የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church
رفتن به کانال در Telegram
1 070
مشترکین
+124 ساعت
+177 روز
+3830 روز
آرشیو پست ها
የእግዚአብሔር ምሕረት አያልቅምና፥ ርኅራኄውም አይጠፋምና ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው። ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው።” (ሰቆቃው ኤርምያስ 3፥22-23)
🌼 የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች፣ ዛሬ በአዲስ ዓመት መጀመሪያ ላይ ቆመናል።
🌻አዲስ ዓመት ማለት እንዲሁ የቀን መቁጠሪያ መቀየር ብቻ አይደለም። አዲስ ዓመት የእግዚአብሔር ታማኝነት፣ ምሕረትና ርኅራኄ በሕይወታችን ላይ የላቀ መሆኑን የምናይበት ልዩ ምዕራፍ ነው።
⏮️ ያለፈውን ዓመት በብዙ ፈተና፣ በደስታም ሆነ በኀዘን አሳልፈን ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን ዛሬ እዚህ የቆምነው በገዛ ጉልበታችን ሳይሆን በእግዚአብሔር ቸርነት ነው። ማለዳ ማለዳ አዲስ የሚሆነው የእግዚአብሔር ምሕረት፣ ዛሬም በዚህ አዲስ ዘመን ከእኛ ጋር ነው።
✅በዚህ አዲስ ዓመት እግዚአብሔር በሕይወታችን ላይ ሊያደርጋቸው የሚፈልጋቸውን ሦስት ዋና ዋና እውነቶች እንመለከታለን፦
1. ያለፈውን መተው እና ወደ ፊት መራመድ
ብዙዎቻችን ወደ አዲሱ ዓመት ስንገባ የድሮውን ትዝታ፣ ጸጸት፣ ቂም ወይም ሽንፈት ይዘን ለመግባት እንሞክራለን። ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ በኢሳይያስ 43፥18-19 ላይ እንዲህ ይላል፦ “የቀደመውን ነገር አታስቡ፥ የጥንቱንም ነገር አታስተውሉ። እነሆ፥ አዲስ ነገርን አደርጋለሁ፤ እርሱም አሁን ይበቅላል፥ እናንተስ አታውቁትም?”
እግዚአብሔር በሕይወታችን አዲስ ነገር ማድረግ የሚጀምረው፣ እኛ የድሮውን ስንለቅ ነው። ያለፈው ዓመት ስህተት ወይም ውድቀት ዛሬ ላይ ሊያስረን አይገባም። ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳለው፦ “በኋላዬ ያለውን እየረሳሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ እዘረጋለሁ።” (ፊልጵስዩስ 3፥13)። ይህ አዲስ ዓመት ይቅር የምንልበት፣ ቂምን የምንጥልበትና በእግዚአብሔር ይቅርታ ታድሰን ወደ ፊት የምንራመድበት ዘመን ሊሆን ይገባል።
2. የአስተሳሰብና የልብ መታደስ (አዲስ ማንነት)
አዲስ ዓመት ውጫዊ ለውጥ ብቻ ሳይሆን ውስጣዊ ለውጥን ይጠይቃል። ልባችንና አስተሳሰባችን ካልተቀየረ፣ አዲሱ ዓመት የድሮው ሕይወታችን ድግግሞሽ ብቻ ነው የሚሆነው። እግዚአብሔር በነቢዩ ሕዝቅኤል በኩል እንዲህ የሚል ተስፋ ሰጥቶናል፦ “አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፤ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አውጣለሁ የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ።” (ሕዝቅኤል 36፥26)
እግዚአብሔር በዚህ ዓመት የቆሰለውን፣ የደነደነውንና የተሰበረውን ልባችንን በአዲስ መንፈስ ሊቀይረው ይፈልጋል። በአዲሱ ዓመት በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት ሆነን እንድንመላለስ ተጠርተናል። “ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፏል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኗል።” (2ኛ ቆሮንቶስ 5፥17)።
3. እግዚአብሔርን በሕይወታችን የመጀመሪያ ማድረግ
ይህ አዲስ ዓመት ፍሬያማና በረከት የሞላበት እንዲሆንልን ከፈለግን፣ እግዚአብሔርን በዕቅዳችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን ሁሉ መጀመሪያ ማድረግ አለብን። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማቴዎስ ወንጌል ላይ ሲያስተምር፦ “ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።”(ማቴዎስ 6፥33) ብሎናል።
ዘመኑን የሚባርከው፣ ቀናቱን ብሩህ የሚያደርገው እግዚአብሔር ነው። እግዚአብሔር በፊታችን ሲቀድም ጠማማው ይቃናል፣ የወረደው ከፍ ይላል። ስለዚህ ዘመናችንን፣ ልጆቻችንን፣ ትዳራችንንና ሥራችንን በእግዚአብሔር ፊት በአደራ በማስቀመጥ ልንጀምር ይገባል።
‼️ የተወደዳችሁ ቅዱሳን፣ እግዚአብሔር የሰጠን ይህ አዲስ ዓመት የጸጋ፣ የሰላም፣ የፍቅርና የስኬት ዘመን እንዲሆንልን የእርሱ ፈቃድ ነው።
😊 እኛም ያለፈውን ትተን፣ ልባችንን ለእርሱ ሰጥተን፣ እርሱን አስቀድመን ስንጓዝ ዘመናችን ሁሉ በበረከት ይሞላል።
ዳዊት በመዝሙሩ እንዳለው፦ “ዓመትን በቸርነትህ ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።”(መዝሙር 65፥11)።
🌼እግዚአብሔር ይህንን አዲስ ዓመት በቸርነቱ ያቀዳጅልን! ምድራችንን ሰላም፣ ቤታችንን በረከት፣ ልባችንን ፍቅር ያድርግልን።🌻🌼
አሜን። መልካም አዲስ ዓመት!
Nati M.
ኢየሱስ ሆይ ና! Singer Gashaw Temesgen.m4a4.85 MB
+8
የቤተሰብ የአመቱ መዝጊያ ኘሮግራም ማስታወሻ
መልካም አዲስ ዓመት
The Seventh-day Adventist Church has passed 24 million members worldwide, according to the advance release of the 2026 Annual Statistical Report from the General Conference. Africa accounted for more than 81% of the church’s net membership growth in 2025.
The new figures come as Adventists worldwide launch OneVoice27, a global evangelistic initiative focused on digital and personal outreach.
🔗Read more: https://spectrummagazine.org/current-share/adventist-membership-passes-24-million-as-onevoice27-launches
#AdventistNews #Membership #OneVoice27
#onevoice27 #hopestartshere #allthingsnew
#OneVoice27
#HopeStartsHere
#AllThingsNew
ሰላም ሰላም!
ይህ ከሀዋሳ መናኸሪያ አጥቢያ ቤ/ክ የተላለፈ መልዕክት ነው::
------
እንደምን ሰነበታችሁ ወገኖች!
እግዚአብሔር ቢፈቅድና ብንኖር ከጳጉሜ 01/2018 እስከ መስከረም 02/2019 ዓ.ም የሚካሄደውን የቤተሰብ ሥልጠና መከታተል የምንፈልጉ ወገኖች በሙሉ:
ቅደመ ሁኔታዎችን ለማሟላትና በመጨረሻው ቀን ለተሳታፊ ባለትዳሮች የሚሰጠውን ሰርትፊኬት ለማዘጋጀት እንዲረዳን ስማችሁን ለአጥቢያ ቤተ ክርስቲያናችን ወንጌላዊያን ወይንም ሽማግሌዎች በመስጠት ወይም ከሥር በተጠቀሰው ስልክ ቁጥር እየደወላችሁ እንድታስመዘግቡ እያሳሰብን፤
እነዚሁ ጥንዶች ከመጀመሪያው የማክሰኞ ምሽት የቤተሰብ ትምህርት አንስቶ እስከ ሰንበት ጠዋት የጋብቻ ተሀድሶ ድረስ ትምህርቶቹን ያለ ማቋረጥ እንዲከታተሉ የሚጠበቅ ሲሆን ይህንን ላደረጉ ደግሞ
ቤተ ክርስቲያን እና ኢትዮ ባርናባስ የወንጌል አገልግሎት ያዘጋጁት የምስክር ወረቀት በሰንበት ቀን ዋናው አገልግሎት ላይ የሚሰጥ ይሆናል።
ማሳሰቢያ: ከሐሙሱ የባለ ትዳሮች ስልጠና በስተቀር ሁላችንም በሁሉም መንፈሳዊ ፕሮግራሞች የተጋበዝን ስለሆነ ተገኝተን ሌሎችንም እንጋብዝ
ጌታ ይባርካችሁ!
0916836762
One Voice 27 :Mission for all
is soon to be launched.
Mission For All
Are you ready?
ቀን ነሀሴ 23,2018:ሀዋሳ
ማስታወቂያ!
የኢሌደር ጴጥሮስ ጎዴቦ ባለቤት ወ/ሮ አበባይቱ ጊቻሞ እናታቸውን ቀብረው የመጡ መሆኑን ተከትሎ ቤተክርስቲያናችን የማፅናኛ ፕሮግራም ዛሬ ከሰዓት ከቀኑ 9:00 ጀምሮ በመኖሪያ ቤታቸው አዘጋጅታለች።
በመሆኑም ቤተክርስቲያናችን ለእህታችንና ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን እየተመኘች ምዕመንም በፕሮግራሙ በመገኘት እንድታፅናኑ በጌታ ፍቅር እናሳስባችኋለን!
ተባረኩ
አድራሻ- ከሚሽን መካነ መቃብር በኩል ከመጡ የአድቬንቲስት 2ኛ ደረጃ ት/ ቤትን(High School) እንደጨረሱ ባለው ወደ ግራ በሚያስገባው መግቢያ ሲገቡ ከፈርኒችር ቤቱ ቀጠወሎ(ጀርባ)ያለው ግቢ::
+1
ከደቡብ ግሪን ኢት/ ሰበካ የጎዳና ፈላጊ ክለብ በሐዋሳ ካምፖሬ ጉዞ መልስ በአንድ አገልጋይ ላይ ከአቅም በላይ የሆነ አደጋ ደርሶበት ሐዋሳ ያኔት ሆስፒታል የራስ ቅል ቀዶ ጥገና ህክምና ተደርጎለት በአሳሳቢ ሆኔታ ላይ (@Hawassa referral hospital) ስላለ እባካችሁ እንጸልይለት የበኩላችንንም ድጋፍ እናድርግለት:: የጎዳና ፈላጊው ስም ሺበሺ ደምሴ ሲሆን ፀልዩለት እንደግፍ ::
አከዉንት ቁጥር 1000235484017 አያሌው ደምሴ
ጌታ ይባርካችሁ!
Hello dears,
We received requests that some couldn't apply for the Space Science virtual session to be held at Hawassa American Corner announced earlier.
Having arranged with the central organizers of the training we got permission to accommodate a few more trainees for that on a new link:
https://tally.so/r/gDPxVJ?address=Hawassa
So, please get registered as soon as possible and let us know if you face any inconvenience while registering.
You may reach us at: hawassaac@gmail.com
Kind regards,
ሰላም ቤተሰብ!
ይህ ነገር ከ9-12 ክፍል ላሉ ወጣቶቻችን ሳይጠቅም ይቀራል?
እስኪ ተመልከቱት።
ተባረኩ!
የኤልሻዳይ ኳየር አገልግሎት - 2008 ዓ.ም
