር ጊዜ የሚደርሱ ጥቂት እውነተኛ ጓደኞች መኖራቸው ይበልጣል። 6. ፦ ሌሎችን ለማስደሰት ከመሞከር በፊት ራስን መቀበልና መውደድ ለደስታ ቁልፍ መሆኑን ተረዳሁ። 7. ፦ ሰዎችን ይቅር የምንለው ለእነሱ ብለን ሳይሆን እኛ ከቂም ሸክም ተላቀን በሰላም ለመኖር ስንል እንደሆነ አወቅኩ። 8. ፦ በህይወት ውስጥ የማይለወጥ ነገር ቢኖር ለውጥ መኖሩ ብቻ ነው። ከሁኔታዎች ጋር መላመድ መቻል የጥንካሬ ምልክት ነው። 9. ፦ ባወቅክና በከበርክ ቁጥር ይበልጥ ትሁት መሆን የውስጥ እርካታን እንደሚሰጥ ተረዳሁ። 10. ፦ ስኬት ማለት በገንዘብ ብዛት ብቻ ሳይሆን በህይወትህ ምን ያህል ሰላም እንዳለህና ስንት ሰዎችን እንደረዳህም ጭምር ነው። 11. ፦ ትምህርት ቤት ባንቆምም ህይወት በየቀኑ አዲስ ትምህርት እንደምታስተምረንና ለተማሪነት ዝግጁ መሆን እንዳለብን አወቅኩ። 12. ፦ ደስታ ከውጭ በሚመጡ ነገሮች ላይ ሳይሆን እኛ ነገሮችን በምናይበት እይታና በውስጣዊ እርካታችን ላይ የተመሰረተ ነው።

የተከለሰ የ2018 የትምህርት ዘመን የትምህርት የማጠቃለያ ፈተና መርሃ-ግብር @eec1227
+1
የተከለሰ የ2018 የትምህርት ዘመን የትምህርት የማጠቃለያ ፈተና መርሃ-ግብር @eec1227

+5
GRADE 8 MODEL EXAM 
Second semester May-2018E.C/2026 G.C
By: Addis Ababa City Administration Education Bureau Join🔻 ══════════════ • https://t.me/ETMathsNetwork • Don't forget to react and share. •♥️•♥️ Many Thanks ♥️•♥️• 𝐃𝐈𝐆𝐈𝐓𝐀𝐋 𝐄𝐃𝐔𝐂𝐀𝐓𝐈𝐎𝐍 𝐅𝐎𝐑 𝐀𝐋𝐋

+6
G 6 AMH. MODEL EXAM.pdf7.62 KB