የጥበብ - መንገድ ™
رفتن به کانال در Telegram
❝ Art is a step from nature toward the Infinite ~ Kahlil Gibran ™🌸📚 @abawassie ✉️
نمایش بیشتر5 370
مشترکین
+124 ساعت
+787 روز
+25530 روز
آرشیو پست ها
5 372
ሮሚና ካፌ ዝናብ እያካፋ በአይናችን እየተጨዋወትን ነው : በአይኖቿ የነፍስን ዜማ ታዜማለች በነፍሴ ጆሮ እሰ'ማታለሁ : በዝምታችን ውስጥ የዘላለምን የመንፈስ አለም እንጨዋወታለን : በመሃል ለራሴ 'በጆሮ የሚሰማውን ብቻ የሚሰማ ምንኛ ያልታደለ ነው : በአይኑ ብቻ የሚያይ እንደምን ያለ አሳዛኝ ነው?' ስል ራሴን እጠይቃለሁ : በዝምታችን ውስጥ ከውብ ሙዚቃ የሚልቅን ውበት አግኝቻለሁና።
አፏን ከፈተች - ተናገረች : ያኔ የምድር ልሳናት ሁሉ ተዘጉ : ፀሃይ እሷ ባለችበት እንደማትወጣው እንዲሁ : አዎራች - ከትውስታ ማህደር ገለጠች : ጠየቀች...
'በአምስቱ መሳም ሳመኝ ብዬክ ነበር'ኣ?'
አዎ!... መለስኩ
'እሽ አሁን በስንቱ መውደድ ትወደኛለህ?'
አመነታሁ - ስንት ልበል? አንድ ልበል? በዘላለም? ሁለት ልበል በተቃርኖ? ሶስት ልበል በስላሴ? ያኔ የፍቅር ጌታ ዳንቴን ለቢያትሪስ ሲፅፍ ያነቃው አሞር ራባይ አል-ባሲርን ወደኔ ላከ : እኔም እንዲህ ስል መለሰኩ 'በሁለት ፍቅር እወድሻለሁ!'
.
.
.
ከራስ ወዳድነቴ የተነሳ እወድሻለሁ : በፊት በፊት ይመሻል ይነጋል : ቀንና ደቂቃ ይነጉዳል እ...ር...ፍ የሚል የለም ሁሉም ሯጭ ነበር : አሁን ጊዜ ራሱ ቀልብ ገዛ : ስዓታት ትርጉምን አገኙ : ቀኑ ረፍትን ሰጠኝ - ስለሰጠሽኝ ሁሉ ከራስ ወዳድነቴ ተነስቼ አሸወድሻለሁ
ስምሽ ሲጠራ በደረቴ ውስጥ የተዘጋ በር ይከፈታል : በርግጥ ልቤ የአትክልት ስፍራ ቢሆን የሚፀድቀው ስምሽ ብቻ ነበር : አንችጋ ስሆን ራሴ ከራሴ ሲበልጥ አየዋለሁ - ተአምርሽ መቸስ አጃኢብ ነው።
ጆሮዎች ሳቅሽን ሲሰሙ ወንዝ በደረቅ መሬት ሲፈስ መሬቱ እንደሚርሰው እንዲሁ ይረሰርሳሉ : ልቤም የረሳውን ዘፈን ያስታውሳል።
ዝምታሽ ውስጥ መዝሙር አለ : ከያሬድ የላቀ : አንችን ሲያይ አየር አይነፍስም - እንደ ብርቱ ፃድቅ ሰው ይጸልያል አንጂ።
በጨለማዬ ውስጥ በጨለማዬ ውስጥ የበራሽ ብርሃን : በጥማቴ ውስጥ የተወለደች ምንጭ ነሽና - በራስ ወዳድነቴ እወድሻለሁ!
ደግሞም ስለአንችነትሽ እወድሻለሁ : ነፍስሽና ነፍሴ የጥንት ዘመዶች ናቸው : ስላወኩኝ እወድሻለሁ : ለዚህም ነው የሞት መልአክ መጥቶ : ነፍስያዬን አስጨንቆ አንድ ነገር ብቻ ተመኝ : አንድ ብቻ ነገር አድርግ ቢለኝ : ሁለቴ ሳላስብ 'ምኞቴ ምስጋና ብቻ ነው!' የምለው።
ቢሊዬን ነፍሳት በተርመሰመሱባት በዚች ምድር : ዘመት በነጎደባት አለም አማልዕክት ያልተገባኝን እሷን ስላሳዩኝ ምኞቴ ምስጋና ብቻ ነው።
ፍቅር ቅዱስ ቋንቋ ቢኖረው አንቺን በራሱ በፍቅር ለመግለፅ ዘመንን ከክሩኖስ ተበድሬ ይሄን ቋንቋ ብቻ የማጠናውም ለዚህ ነው - በሚገባሽ ልክ ለመውደድ።
በርግጥ ሺ ልብ ቢኖረኝ አንዱ አይንሽን : ሌላው ፀጉርሽን : አንደኛው ድምፅሽን ብቻ መላ ህዋስሽን እንዲወዱ በማድረግ ሌላ ስራ አልሰጣቸውም ነበር : ልቤ አፍ ሲኖረው የምፈቅድለት ብቸኛው ነገር በእያንዳንዱ ምቱ ስምሽን እንዲጠራ ነበር።
.
.
.
አሁን ከአይኗቿ ቀኖቸን የሚያበራ ፀዳች ወጣ - አንደበቷ ቃል አልተነፈሰም : በዝምታ ጥልቀት ተመለከተችኝ : በቃላት በማልገልፀው የነፍስ ቋንቋ *** ስልት ሹክ አለችኝ : እኔም የነፍሷን ድምፅ ለነፍሴ አሰምቼ አይኖቼን ጨፈንኩ : ስጨፍን የሚታየኝ ብቸኛው ነገር የሷ ብርሃን ነበር።
https://t.me/Jonahism5 372
[ያኔ ሂትለር ...]
ይሄን የጀምስ ሚለር ፁፍ ካነበብኩ በኋላ ስላላመንኩት ቀልቤን የሳበውን የጀነራሉን ዲያሪ ለማየት ስሞክር ሰዎዬው እውነትም እንደዛ አይነት አቋም ነበረው : የሆነ ቦታ ላይ 'Berlin gave me the blues. We have destroyed what could have been a good race and we are about to replace them with Mongolian savages. And all Europe will be communist…' ይለናል።
ደግሞ ቀጠል አድርጎ የስልጣኔ ጨራ የነካንት አገር አፍርሰን ራሽያ አለምን እንድትውጥ መንገድ ከፈትንላት በእውነታው ግን 'the Germans are the only decent people left in Europe.' ሲል ይቀጥላል።
ለእኔ ከሰውዬው የመጨረሻ ጥቅሴ ይሄ ይሆናል 'I think we’ve been fighting the wrong people all this time...'
አብዛኛው ለሚስቱ ቢያትሪስ የፃፋቸው ደብዳቤ ውስጥ የተገኙ ናቸው : በርግጥ ስለአንዳንድ ማህበረሰቦች ደግሞ በጣም የከፋ ነገር ተናግሯል።
ታዲያ የዘመንና የአለም አካሄድ ውጥረት ሲበዛው የቢሆን ነገሮች መልካም ናቸው : ግን ሂትለር አሸንፎ ቢሆንስ ኑኖ አለም ምን ትመስል ነበር?
ምዕራባዊያን ያን ሁሉ ስአት የተሳሳተ ጠላት ቢሆንስ ሲዋጉ የኖሩት?
Join
👇
https://t.me/Jonahism
5 372
[ኢአማኒነት ከደሙ ንፁህ አይደለም !]
ስታሊን በኦርቶዶክስ አለም ሶስተኛውን ትልቁን ካቴድራል [The Cathedral of Christ the Saviour] በታሊባናዊ መንገድ በድማሚት አጋይቷል : መንግስታዊ የነበረው ኢአማኒነት [ማሌት] 41000 የሚደርሱ ቤተክርስቲያን አብዛኛውን ዘግቷል ቀሪውን አፍርሷል።
ዴኒሽ እንደሚነግረን በሁለት ሺህ አመታት ውስጥ በዛ በጥቂት አመታት ብቻ ኢአማኒ : ፀረ ሃይማኖት እና ከሃይማኖት ውጭ በሆነ ጦርነት የጨረስናቸውን ያክል መጨረስ አልቻልንም [ዴኒሽ ምናልባትም በቀርብ አመታት ውስጥ ያገኘነውን የአጥፊ መሳሪያ ጉልበት በመስቀል ጦርነት እና በኢንኩዚሽን ጊዜ ብናገኘው ምን ሊፈጠር እንደሚችል ለማሰብ ፍቃደኛ አይደለም : በርግጥ የሚያናደኝ ሰው ነው!]
ኤቲዝም ከሳይንስ እና እድገት ጋር ብቻ ማያያዝ ከታሪክ እውነታ መግደፍ ነው : ብዙ ኢአማኒያን ሃይማኖትን ለማጥፋት የወጠኑ አሉ : የኮሙኒስት ፍልስፍናም ስሩ ኢአማኒነት ነው : በፈረንሳይ አቢዮት ጊዜ የነበረውን አስታውሱ [Cult of Reason] ወደ 30000 ቀሳውስት ተገድለዋል : በርግጥ በፍጥነት ተሸንፎ Cult of the Supreme Being በተሰኘ በዴይስቶች ተተክቷል : ይሄም ይበልጥ ቀሽም ነበር።
ከ1928-1932 የመጀመሪያው አምስት አመት ዕቅድ በተለይ 'atheist five-year plan' የነበረበት ዘመን ነበር የሶቪየቱ ጊዜ : ከዚህ በፊት በአንድ ቪዲዮ እንደገለፅኩት 'League of Militant Atheists' የተባሉ ክንፎች ነበሩ : በዚህ ኤቲዝም በስልጣን ላይ በወጣበት ዘመን ከ15 - 60 ሚሊየን ሰው እንደሞተ ይነገራል።
ሃይማኖት ከጠፋ ሰላም እንሆናለን ይሉት ቅዥት የማይገባኝ ለዚህ ነው!
ሃይማኖትን እቃወማለሁ? አዎ በሚገባ : የመጨረሻው የቤተመቅደስ ድንጋይ በመጨረሻው ካህን ላይ እንዲወድቅ እኛለሁ : ነገር ግን ከሃይማንት እኩል በሌሎች ተራ optimistic በሆኑ ቅዠቶችም አልማረክም።
ወንድሜ የሰው ልጅ የትኛውንም ውብ ነገር ለማበላሸት ቅን ፍጥረት ነው : ለዚህ ነው በጥንተ-አብሶ [original sin] የማምን ኤቲስት የሆንኩት።
በዛው ልክ ከጥፋት ውስጥ ውበትንም የሚሰራው ራሱ ነው : በዚህም ቅድስና ነውን አያለሁ! ከጥንተ ሃጢያቱ ሲፈወስ መልካምን ይሰራል ወይስ ቅዱስ ሁኖ ተፈጥሮ ወደ ሃጢያት ተጓዘ የሚለው የሩሶ ዘመዶች እና እኛ ሆብሳዊያን የምንከራከርበት ይሆናል! በርግጥ ሆብስም ሙሉ ለሙሉ እውነተኛ ሩሶም ሙሉ ቀሽም ነው የሚል እምነት የለኝም : ቢሆንም ቢሆንም ግን ሆብሳዊ ነኝ!
'አይ እኔ እንደዚህ አይነት ኢአማኝ አይደለሁም!' ኦ ሃይማኖትን በጥቅሉ ገዳይ እንደሆነ ከሰበክ ጂዬን እና ኮንከሮችም 'አይ እኔ እንደዚህ አይነት ሃይማኖት አይደለሁም!' ይሉሃል።
አንዳንድ ሃሳቦችን እንደ መፈክር መጠቀም መልካም ቢሆንም እውነታውን ግን ይሸፍናሉ : ሰዎች በሃይማኖትም ሆነ ያለሃይማኖት አደገኛ ወንጀሎችን ከፈፀሙ ነገሩ ያለው በቀጥታ አንዱ ላይ ነው ማለት አይደለም!
join
👇
https://t.me/Jonahism
5 372
ተይው -እንተወው !
..
የዘመን ቃፊሩን ማለፍ አልቻልንና ፤
ይህ ዓለም ጥበቱ አልመጠነንና ፤
ተይው እንተወው..
ውጥኑ ግብ ይሁን ጅማሬው ፍፃሜ ፤
ቅፅበቷ ሙሉ ዕድሜሽ ወቅቷ ዘላለሜ !
© ደበበ ሰይፉ 📖
5 372
ድርሰቶቼ/ጽሁፎቼ በሙሉ ስለ አንተ ነበሩ፤ እዚያ ላይ ያደረግኩት ነገር ቢኖር፣ በአንተ እቅፍ ውስጥ ሆኜ ማልቀስና ማማረር ያልቻልኩትን ነገር በጽሁፌ ማልቀስ ብቻ ነበር። ከአንተ ለመለየት ሆን ብዬ ያራዘምኩትና ያስረዘምኩት የስንብት መንገድ ነበር፤ ምንም እንኳ ይህንን እንድሰናበትህ ያስገደድከኝ አንተ ብትሆንም፣ መንገዱ ግን በእኔ ምርጫና አቅጣጫ የተመራ ነበር።ነገር ግን ይህ ሁሉ ምን ይረባል! ይህ ሊወራ የቻለው በእኔ ሕይወት ውስጥ ስለተከሰተ ብቻ ነው፤ ያለበለዚያማ ቦታ የሚሰጠው እንኳ አልነበረም። በተጨማሪም በልጅነቴ ህይወቴን እንደ ቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ ቆየት ብሎ ደግሞ እንደ ተስፋ፣ ከዚያም በኃላ ደግሞ በተደጋጋሚ እንደ ተስፋ መቁረጥ ገዝቶታል። በአንተ ቅርፅና አምሳል እየመጣ ጥቂት የማይባሉ ጥቃቅን ውሳኔዎቼን በላዬ ላይ ወስኗል። - ፍራንዝ ካፍካ ለአባቱ ከፃፈዉ ደብዳቤ ላይ የተቀነጨበ
መልካም የአባቶች ቀን!
5 372
Repost from Seblework Old Books Delivery ™📚
የካፊያ ምች 📖
ሳልላክ ተልካ እንሂድ አለቺኝ
ካላጣችው ሰዓት ከቤት አስወጣችኝ
ጥርቅም እቅፍ አድርጋ በካፊያ ሳመቺኝ
የእድሜ ልክ ልክፍቱን ያኔ አስለከፈችኝ ።
መብረቅ እየጮኸ ዝናብ እያካፋ
የእኔ ልብ በሷ የሷ በእኔ ጠፋ
የሰማዩ ባህር ቁልቁል ተንዶብን
ውሃ ጠማኝ ውሃ እየዘነበብን ።
ጠፍቼ ስመለስ ከእቅፏ ስወጣ
በርዶኝ አተኮሰኝ እቤቴ ስመጣ
እያደር አደረ ከርሞ ከረመብኝ
የዘመን ህመሜን ያን እለት ታመምኩኝ ።
አሁን አሁን ታዲያ!
ደመናው ሲጠቁር ነጎድጓድ ሲያጓራ
ነፋስ ሲያጉረመርም ክረምቱን ሲጠራ
ግንቦት ማለቂያ ላይ ይነሳል ህመሜ
ሲያቀብጠኝ በዝናብ በካፊያ ተስሜ ፣
....... ምች ተሳልሜ
ተፈሪ ዓለሙ ፣ 1974 ዓ.ም
5 372
Repost from Seblework Old Books Delivery ™📚
‹ልጄ ሆይ 'ለንስሓ ዕድሜ ስጠኝ' ብሎ መለመን ደግነት ወይም ክርስቲያንነት አይምሰልህ። ነገር ግን 'ለንስሓ ዕድሜ ስጠኝ' ብሎ መለመን 'በሕፃንነቴ እንደ ልቤ ኃጢአትን ለመሥራት ጉልበቴ ሲደክም ያንጊዜ ንስሓ እገባለሁ' ማለት ነው።
ትርጓሜውንም ገልጬ ብነግርህ 'ለንስሓ ዕድሜ ስጠኝ' ብሎ መለመን 'የዚህን ዓለም ተድላና ደስታ ፍትወትንም ሁሉ ሳልጠግበው አትግደለኝ' ማለት ነው። ....ሰውም ተወልዶ እስኪሞት ድረስ ምንም ቢሆን ከኃጢአት ንጹሕ ሆኖ አይገኝምና በየጊዜው ንስሓ ግባ እንጅ ለንስሓ የሽምግልና ጊዜ ብቻ አትጠብቅ።›
ወዳጄ ልቤና እና ሌሎቹም 📖
ክቡር ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ
@sebleold inbox 📚
5 372
በ1990ው የአለም ዋንጫ በኛ አቆጣጠር ሰኔ 26 ቀን 1982 ዓ.ም በስታዲዮ ሳን ፓውሎ አርጀንቲና ከጣሊያን ወሳኙን የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ሊያደርጉ ነው። ጣሊያን ያዘጋጀችውን የአለም ዋንጫ ማስቀረት አለባት ብለው በሀገሪቷ ከመንግስት በላይ የሚፈሩት ማፍያዎች ወስነዋል። ዳኞችም የጣሊያንን ጨዋታዎች በጥንቃቄ ነበር የሚዳኙት። ከየትኛውም ህዝብ በላይ ለብ/ቡድናቸው ሟች የሆኑት ጣሊያኖች በወቅቱ የቡድናቸው እያንዳንዱ ጨዋታዎች እህል ውሃቸው ሆኖ ነበር።
ከዚህ ጨዋታ በፊት ግን መላው የጣሊያን ህዝብ ግራ ተጋባ። ... በተለይ ናፖሊያውን "ፈጣሪ ሆይ ምን በድለንህ ነው ይህን ወሳኝ ጨዋት በዚህ መልኩ ያደረከው" አሉ። ...የኔፕልስ ከተማ ሬዲዮኖችም ብ/ቡድናቸው እየተጫወተ ያለወትሯቸው ስለጨዋታው ዝምታን መርጠዋል። ... የከተማዋ ጋዜጦችም የሚሉት ጠፍቷቸዋል። ማራዶና በነገሰባትና ያለቅጥ በተወደዳባት ጣሊያን፣ ከዛም አልፎ በተመለከባት ኔፕልስ ሁሌም ዘብ ከሚቆሙሉት ብ/ቡድናቸው ተቃራኒ ሆኖ ሊጫወት ነው። አሸናፊው የግድ መለየት ባለበት በዚህ ጨዋታ ማንም አሸነፈ ማን ጨዋታቸው ሲያልቅ ጣሊያኖችና ናፖሊያውያን ማዘናቸውና መከፋታቸው አይቀርም። ይሄን ሁሉም አውቆ ጨዋታው ሲጀመር እየተቁነጠነጠ ማየት ጀመረ።
በጨዋታው በሙሉ ደቂቃዎች አቻ ሆነው በመለያ ፍፁም ቅጣት ምቶች አርጀንቲናና ማራዶና አሸነፉ። ጣሊያንና እንደ አይናቸው ብሌን የሚያዩት ብ/ቡድናቸው መራር የሽንፈት ፅዋን ተጎነጩ። ጣሊያኖች መረራቸው። ማፍያዎች በተራቸው ግራ ተጋቡ። የጣሊያን መንግስት በዚህ ጨዋታ ውጤት ዙሪያ (ውጤቱን ባያስቀይርም) በማራዶና ዙሪያ ግን እልባት ማግኘት አለብኝ ብሎ ወሰነ።
ከጨዋታው በኋላ በማግስቱ ከለሊቱ 9 ሰዓት አካባቢ ታዲያ የማራዶና የመኖሪያ ቤቱ ስልክ ጠራ። ባለቤቱ ሄዳ አነሳችው። ከዛም ሳትዘጋው ማራዶናን ቀስቅሳ "አንተን ፈልገው ነው ተነስና አውራቸው" አለችው። "ማነው?" ሲላት "እኔንጃ ሰምቼው የማላውቀው ድምፅ ነው" ብላ መለሰችለት። ማራዶናም ወደ ስልኩ ሄዶ ወደ ጆሮው አስጠግቶ "ሄሎ" አለ። "ነገ በጠዋት ማንም ሳይነሳ ጣሊያንን ለቀህ እንድትወጣ" ብሎ አዘዘውና ስልኩ ተቋረጠ። ደዋዩ የጣሊያን ዋናው የማፍያ ቡድን የሚባለው የካሞራ ማፊያ አለቃ ነበር። ... በጣሊያንና በማራዶና መሀል የነበረው የሰመረ ጋብቻም በዚች ቅፅበት ተቋጨ።
©Firdyawkl Negussie
5 372
በ1990ው የአለም ዋንጫ በኛ አቆጣጠር ሰኔ 26 ቀን 1982 ዓ.ም በስታዲዮ ሳን ፓውሎ አርጀንቲና ከጣሊያን ወሳኙን የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ሊያደርጉ ነው። ጣሊያን ያዘጋጀችውን የአለም ዋንጫ ማስቀረት አለባት ብለው በሀገሪቷ ከመንግስት በላይ የሚፈሩት ማፍያዎች ወስነዋል። ዳኞችም የጣሊያንን ጨዋታዎች በጥንቃቄ ነበር የሚዳኙት። ከየትኛውም ህዝብ በላይ ለብ/ቡድናቸው ሟች የሆኑት ጣሊያኖች በወቅቱ የቡድናቸው እያንዳንዱ ጨዋታዎች እህል ውሃቸው ሆኖ ነበር።
ከዚህ ጨዋታ በፊት ግን መላው የጣሊያን ህዝብ ግራ ተጋባ። ... በተለይ ናፖሊያውን "ፈጣሪ ሆይ ምን በድለንህ ነው ይህን ወሳኝ ጨዋት በዚህ መልኩ ያደረከው" አሉ። ...የኔፕልስ ከተማ ሬዲዮኖችም ብ/ቡድናቸው እየተጫወተ ያለወትሯቸው ስለጨዋታው ዝምታን መርጠዋል። ... የከተማዋ ጋዜጦችም የሚሉት ጠፍቷቸዋል። ማራዶና በነገሰባትና ያለቅጥ በተወደዳባት ጣሊያን፣ ከዛም አልፎ በተመለከባት ኔፕልስ ሁሌም ዘብ ከሚቆሙሉት ብ/ቡድናቸው ተቃራኒ ሆኖ ሊጫወት ነው። አሸናፊው የግድ መለየት ባለበት በዚህ ጨዋታ ማንም አሸነፈ ማን ጨዋታቸው ሲያልቅ ጣሊያኖችና ናፖሊያውያን ማዘናቸውና መከፋታቸው አይቀርም። ይሄን ሁሉም አውቆ ጨዋታው ሲጀመር እየተቁነጠነጠ ማየት ጀመረ።
በጨዋታው በሙሉ ደቂቃዎች አቻ ሆነው በመለያ ፍፁም ቅጣት ምቶች አርጀንቲናና ማራዶና አሸነፉ። ጣሊያንና እንደ አይናቸው ብሌን የሚያዩት ብ/ቡድናቸው መራር የሽንፈት ፅዋን ተጎነጩ። ጣሊያኖች መረራቸው። ማፍያዎች በተራቸው ግራ ተጋቡ። የጣሊያን መንግስት በዚህ ጨዋታ ውጤት ዙሪያ (ውጤቱን ባያስቀይርም) በማራዶና ዙሪያ ግን እልባት ማግኘት አለብኝ ብሎ ወሰነ።
ከጨዋታው በኋላ በማግስቱ ከለሊቱ 9 ሰዓት አካባቢ ታዲያ የማራዶና የመኖሪያ ቤቱ ስልክ ጠራ። ባለቤቱ ሄዳ አነሳችው። ከዛም ሳትዘጋው ማራዶናን ቀስቅሳ "አንተን ፈልገው ነው ተነስና አውራቸው" አለችው። "ማነው?" ሲላት "እኔንጃ ሰምቼው የማላውቀው ድምፅ ነው" ብላ መለሰችለት። ማራዶናም ወደ ስልኩ ሄዶ ወደ ጆሮው አስጠግቶ "ሄሎ" አለ። "ነገ በጠዋት ማንም ሳይነሳ ጣሊያንን ለቀህ እንድትወጣ" ብሎ አዘዘውና ስልኩ ተቋረጠ። ደዋዩ የጣሊያን ዋናው የማፍያ ቡድን የሚባለው የካሞራ ማፊያ አለቃ ነበር። ... በጣሊያንና በማራዶና መሀል የነበረው የሰመረ ጋብቻም በዚች ቅፅበት ተቋጨ።
©Firdyawkl Negussie
5 372
በዓለም የፍልስፍና ታሪክ ውስጥ እንደ ጀርመናዊው ፈላስፋ ጆርጅ ዊልሄልም ፍሪድሪክ ሄጌል ከተለመደዉ ቁስዊነት እና ሃሳብዊነት ክፍፍል ተሻግሮ ዓለምን፣ ታሪክን፣ ሰውንና ፈጣሪን በአንድ ወጥ ታላቅ ስርዓት ውስጥ አጠቃልሎ ለማየት የደፈረ ፈላስፋ ጥቂት ነው። የሄጌል ፍልስፍና ዋና ማዕዘን አንድ ነው፤ዓለም ቋሚ የሆነ ቁስ ሳይሆን ዘወትር በሂደት ላይ ያለ በተቃርኖዎች ውስጥ አልፎ የሚያድግና ወደ ፍፁም ነፃነት የሚጓዝ ሁለንተናዊ ንቃተ ህሊና ነው የሚል ሲሆን። ይህንን ንቃተ ህሊና ሄጌል "ፍፁም መንፈስ( Geist)" ይለዋል።
ለሄጌል "እውነት" ማለት በአንድ ቦታ ተቀምጦ በሳይንስ የምናገኘው ቋሚ እውነታ (Static Fact) አይደለም፤ እውነት ራሱ ሂደት ነው። አንድን ዛፍ ለመረዳት ዘሩን፣ ቅጠሉንና ፍሬውን ነጣጥለን ማየት አንችልም፤ የዛፉ እውነት የሚገኘው ከዘርነት ተነስቶ በአበባነት አልፎ ወደ ፍሬነት የሚጓዝበትን አጠቃላይ ታሪክ በአንድ ላይ ሲያጠቃልል ብቻ ነው። ፍፁም መንፈስም (Geist) ልክ እንደዚሁ ነው። መጀመሪያ ላይ ራሱን የማያውቅ ንጹህ ሃሳብ የነበረው መንፈስ፣ ራሱን ለማወቅና ነፃነቱን ለመቀዳጀት ሲል ወደ ተፈጥሮና ወደ ሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ይወርዳል።
ይህ መንፈስ በታሪክ ውስጥ ወደፊት የሚገፋበት መሳሪያ "ዲያሌክቲክስ" (Dialectics) ይባላል።
ማንኛውም ነባራዊ ሁኔታ (thesis) በውስጡ ድክመትና ተቃርኖ ስላለው ራሱ የሚወልደው ተቃራኒ ሃይል (Antithesis) ይነሳበታል። ሁለቱ ሃይሎች በብርቱ ሲጋጩና ሲታገሉ የድሮውን ቅርፅ አጥፍተው ነገር ግን በውስጣቸው የነበረውን መልካም ነገር ጠብቀው ወደ ላቀ ከፍታ የሚወጡበት አዲስ ውህደት (Synthesis) ይፈጥራሉ።
ሄጌል ይህንን ሂደት (Aufhebung) ይለዋል። ታሪክ ዝም ብሎ በዘፈቀደ የሚፈስ ሳይሆን በዚህ በግጭትና በውህደት ሽክርክሪት ውስጥ ወደ ላይ እያደገ የሚሄድ የምክንያት ጉዞ ነው በማለት ይገልፃል።
ይህ ታሪካዊ ዕድገት በሰው ልጆች የእለት ተእለት ማህበራዊ ሕይወት ውስጥ እንዴት ይገለጣል? ሄጌል የሰውን ልጅ ንቃተ ህሊና የሚገነባው "የእውቅና ጥያቄ (Recognition)" ነው ይላል። አንድ ሰው ብቻውን ስላለ ብቻ ራሱን አያውቅም፤ የራሱን ማንነት ለማረጋገጥ የሌላ ሰው እውቅና ያስፈልገዋል። በመሆኑም ሁለት የሰው ልጆች ለመጀመሪያ ጊዜ ሲገናኙ ሁለቱም "እኔ የበላይ ነኝ" የሚል እውቅና ለማግኘት በሞትና በሽረት ትግል ውስጥ ይገባሉ።
እዚህ ላይ ትልቅ ፓራዶክስ ይፈጠራል።
መሞትን ፈርቶ እጅ የሰጠው ወገን "ባሪያ" ሲሆን፤ ለመሞት ያልፈራው ደግሞ "ጌታ" ይሆናል። ነገር ግን ጌታው የበላይነቱን ቢያገኝም እውነተኛ እውቅና ሊያገኝ አይችልም፤ ምክንያቱም እውቅና የሚሰጠው አካል (ባሪያው) በእርሱ ዓይን ሙሉ ሰው አይደለም። በዚያ ላይ ጌታው መስራት አቁሞ በባሪያው ላይ ጥገኛ ስለሚሆን ነፃነቱን ያጣል። ባሪያው ግን ከተፈጥሮ ጋር እየታገሰ፣ ቁስ አካልን እየቀረፀና እየሰራ ሲሄድ የራሱን ውስጣዊ አቅምና ኃይል ይረዳል፤ በዚህም እውነተኛውን ንቃተ ህሊናና ነፃነትን ጨብጦ ጌታውን ይቀድመዋል። የዚህ ስነ ልቦናዊ ትግል ፍጻሜ አንዱ ሌላውን ማሸነፉ ሳይሆን ሁለቱም እኩል ሰው መሆናቸውን ተቀባብለው "እርስ በርስ እውቅና" የሚሰጣጡበት ማህበረሰብ መፍጠር ነው።
ያ ፍፁም መንፈስ ይህንን የሰዎች የእርስ በርስ ትግልና የፍላጎት ግጭት ለራሱ ትልቅ ዓላማ ይጠቀማል። በታሪክ ውስጥ እንደ ታላቁ እስክንድር ወይም ናፖሊዮን ያሉ ታላላቅ መሪዎች ይነሳሉ። እነዚህ መሪዎች የሚንቀሳቀሱት ለራሳቸው ዝና፣ ስልጣንና የግል ጥቅም መስሎአቸው ነው። ሄጌል ግን ይህንን "የምክንያት ተንኮል (Cunning of Reason)" ይለዋል።
ያ ሁለንተናዊው መንፈስ እነዚህን መሪዎች እንደ መሳሪያ ይጠቀማቸዋል። እነርሱ የራሳቸውን ስሜት እያሳደዱ ሳያውቁት ታሪክን ወደፊት ይገፋሉ፤ የሰውን ልጅ ንቃተ ህሊና ያሳድጋሉ። በጥንቱ ምስራቅ ነፃ የነበረው አንድ ሰው(ንጉሱ) ብቻ ከነበረበት፤ በግሪክና ሮም "ጥቂት ሰዎች" ነፃ ወደሆኑበት፣ በመጨረሻም በዘመናዊው ዓለም "ሁሉም ሰው" በተፈጥሮው ነፃ መሆኑን ወደሚያውቅበት ደረጃ ታሪክ ይጓዛል።
ታሪክ ፍጻሜውን የሚያገኘው የሰው ልጅ ይህንን ነፃነቱን በተግባር የሚያረጋግጥበት ፍጹም ምክንያታዊ የሆነ የመንግስት ስርዓት ሲገነባ ነው። ለሄጌል መንግስት ማለት ዝም ብሎ ሌባ የሚጠብቅ ዘበኛ አይደለም፤ መንግስት የቤተሰብን ፍቅርና የገበያውን (ሲቪል ማህበረሰቡን) የግል መብት አጣጥሞ የያዘ፣ "የዛ ሁለንተናዊ መንፈስ በምድር ላይ መገለጫ" የሆነ ከፍተኛው የነፃነት ተቋም ነው።
ሄግል ይሄ ሁለንተናዊ መንፈስ በምድር ላይ ራሱን የሚገልፅባቸዉ መንገዶች አሉ ይላል እነሱም ጥበብ፣ሃይማኖት እና ፍልስፍና ናቸዉ።
ጥበብ ማለት መንፈሳዊ እውነትን በቁሳዊ ነገር (በቀለም፣ በድምፅ፣ በድንጋይ) መግለጽ ነው። መጀመሪያ በግብፅ ፒራሚዶች፣ ቀጥሎ በግሪክ ሀውልቶች፣በመጨረሻም በዘመናዊ ሙዚቃና ግጥም በኩል መንፈስ ውበቱን በቁስ ላይ ያሳያል።
ሃይማኖት ከጥበብ ከፍ ይላል። እውነትን በቁስ ሳይሆን "በስሜትና በውስጣዊ ምስሎች"ይገልጻል። ሄጌል ክርስትናን ከፍተኛው ሃይማኖት ይለዋል። ለምሳሌ "እግዚአብሔር ሰው ሆነ(ስጋዌ)" የሚለው አስተምህሮ ለእርሱ ረቂቁ መንፈስ ወደ ምድር ወርዶ በሰው ልጅ ታሪክና ስቃይ ውስጥ በተግባር መሳተፉን የሚያሳይ ጥልቅ ፍልስፍናዊ ምስል ነው።
የሚቀጥለዉ ፍልስፍና ሲሆን ይህ የመጨረሻውና ከፍተኛው ደረጃ ነው። በፍልስፍና ውስጥ መንፈስ ያንን በጥበብ ያየውንና በሃይማኖት ያመነበትን እውነት፣ በምስል ሳይሆን በቀጥታ "በንጹህ ሃሳብና በአመክንዮ" ይረዳዋል። በፍልስፍና አማካኝነት ያ ሁለንተናዊ መንፈስ (Geist) ራሱን ሙሉ በሙሉ አወቀ፤ ጉዞው ተጠናቀቀ ይለናል።
በቀጣይ ይህን የ ሄግል dialectical idealismን በ dialectical materialism የሚተካዉን የማርክስን ፍልስፍና እንዳስሳለን።5 372
ከብዙ መቅበዝበዝ መባከን በኋላ ፥ በንቃት ኮረብታ ተመዘግዝገን ፡ የድንቁርና እድፍ አንፀተን ቆንጆ ፁሑፍ ጽፈን ስንነሳ ለራሳችን ሞቅ ያለ ጭብጨባ እንቸራለን !
© የአባ ልጅ !
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
