fa
Feedback
ፀዊረ መስቀል

ፀዊረ መስቀል

رفتن به کانال در Telegram

የየእለቱ ወንጌል ክፍል የየበዓላቱ ሥርዓተ ዋዜማ ፤ ሥርዓተ ማኅሌት ፤ #ወረብ፤ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርበት ቻናል ነው ሼር እያደረጉ ሃይማኖታዊ ድርሻዎን ይወጡ። https://t.me/tsewire @tsewire DM @faya6

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ፀዊረ መስቀል

کانال ፀዊረ መስቀል (@tsewire) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 19 643 مشترک است و جایگاه 4 085 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 715 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 19 643 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 11 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -125 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -11 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 0.99% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 0.59% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 194 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 116 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 2 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የየእለቱ ወንጌል ክፍል የየበዓላቱ ሥርዓተ ዋዜማ ፤ ሥርዓተ ማኅሌት ፤ #ወረብ፤ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርበት ቻናል ነው ሼር እያደረጉ ሃይማኖታዊ ድርሻዎን ይወጡ። https://t.me/tsewire @tsewire DM @faya6

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 12 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

19 643
مشترکین
-1124 ساعت
+147 روز
-12530 روز
آرشیو پست ها
አመ ፭ ለሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ.mp36.55 MB

ሥርዓተ ዋይዜማ አመ ፭ ለሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ መኃትው አመ ሐሙሱ ለሐምሌ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ሃሌ ሉያ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በሀገረ ፊሊጶስ ፈጸሙ ገድሎሙ፤መጽአ አፍራሰ እሳት ወመሠጦሙ፤ወሀለዉ ሕዝብ ይኔጽሩ ዕርገቶሙ፤ተመይጠ ጴጥሮስ መንገሌሆሙ፤ወይቤሎሙ ምንተኑ ትኔጽሩነ፤ከመ ዘበኃይልነ ገበርነ፤አዕርገነ ትእዛዙ ለአምላክነ፤ዕቀቡ ትእዛዞ ለአምላክክሙ። ዋዜማ፦ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወረዱ ወቦዑ፤ሀገረ ፊልጶስ፤ቦኡ ልድያ ወበህየ ረከቡ ብእሴ፤ዘስሙ ኤንያ፤ዘ፴ ወ፰ተ ክረምተ ሐመ፤ፈወስዎ ወአሕየውዎ፤ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ። ምልጣን፦ ቦኡ ልድያ ወበህየ ረከቡ ብእሴ፤ዘስሙ ኤንያ፤ዘ፴ ወ፰ተ ክረምተ ሐመ፤ፈወስዎ ወአሕየውዎ፤ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ፤ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ አመላለስ፦ ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ/2/ ሖረ ወገብአ ምስሌሆሙ/4/ በ፭ ለእግዚአብሄር ምድር በምልዓ፦ አዕማድ እሙንቱ የማኖሙ ወድሙር ኲሉ ንዋዮሙ አዕማድ እሙንቱ የማኖሙ። እግዚብሔር ነግሰ፦ ኃረየ ፲ተ ወ፪ተ ሐዋርያተ ሤሞሙ ኖሎተ ይቤሎሙ ኢየሱስ ዘኪያክሙ ስምዓ ኪያየ ሰምዓ ስምዖ ለዘፈነወኒ። ይትባረክ እግዚአብሔር፦ አንትሙሰ ኅሩያን ፍጥረትክሙ ስብኩ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያት ሕዝብ ዘኃርየ ወጸውዐ ሎቱ ለርስቱ፤ስቡሕኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም፤ዘኪያክሙ ስምዓ ኪያየ ስምዐ ስምዖ ለዘፈነወኒ። ጸሎተ ዘሰለስቱ ደቂቅ፦ ስምዖን ጴጥሮስ ወጳውሎስ፤ቦኡ ሀገሮ ለኤንያ ወበህየ ፈወሱ ዱያነ። ሰላም፦ ስምዖን ጴጥሮስ ወጳውሎስ፤ቦኡ ልድያ ሀገሮ ለኤንያ ወበህየ ፈወሱ ዱያነ ዘስሙ ለኢየሱስ ገብሩ ሰላመ። አመላለስ፦ ወበህየ ፈወሱ ዱያነ /2/ ዘስሙ  ለኢየሱስ ገብሩ ሰላመ /4/

ያለአንተ ምንም ማድረግ ስለማይቻለኝ በሕይወቴ ጣልቃ እንድትገባ እፈልጋለሁ
ጌታ ሆይ ወደገንዳው የሚያስገባኝ ሰው የለኝም፡፡ /ዮሐ ፭፯ ሰው ስለሌለኝ ወደ አንተu ሳበኝ፡፡ ራሴን መቆጣጠር አልተቻለኝም። ጻድቅ እንድሆን የጽድቅን ሥራ እንድሠራ ጠየቅከኝ ስለዚህ ሳበኝ የሚለው የመለኮትን እርዳታ የሚፈልግ ሰው የጩኸት ድምፅu ነው:: እመኑኝ ወደ ንስሐ እንዳንመጣ አቅም ያጣነው የጸሎት አለመኖር ችግር ነው:: እግዚአብሔር ወደ ሕይወቴ ጣልቃ እንዲገባና ወደ ንስሐ እንድመጣ እፈልጋሁ፡፡ ንስሐ መግባትን ስንፈልግ በራሳችን ማስተዋልና ጉልበት ግን እንመካለን፡፡ ንስሐ መግባትን ስንፈልግ የእግዚአብሔን እርዳታ ግን አንፈልግም፡፡ ይህ የማይቻል እንደሆነ ቅዱስ ይስሐቅ ሦርያዊ እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ «ከጸሎት ሕይወት ውጭ ሌላ ወደ ንስሐu ሕይወት የሚመራ ኃይል፤ በእርሱ ውስጥ እንዳለ የሚያምን ወገን ቢኖር በሰይጣን የተታለለና የታወረ ነው» በእውነት ንስሐ ለመግባት ከፈለግክ ራስህን በጸሎት ውስጥ አድርገህ ጌታን ሳበኝ ከአንተ ኋላ እንሮጣለንu ልትለው ይገባል፡፡ በራሴ ፈቃድ ውስጥ አትተወኝ፡፡ የኔ ደካማ ባሕርይ ወደ አንተ ሊያቀርበኝ አልተቻለውምና ሳበኝ። ከሰዎች መካከል አንዱ ተይዞ ነበር፡፡u በገመድ ታስሮ ቢላዋ ተዘጋጅቶለት ነበር፡፡ መሥዋዕትም ሆኖ ሊሠዋ ነበር፡፡ እርሱም የአብርሃም ልጅ ይስሐቅ ነው:: ራሱን ማዳን እንደምን ይቻለዋል? ሳበኝ ከኋላህ እንሮጣለንy ከማለት ውጭ ሌላ ሊያድነው የሚቻለውu አልነበረም:: ጌታ ከመሠዊያው ጫፍ ሳበው ጌታ ባይስበው በሕይወትም እንዲቆይ ባይፈቅድለት ኑሮ ራሱን ማዳን ባልተቻለውም ነበር፡፡                                                    🙏💒💙አቡነ ሺኖዳ፫

🎯 ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ? ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ዘማሪ አቤል መክብብ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎤 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 🎤 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 🎚 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 🎚 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ 🎤 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇 🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧

1/11/2018                       ዮሐንስ 20:19-ፍጻሜ      ያም ከሳምንቱ የመጀመሪያው ቀን በመሸ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ አይሁድን ስለፈሩ ተሰብስበው የነበሩበት ቤት ደጁ ተቈልፎ ሳለ ጌታችን ኢየሱስ መጥቶ በመካከላቸው ቆመና፥ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” አላቸው። ይህንም ብሎ እጆቹንና ጎኑን አሳያቸው፤ ደቀ መዛሙርቱም ጌታችንን ባዩት ጊዜ ደስ አላቸው። ጌታችን ኢየሱስም ዳግመኛ እንዲህ አላቸው፥ “ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ አብ እኔን እንደ ላከኝ እንዲሁ እኔ እናንተን እልካችችኋለሁ።” ይህንም ብሎ እፍ አለባቸው፤ እንዲህም አላቸው፥ “መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ። ኀጢአታቸውን ይቅር ያላችሁላቸው ይሰረይላቸዋል፤ ይቅር ያላላችኋቸው ግን አይሰረይላቸውም።” ጌታችን ኢየሱስ በመጣ ጊዜ ዲዲሞስ የሚሉት ከዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ ቶማስ ከደቀ መዛሙርቱ ፤ሌሎች ደቀ መዛሙርትም፥ “ጌታችንን አየነው” አሉት፤ እርሱ ግን፥ “የችንካሩን ምልክት በእጁ ካላየሁ፥ ጣቴንም ወደ ተቸነከረበት ካልጨመርሁ፥ እጄንም ወደ ጎኑ ካላገባሁ አላምንም” አላቸው። ከስምንት ቀን በኋላም ዳግመኛ ደቀ መዛሙርቱ በውስጡ ሳሉ፥ ቶማስም አብሮአቸው ሳለ በሩ እንደ ተዘጋ ጌታችን ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆመና፥ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” አላቸው። ከዚህም በኋላ ቶማስን፥ “ጣትህን ወዲህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና ወደ ጎኔ አግባ፤ እመን እንጂ ተጠራ ጠራጣሪ አትሁን” አለው። ቶማስም፥ “ጌታዬ አምላኬም” ብሎ መለሰ። ጌታችን ኢየሱስም ስለአየኸኝ አመንህን? ብፁዓንስ ሳያዩ የሚያምኑ ናቸው” አለው። ጌታችን ኢየሱስም በዚህ በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ብዙ ሌላ ተአምራት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ። ነገር ግን ይህ የተጻፈ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እናንተ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ የዘለዓለም ሕይወትን ታገኙ ዘንድ ነው.....
1 ጢሞቴዎስ 5:1-18 1 ጴጥሮስ 3:1-7 ሐዋ፡ሥራ 9:36-ፍጻሜ
ቅዳሴ ዘኤጲፋንዮስ (ዐቢይ)
ምስባክ                          መዝሙር 18:12-13
ለስሒት መኑ ይሌብዋ አምኅቡዓትየ አንጽሐኒ ወእምነኪር መሐኮ ለገብርከ
ትርጉም
ስሕተትን ማን ያስተውላታል? ከተሰወረ ኀጢአቴ አንጻኝ ከልዩ ሰው ባሪያህን አድነው

ሥርዓተ ማኅሌት አመ ፩  ለሐምሌ ልደታ ለማርያም    ሥርዓተ ነግሥ፦ ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ንዌድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤በአሐቲ ቃል። መልክዐ ሥላሴ ፦ ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ ለሣህል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል። ዚቅ፦ ሰዓሊ ለነ ማርያም ኀበ ወልድኪ፤ ከመ ያዝንም ለነ ዝናመ ምሕረት እምነቅዓ ሕይወት፤ ዘአፀርዎ ሰቃልያን፤ በጎልጎታ መካን፤ ስትዪ ሕዝበ ክርስቲያን፤ ስቴ ዘበአማን። ዓዲ ዚቅ፦ ስብሐት ለአብ ለአኃዜ ኲሉ ዓለም፤ ስብሐት ለወልድ ለገባሬ ኲሉ ዓለም፤ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ለዘያርኁ ክረምተ በበዓመት። ወረብ ፦ ስብሐት ለአብ ለአኃዜ ኲሉ ዓለም ስብሐት ለወልድ ለገባሬ ኲሉ ዓለም/፪/ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ለዘያርኁ ክረምተ በበዓመት/፪/ ዘጣዕሙ፦ ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ህይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኰት ስሙ። ዚቅ፦ ምንተ እንከ ዕብል በእንተ ማርያም፤ መሠረተ ጽድቅ ኀደረ ላዕሌሃ፤ ወአዘዘ ደመና በላዕሉ። መልክአ ማርያም ፦ ሰላም ዕብል ለዘዚአኪ ሰኰና፤ ዘኢድኅፃ በውስተ ፍና፤ ማርያም ድንግል ትእምርተ ኪዳን ቀስተ ደመና፤ አምዕዝኒ በዕፍረትኪ ወጸግውኒ ጥዒና፤ በከመ ትገብር እም ለንዑስ ሕፃና። ዚቅ፦ እሰይም ቀስትየ በውስተ ደመና፤ እዜከር ኪዳንየ ይቤ እግዚአብሔር፤ ዘመሐልኩ ላቲ ለማርያም እምየ፤ እሁብ ዘርዓ ወማዕረረ፤ በረከተ ፍሬሃ ለምድር። ወረብ፦ እዜከር ኪዳንየ ዘመሐልኩ ላቲ ለማርያም ይቤ እግዚአብሔር/፪/ እሰይም "ቀስትየ በውስተ ደመና" /፪/እሰይም/፪/ መልክአ ማርያም፦ ሰላም ለቆምኪ በቀልተ ዘተመሰለ፤ ኃበ ሙኃዘ ማይ ዘበቈለ፤ ማርያም ድንግል እስእለኪ ስኢለ፤ ኢይረድ ታሕቲተ ምጥቅኒ ላዕለ፤ ኢረከብኩ በርኅራኄ ከማኪ ዘብዕለ። ዚቅ፦ ሃሌ ሉያ ዕፅ ዘበቈለት ኀበ ሙኃዘ ማይ፤ ፍሬሃ ሠናይ አዳም ለርእይ፤ ማርያም ታዕካ በምድር፤ ወታዕካ በሰማይ። መልክአ ማርያም፦ በዝንቱ ቃለ ማኅሌት ወበዝንቱ ይባቤ፤ ለዘይስዕለኪ ብእሲ ጊዜ ረከቦ ምንዳቤ፤ ብጽሒ ፍጡነ ትሰጠዊዮ ዘይቤ፤ ማርያም ዕንቊየ ክርስቲሎቤ ወምዕዝተ ምግባር እምከርቤ፤ ዘጸገየ ማሕጸንኪ አፈወ ነባቤ። ዚቅ፦ ሰአሊ ለነ ማርያም፤ ንጽሕት በድንግልና አልባቲ ሙስና፤ ፀምር ፀዓዳ ዕራቊ ደመና፤ ሱራፌል ወኪሩቤል ይኬልልዋ። ምልጣን፦ በብሩህ ደመና ዘከለላ፤ በሐኪ ማርያም እሞሙ ለሰማዕት፤ ወእኅቶሙ ለመላእክት፤ እንተ እምአፉሃ ይወጽእ ቃለ ጽድቅ። አመላለስ፦ እንተ እምአፉሃ ይወጽእ/፪/ ይወጽእ ቃለ ጽድቅ/፬/ ወረብ፦ በብሩህ ደመና "ዘከለላ"/፪/በብሩህ ደመና/፪ በሐኪ ማርያም እሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት/፪/ እስመ ለዓለም፦ ደመና ቀሊል ዘትፀውር መና፤ ማርያም ይእቲ ንጽሕት በድንግልና፤ እስመ እምከርሣ ሠረፀ ፍሬ ስብሐት፤ ዘበትርጓሜሁ እግዚአብሔር ምስሌነ። ዓዲ እስመ ለዓለም፦ ቅንዑ ለእንተ ተዓቢ ጸጋ መድኃኒት ለነፍስ ወሥጋ፤ እስመ ርቱዓት ፍናዊሃ ጻድቃን የሐውርዎን ወኃጥአን ይስዕንዎን፤ ዘእንበለ ትብጻሕ ግብተ አሠንዮ ፍኖተ፤ ይፈኑ ለክሙ እመቅደሱ ረድኤተ፤ መድኃኒተ መቤዛዊተ እሞ ቅድስተ። ወረብ፦ ቅንዑ ለእንተ ተዓቢ ጸጋ መድኃኒት ለነፍስ ወሥጋ ማርያም ድንግል/፪/ እስመ ርቱዓት ፍናዊሃ ጻድቃን የሐውርዎን ወኃጥአን ይስዕንዎን/፪/  ቅንዋት፦ ሤመክሙ እግዚአብሔር ጳጳሳተ ቀሳውስተ ወዲያቆናተ፤ ከመ ትርእዩ ቤተ ክርስቲያኑ እንተ አጥረያ በደሙ፤ ወአተባ በዕፀ መስቀሉ። ዓዲ ቅንዋት፦ ክብሮሙ ለቅዱሳን ሞገሶሙ ለጻድቃን፤ መርሖሙ ለዕውራን ዝንቱ ውእቱ መስቀል፤ እንስሳ ገዳምኒ አዕዋፈ ሰማይኒ ያንቀዓድዉ ኀቤከ፤ አምላክ መስተመይጥ፤ ያፀግብ ነፍሰ ነዳያን ያከርም በበዓመት፤ ለዘበእንቲአነ ውስተ ማኅፀና ለማርያም ተሠወርከ፤ ወበደመናትኒ ሰማየ ዘከለልከ፤ ወኵሉ ቀሊል በኀቤከ። እስመ ለዓለም ዘሰንበት  የማነ ብርሃን ኀደረ ኀበ ማርያም ድንግል ጥዕምት በቃላ ወሠናይት በምግባራ፤ እሞሙ ለሰማዕት፤ ወእኅቶሙ ለመላእክት፤ እንተ ተሰምየት ሰንበተ ክርስቲያን ተስፋ ቅቡፃን መድኃኒተ ኮነት ለኵሉ ዓለም፡፡

💠የንስሐ ◇የሽብሻቦ ◇ወረብ ◇የቅዱሳን እንዲሁም የመላእክት መዝሙር የምትፈልጉ ከሆነ አሁኑኑ JOIN በሉት ይሄ ቻናል ምርጥ ምርጥ መዝሙሮችን በጥራትና በፍጥነት ያሳያል። 𝐉𝐨𝐢𝐧👇👇👇 h
💠የንስሐ ◇የሽብሻቦ ◇ወረብ ◇የቅዱሳን እንዲሁም የመላእክት መዝሙር የምትፈልጉ ከሆነ አሁኑኑ JOIN  በሉት  ይሄ ቻናል ምርጥ ምርጥ መዝሙሮችን በጥራትና በፍጥነት ያሳያል። 𝐉𝐨𝐢𝐧👇👇👇 https://t.me/addlist/sZA2UFcsVPplMjI0

[እንኳን ለሠኔ 30 የመጥምቁ ዮሐንስ ልደት አደረሳችኹ] ✍በመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ [መጥምቁ ዮሐንስ በእናቱ ማሕፀን ስላቀረበው ስግደት ያዕቆብ ዘሥሩግ ያቀረበው ቅኔያዊ ውዳሴ] ♥ የእነዚኽ ዘመዳሞች (የኤልሳቤጥና የእመቤታችንን) መልካም ገጠመኝ አኹንም ያስደንቀኛል፤ ውበቱን እገልጥ ዘንድም አንድ ዐሳብ ይጎነትለኛል፡፡ ብላቴናዪቱ (እመቤታችን) እና አረጋዪቱ (ኤልሳቤጥ) አንድ አስደናቂ ታሪክ አስተምረውኛል፤ እየተደነቅኊ ስለ ርሱ እናገር ዘንድም ፍቅር ይወተውተኛል፡፡ ♥ ድንግሊቱ በፍቅርዋ መካኒቱም በደስታዋ፤ ስለ ኹለታቸውም እሰብክ ዘንድ ፈልገውብኛል፡፡ ርስ በርስ የተያዩት አጽናፋት በተከሥቷቸው እንደሚተያዩት ነበር፣ የየራሳቸው የጊዜ ኹኔታ ቁልጭ ብሎ እንደሚታይባቸው እንደ ምሥራቅ እና እንደ ምዕራብ ናቸው፡፡ ♥ አረጋዪቱ (ኤልሳቤጥ) ምሽት የሚታይበትን፤ በዕድሜው ብዛት (በርጅናው) ብርሃንን የሚሸፍነውንና የሚቀብረውን አጽናፍ ትመስላለች (ዮሐ ፭፥፴፭)፡፡ ብላቴናዪቱም (እመቤታችን) ቀኑን በዕቅፏ ተሸክማ ወደ ምድር የምታመጣውንና፤ የንጋት እናት የኾነችውን ምሥራቅን ትመስላለች (ሕዝ ፵፬፥፪)፡፡ ♥ በወጣትነት እና በእርጅና ጊዜ የመደነቅ ስሜት ይበዛ ዘንድ ንጋት እና ምሽት የሚተያዩት በፍቅር ነው፡፡ ታላቁን የጽድቅ ፀሓይ (ጌታን) የምትሸከመው ንጋት (እመቤታችን) (ሚልክ ፬፥፪)፣ እና ብርሃንን (ጌታን) የሚያበሥረው ኮከብ (ዮሐንስ) የሚወጣባት ምሽት፡፡፡ ♥ ታላቁ ንጉሥ በብላቴናዪቱ (በእመቤታችን) ዐድሮ ዘውዶችን ያበጃል፣ አረጋዪቱ (ኤልሳቤጥ) መንግሥቱን የሚያውጀውን አገልጋይ ትሸከማለች፡፡ በድንግልና የፍጥረታት ጌታ ይከበራል፤ በመካንነት የሌዋውያን (ወንድ) ልጅ ከፍ ይደረጋል፡፡ ♥ ብላቴናዪቱ (እመቤታችን) አዳምን የፈጠረው ቀዳማዊዉን ሕፃን ትሸከማለች፤ አረጋዪቱ (ኤልሳቤጥ) ዛሬ በጋብቻ ውስጥ የተፈጠረውን ሕፃን ትሸከማለች (ሉቃ ፩፥፳፬-፳፭)፡፡ የይሁዳ ብላቴና ውስጥ ያዕቆብ ስለ ርሱ የጻፈው ያ የአንበሳ ደቦል አለ (ዘፍ ፵፱፥፱)፤ በሌዋዊቱ ውስጥ ደግሞ ጥምቀትን የመሠረታት ካህን (ሉቃ ፫፥፫)፡፡ ♥ ከአረጋዪቱ (ኤልሳቤጥ) ጋር ስለዚኽ ዐዲስ ፅንስ ሐሤት ታደርግ ዘንድ፤ ድንግል በቅድስና ልቃ እና ተመልታ መጣች (ሉቃ ፩፥፴፱)፡፡ በረከትን (ጸጋን) የተመላችው (እመቤታችን) እና የሌዋውያን ሴት ልጅ የኾነችው (ኤልሳቤጥ)፤ እንዲኹም ምድር በመላ የበለጸገበት የከበረ ሀብት የመሉባቸው ኹለቱ ጀልባዎች ርስ በርስ ተገናኙ (ተያዩ)፡፡ ኹለት ወላዶች፡- አንደኛዋ ተበሣሪና አንደኛዋ አብሣሪ ኾና፣ የዚያኑ የአንዱን (ተመሳሳዩን) ለዓለም ኹሉ የኾነ የመዳን መልእክት ይዛ፡፡ ♥ ብላቴናዪቱ (እመቤታችን) ጐበኘቻት፣ እና አንጸባራቂ በኾነ ሰላምታ ተናገረቻት፤ ወዲያውም በርሷ (በኤልሳቤጥ) ውስጥ ተሸፍኖ ያለው ሕፃን አውቆ በደስታ መዝለል ዠመረ (ሉቃ ፩፥፵፩)፡፡ ማርያም ሰላምን መናገርዋ ያማረ ነበረ፣ በቅርብ እና በሩቅ ላሉት ሰላምን ዘርታለችና (ሉቃ ፩፥፵)፡፡ ርሷ ለሰው ዘር በሙሉ የኾነ ሰላም እንደመላበት ክቡር ስጦታ ነበረች፣ በጠላትነት ለነበሩት የሚኾን ታላቅ ሰላም (ወሀቤ ሰላም ጌታ) በርሷ ውስጥ ተሰውሮ ነበርና፡፡ ♥ ርሷ ራሷ ከላይ ሰላምን እንደተቀበለች፣ እንዲኹ ደግሞ ለዓለም ኹሉ ሰላምን ሰጠች (ሉቃ ፪፥፲፬)፡፡ በርሷ አፍ ሰላም በብዛት ተትረፍርፎ ይነገር ነበር፣ ይኽች ቡርክት የኾነች እንዲኽ ሰላምን ታውጅ ዘንድ የተገባት ነበር፡፡ ሰላም በውስጧ (በማሕፀኗ) ነበረና በከንፈሯ ሰላምን ሰጠች፣ ይኽነን የሰማው ሕፃንም በደስታ ይፈነድቅ ዠመር (ሉቃ ፩፥፵፩)፡፡ ♥ ገና ሳያየው በፊት ያውቀው እንደነበር በማሳየቱ፣ ሲያየውና “ይኽ ርሱ ነው” ብሎ ሲናገር ነገሩን የሚጠራጠረው አይኖርም (ዮሐ ፩፥፳፱-፴)፡፡ ገና ሳይወለድ ርሱን (ጌታን) ለዓለም አስተዋወቀው፣ ከተወለደ በኋላ ርሱን ሲያውጀው ማንም ከምስክርነቱ እንዳይሸሽ፡፡ በተፈጥሮ ላይ ጌታ የኾነው በብላቴናዪቱ ማደሩ ይገለጥ ዘንድ፣ ተፈጥሮን በማሸነፍ ከተፈጥሮ ውጪ (ዮሐንስ) ስለ ወልድ መሰከረ፡፡ ♥ ስለ ወልድ የኾኑት ነገሮች ኹሉ ለመግለጽ እጅግ ከባድ ናቸው፣ በእምነት ዦሮ ካልኾነም በቀር አይሰሙም፡፡ እነዚኽ ነገሮች ኹሉ ዐዲስ ነበሩና ሰው አልተረዳቸውም ነበር፤ ፍቅር ባለው ሰው በአድናቆት ካልኾነ በቀርም አይታዩም፡፡ለማርያም አድናቆት ለኤልሳቤጥም ታላቅ ሙገሳ ይገባል፣ ማስተዋል ለሚችል ሰው በኹለቱም ውስጥ ዐዳዲስ መገለጦች አሉባቸውና፡፡ ♥ ስለኹለቱም ለመናገር ቃላት በቂዎች አይደሉም፣ አንደበትም (ንግግርም) ዝም ይላል፤ ከአድናቆት የተነሣ ዝምታ ንግግርን ይውጠዋል፡፡ ቃላት ስለማንኛዪቱ ለመናገር ይበቃሉ?፣ እነሆ ኹለቱም ከንግግር (ከአንደበት ገለጻ) በላይ ናቸውና፡፡ ማርያምን በቀረብናት ጊዜ አንደበት በዝምታ ይዘጋል፣ ምክንያቱም የድንግልናን ማስረገጫዎች (ምልክቶች) በርሱም ያደረውን ሕፃን ይመለከታልና፡፡ ወደ ኤልሳቤጥም ስንመጣ ትንታኔ ይከዳናል፣ ከርሷ ማሕፀን ውስጥ አስደናቂውን ብሥራት ይሰማልና፡፡ ♥ ድንግሊቱ ፀንሳለችና እነሆ የመካኒቱም ልጅ በደስታ ይዘልላል፤ ስለ ታላላቆቹ ሕፃናት ዕጥፍ ድርብ መደነቅ ይይዘናል፤ ኧረ በማንኛቸው እንደመም (እንደነቅ)? አንደኛዪቱ (እመቤታችን) ያላገባች ኾና ሳለች ወንድ ሳያውቃት ፍሬ በውስጧ አለ፤ በሌላኛዪቱም (በኤልሳቤጥ) ማሕፀን ውስጥ ገና ያልተወለደ ሕፃን በደስታ ይዘልላል፡፡ ♥ ማንኛዪቱን እናድንቅ፡- ልጅዋ የምሥራች ነጋሪ የኾነውን በዕድሜ የገፋችውን ሴትን፣ ወይንስ ድንግል ኾና ግን ደግሞ ሕፃን በውስጧ የተሸከመችዪቱን ብላቴና? ይኽችኛዪቱ (እመቤታችን) ወንድን ፈጽማ አታውቅም ግን ደግሞ ማሕፀኗ ሙሉ ነው (ማቴ ፩፥፲፰)፣ ያቺኛዪቱም (ኤልሳቤጥ) ልጇ ገና ሳይወለድ በፊት መንገድ ያዘጋጃል (ሉቃ ፩፥፵፬)፡፡ ያለጋብቻ ውሕደት የኾነችው ርሷ (እመቤታችን) ከንፁሕ ፅንሷ የተነሣ እጅግ ታስደንቃለች፣ ያልወለደችዪቱም (ኤልሳቤጥ) ደግሞ ልጇ ብሥራትን ለማብሠር ይላወሳል (ይዘላል)፡፡ [በእናቱ ማሕፀን በደስታ የዘለለው የቅዱስ ዮሐንስ በረከቱ ይደርብን]

Story

ሕፃኑም ከተወለደ በኋላ አባቱ ካህኑ ዘካርያስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ እንደዚህ አለ፦ ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤ እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤ ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፤ ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል። (ሉቃ ፩፥፸፮-፸፱) በዚያም ዘመን ሄሮድስ የአምላካችን፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መወለድ ከሰብአ ሰገል ሲሰማ መንግሥቴን ይወስድብኛል ብሎ በመፍራቱ የቤተልሔም ሕፃናትን መግደል የመጀመርያ ውሳኔው ሆነ። (ማቴ. ፪፥፩-፲፮) ቅድስት ኤልሳቤጥም ልጇን ዮሐንስን ይዛ ወደ ምድረ በዳ ተሰደደች። የአዋጅ ነጋሪው ቃል ተብሎ የተነገረለት ቅዱስ ዮሐንስ ጊዜው ሲደርስ ከነበረበት በረሐ ድምፁን እያሰማ መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ! እያለ እየሰበከ በዮርዳኖስ ዙሪያ ወዳለው አገር ሁሉ ወጣ። (ሉቃ. ፫፥፫-፮) ። በስብከቱም እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ፤ መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ኹሉ ይቈረጣል፤ ወደ እሳትም ይጣላል፤ ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው ያካፍል፤ ምግብም ያለው እንዲሁ ያድርግ፤ ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ፤ በማንም ላይ ግፍ አትሥሩ፤ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፤ ደመወዛችሁም ይብቃችሁ፤ ይል ነበር። (ሉቃ. ፫፥፯-፲፬) ። የትሕትና አባት የሆነው ቅዱስ ዮሐንስ ጌታ ሊጠመቅ ወደ እርሱ ሲመጣ እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል፤ አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? በማለት የጌታችንን አምላክነት ፍጹም በሆነ ትሕትና ተናግሯል (ማቴ. ፫፥፲፬) ። ብዙ ተከታይ የነበረውና በስብከቱ የብዙ ሰዎችን ቀልብ የገዛው ቅዱስ ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲናገር ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው፤ ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል። እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ። እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል። (ዮሐ ፫፥፳-፱-፴) በማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ክብር የሚገባውና ከሁሉ የበለጠ ሙሽራ መሆኑን ተናግሯል። መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ካህን፣ መምህር፣ ሐዋርያ፣ ባሕታዊ፣ ነቢይ፣ ጻድቅ እና ሰማዕት ነው። ሊቁም ከሰማይ መላእክት ወገንም ሆነ በምድር ካሉ ቅዱሳን፣ ነቢያት፣ ካህናት፣ መምህራንና ሐዋርያት መካከል ማንም እንደ ቅዱስ ዮሐንስ መለኮትን ለማጥመቅ የተመረጠ አለመኖሩን በመጥቀስ ዮሐንስ ሆይ ራጉኤል በትጋቱ፣ ኢዮብም በጽድቁ ቢመኙም ሆነ ቢጨነቁ እንደ አንተ የሚነድ እሳትን (መለኮትን) ሊያጠምቁ አልተቻላቸውም ሲል ተናግሮለታል። (መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ) ። መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የጻድቃን የሰማዕታት በኩር፣ የሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያው ሐዋርያ፣ መምህር፣ ሰማዕት፣ የብሉይ ኪዳን ነቢያትም መጨረሻ ነውና፤ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል እንዳሉ፥ እርሱ ግን ለመጀመሪያ ጊዜ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ (ዮሐ 1፥29) ብሎ ስብከት የጀመረው እርሱ ነውና፣ ገና በማህፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስን የተቀበለና ለጌታችን የመጀመሪያውን የምስጋናና የስግደት መብዐ ያቀረበ፣ የሐዲስ ኪዳንን ብሥራት ከሰው ልጆች ሁሉ በፊት ያወቀ፣ ስለሆነ፣ የብሉይ (የአሮጌው) ዘመን ፍፃሜ ማግኝቱንና የሀዲስ ኪዳንን መምጣት የመጀመሪያ የብሥራት አዋጅ ነጋሪ በመሆኑ፤ የቅድስት ቤተክርስቲያናችን ሊቃውንትና አባቶች ምሳሌና ምስጢርን በማስማማት ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከብሉይ ወደ ሐዲስ፣ ከዓመተ ኩነኔ ወደ ዓመተ ምሕረት የተሸጋገርንበትን እንድናስብ ቤተክርስቲያን ይህቺን ቀን በሥሙ ሰይማ ዓመታትን ለሚያቀዳጅ እግዚአብሔር ምስጋናን ታቀርባለች። ስለዚህ የአዲስቱ ዓመት የመጅመሪያዋ አዲሲቱ ቀን ቅዱስ ዮሐንስ ትባላላች። በመሆኑም በየዓመቱ አዲስ ዓመትን ስንቀበል በተለየ ተስፋና ደስታ ነው፤ የጎመን ምንቸት ውጣ የገንፎ ምንቸት ግባ እንዲሉ። ስምዑ አዝማዲሃ ወሰብአ ቤታ እስመ አዕበየ እግዚአብሔር ሣህሉ ላዕሌሃ ወተፈሦሑ ፍስሓ ፈድፋደ ወፈቀዱ ይስምይዎ በስመ አቡሁ ዘካሪያስ ወትቤ እሙ ዮሐንስሃ ይሰመይ ሰኔ ፴ ቅዱስ ዮሐንስ የተወለደበትን ቀን ቤተ ክርስቲያን በቅዳሴ እና ታቦት በማውጣት ታከብራለች። በጌታ የተወደደ እና የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ሆኖ አምላክን ለማጥመቅ የታደለው የቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት አይለየን፣ መንፈስ ቅዱስን ተሞልተው ድንቅ ያደረጉና ሕያው ምስክርነትን የሰጡት የመላው ቤተሰብ በረከትም ከሁላችን ጋር ይሁን። ሰላም ለጽንሰትከ እንበለ ሀጢያት ወግማኔ፤ ወለልደትከ ሰላም አመ ሠላሳሁ ለሰኔ፤ ዮሐንስ ዘኮንከ ደመና ሰማይ ኮናኔ ፤ አዝንም መና አዕምሮ ወኅብስተ ጥበብ መድሀኔ፤ ኀበ ሕዝበ ልብየ ኀበሩ ወገብሩ ኩርጓዴ፤ (መልክዐ ዮሐንስ መጥምቅ) ሰላም ለከናፍሪከ ነቢበ ከንቱ ዘኢኀሠሣ፤ ወለአፉከ ሰላም ዘኢጥዕመ እክለ አበሳ፤ ዮሐንስ ሕጻን ለእምከ ውሣጤ ከርሳ፤ እፎ አንፈርዓጽከ እንዘ ትሰግድ ለንግሳ፤ አመ ሐወጸትከ ማርያም አምላከ ፀኒሳ ሰላም ለልደትከ ከመ ገብርኤል አደሞ፤ ፮ተ አውራኅ ለልደተ ክርስቶስ ዘይቀድሞ፤ ዮሐንስ ምዑዝ እምስሂን ወቀናንሞ፤ ለለነበብኩ በጽሒቅ ለመልክእከ ሰላሞ፤ ከመ ከላስስት በሕፅንየ ሢሞ። ( አርኬ ዘሰኔ 30 ) መልካም በዓል ‼️

መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ሰላም ለልደትከ ከመ ገብርኤል ክላስስት ስድስተ አውርኃ ለልደተ ክርስቶስ እንተ ቀደሞ፤ ዮሐንስ ስኂን ወምዑዝ እምቀናንሞ፤ ለለነበብኩ በጽሒቅ ለመልክዕከ ሰላሞ፤ ከመ ክላስስት በሕጽንከ ሴሞ ስምዑ አዝማዲሃ ወሰብአ ቤታ እስመ አዕበየ እግዚአብሔር ሣህሉ ላዕሌሃ ወተፈሦሑ ፍስሓ ፈድፋደ ወፈቀዱ ይስምይዎ በስመ አቡሁ ዘካሪያስ ወትቤ እሙ ዮሐንስሃ ይሰመይ። (ምልጣን በእንተ ልደቱ ለዮሐንስ መጥምቅ) ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ በቀዳማዊ ምዕራፉ እንዲህ ይላል ፦ « ወይቤሎ መልአክ ኢትፍራህ ዘካርያስ እስመ ተሰምዐ ጸሎትከ ወብእሲትከኒ ኤልሳቤጥ ትወልድ ለከ ወልደ ወትሰምዮ ስሞ ዮሐንስ። መልአኩም እንዲህ አለው። ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ወይከውነከ ትፍሥሕተ ወሐሴተ ወብዙኃን ይትፌስሑ በልደቱ። እስመ ዐቢየ ይከውን ውእቱ በቅድመ እግዚአብሔር ወኢይስቲ ወይነ ወሜስ ወይመልእ ላዕሌሁ መንፈስ ቅዱስ እምከርሠ እሙ። ወለብዙኃን እምደቂቀ እስራኤል ይመይጦሙ ሀበ እግዚአብሔር አምላኮሙ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤ ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው ይመልሳል። ወወእቱ የሐውር ቅድሜሁ በመንፈስ ቅዱስ ወበኀይለ ኤልያስ ከመ ይሚጥ ልበ አበው ኀበ ውሉድ ወለከሓዲያን ውስተ ሕሊና ጻድቃን ከመ ይሥራዕ ሕዝበ ዘይደልው ለእግዚአብሔር። እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ፥ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል። » (ሉቃስ ፩፥፲፫ —፲፯) « ወቦአት ቤተ ዘካርያስ ወአምኅታ ኤልሳቤጥ። ወሶበ ሰምዐታ ኤልሳቤጥ ቃላ ለማርያም እንዘ ትትአምኃ አንፈርዐጸ እጓለ በውስተ ከርሣ። ወመልአ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ኤልሳቤጥ። ማርያምም በዚያ ወራት ተነሥታ ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ከተማ ፈጥና ወጣች፥ ወደ ዘካርያስም ቤት ገብታ ኤልሳቤጥን ተሳለመቻት። ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥ ወከልሐት በዐቢይ ቃል ወትቤ ቡርክት አንቲ እምአንስት ወቡሩክ ፍሬ ከርሥኪ። ወምንትኑ አነ ከመ ትመጽኢ እሙ ለእግዚእየ ኅቤየ። እስመ ናሁ ሶበ ሰማዕኩ ቃለኪ እንዘ ትትእምኅኒ አንፈርዐጸ እጓል በውስተ ከርሥየ በፍስሓ ወበሐሤት። ወብፅዕት አንቲ እንተ ተእምኒ ከመ ይከውን ቃለ ዘነገሩኪ እምኅበ እግዚአብሔር። በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች። አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው። የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና። ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት። » (ሉቃስ ፩፥ ፵ —፵፭ ) ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት። (ሉቃ ፩፥፵፩) አባቱ ዘካርያስም መንፈስ ቅዱስ ሞላበትና ትንቢት ተናገረ። (ሉቃ ፩፥፷፯) ቅዱስ ማርቆስም ወንጌሉን ሲጽፍ «የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ እነሆ መንገድህን የሚጠርግ መልእከተኛዬን በፊትህ እልካለሁ የጌታን መንገድ አዘጋጅ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ» ተብሎ በኢሳይያስ እንደ ተነገረ የነቢዩ ዘካርያስ ልጅ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዘመነ ብሉይ መጨረሻና በዘመነ ሐዲስ መጀመሪያ ላይ ተነሥቶ «መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ» እያለ ስለ ክርስቶስ አዳኝነት እየመሰከረ በምድረ በዳ የንስሐን ጥምቀት እያጠመቀ ለኃጢአት ሥርየት እየሰበከ መጣ ብሎ በዘመነ ወንጌል የመጀመሪያ ምዕራፍ ገልጾታል፡፡ /ማር.1.40፤ኢሳ.40.3-4/፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የዚህን ታላቅ ቤተሰብ ታሪክ በሉቃስ ወንጌል ላይ ካህኑ ዘካርያስ እና ከካህኑ ከአሮን ወገን የሆነች ኤልሳቤጥ ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ በማለት ይገልፃል። የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት ታሪክም እንዲህ በሚለው በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ይጀምራል፦ ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤ ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው ይመልሳል። እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ፥ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል። (ሉቃ ፩፥፲፭-፲፯) ዮሐንስ ማለት “እግዚአብሔር ጸጋ ነው” ማለት ነው፡፡ ትርጓሜ ወንጌልም መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን ፍሥሐ ወሐሴት (ተድላና ደስታ) ይለዋል፤ ወላጆቹ በእርሱ መወለድ ተደስተዋልና (ሉቃ.፩፥፲፬)፡፡ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ፣ በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት፣ በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ፣ እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ፣ የጌታችንን መንገድ የጠረገ፣ ጌታውን ያጠመቀና፣ ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ባለ ታሪክ ነው። ስለዚሕም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ዮሐንስን ነቢይ፣ ሐዋርያ፣ ሰማዕት፣ ጻድቅ፣ ካሕን፣ ባሕታዊ/ገዳማዊ፣ መጥምቀ መለኮት፣ ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ)፣ ድንግል፣ ተንከተም (የብሉይና የሐዲስ መገናኛ ድልድይ)፣ ቃለ አዋዲ (አዋጅ ነጋሪ)፣ መምሕር ወመገሥጽ፣ ዘየዐቢ እምኩሉ (ከሁሉ የሚበልጥ) ብላ ታከብረዋለች። የእግዚአብሔርን ትእዛዝና ሕግጋት እየጠበቀ በቅድስና ይኖር የነበረው ካህኑ ዘካርያስ ከእግዚአብሔር ተልኮ የመጣውን የቅዱስ ገብርኤል ቃል ባለመስማቱ ሕፃኑ እስከሚወለድ ድረስ ድዳ እንደሚሆን በአብሳሪው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ተነገረው። ይወለዳል የተባለው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን የኤልሳቤጥ መፅነስ በቤተሰቡ መካከል ለረጅም ጊዜ ይፈለግ የነበረ ስለነበር ደስታ ሲፈጥር የካህኑ ዘካርያስ ድዳ መሆን ደግሞ ቤተሰቡን የሚያስጨንቅ ሌላ ክስተት ሆነ። ቅድስት ኤልሳቤጥም ባለመውለዷ ምክንያት በአካባቢው ሰዎች ግን እግዚአብሔር እንዳዘነባትና ልጅ እንደከለከላት ይነገርባት ስለነበር የልምላሜዋ ዘመን ካለፈ በኋላ መፅነስ በመቻሏ ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ በተመለከተበት ወራት እንዲህ አድርጎልኛል (ሉቃ ፩፥፳፭) በማለት ደስታዋን ገልፃለች። አስቀድሞ በነቢዩ በኢሳይያስ የአዋጅ ነጋሪ ቃል ተብሎ እንደተነገረው የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ፥ ለአምላካችንም ጐዳና በበረሀ አስተካክሉ በማለት ፊት አውራሪ ሆኖ የሚላከውን ቅዱስ ዮሐንስን የፀነሰችው ቅድስት ኤልሳቤጥ በፀነሰች በስድስተኛው ወር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ልትጠይቃት ወደ እርሷ በሔደች ጊዜ እጅግ የሚያስገርም ሁኔታ ተፈጠረ። ይኸውም ቅዱስ ዮሐንስ በማኅፀን ውስጥ ኾኖ ለቅድስት ድንግል ማርያም እና በማኅፀኗ ላለው ለዓለም መድኃኒት ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰግዷል (ሉቃ. ፩፥፳፮-፵፩) ።

30/10/2018                     ሉቃስ 1:57-ፍጻሜ     የኤልሳቤጥም የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ፥ ወንድ ልጅም ወለደች። ጎረቤቶችዋም ዘመዶችዋም ጌታ ምሕረቱን እንዳገነነላት ሰምተው ከእርስዋ ጋር ደስ አላቸው። በስምንተኛውም ቀን ሕፃኑን ሊገርዙት መጡ፥ በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ወደዱ። እናቱ ግን መልሳ፦ “አይሆንም፥ ዮሐንስ ይባል እንጂ፡” አለች። እነርሱም፦ “ከወገንሽ ማንም በዚህ ስም የተጠራ የለም፡” አሉአት። አባቱንም ማን ሊባል እንዲወድ ጠቀሱት። ብራናም ለምኖ፦ “ስሙ ዮሐንስ ነው፡” ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያንጊዜም አፉ ተከፈተ መላሱም ተፈታ እግዚአብሔርንም እየባረከ ተናገረ። ለጎረቤቶቻቸውም ሁሉ ፍርሃት ሆነ፤ ይህም ሁሉ ነገር በይሁዳ በተራራማው አገር ሁሉ ተወራ፤ የሰሙትም ሁሉ፦ “እንኪያ ይህ ሕፃን ምን ይሆን?” እያሉ በልባቸው አኖሩት፤ የጌታ እጅ ከእርሱ ጋር ነበረችና። አባቱ ዘካርያስም መንፈስ ቅዱስ ሞላበትና ትንቢት ተናገረ እንዲህም አለ፦ “የእስራኤል ጌታ አምላክ ይባረክ፥ ጐብኝቶ ለሕዝቡ ቤዛ አድርጎአልና፤ ከጥንት ጀምሮ በነበሩት በቅዱሳን ነቢያት አፍ እንደ ተናገረ፥ በብላቴናው በዳዊት ቤት የመዳን ቀንድን አስነስቶልናል፤ ‘ማዳኑም ከወደረኞቻችንና ከሚጠሉን ሁሉ እጅ ነው፤ እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ፤ “በእርሱም ከጠላቶቻችን እጅ ድነን በዘመናችን ሁሉ ያለ ፍርሃት በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ እንድናገለግለው ሰጠን። ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤ “እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤ ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፤ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል።” ሕፃኑም አደገ በመንፈስም ጠነከረ፥ ለእስራኤልም እስከ ታየበት ቀን ድረስ በምድረ በዳ ኖረ.....
ሮሜ 7:14-ፍጻሜ 1 ዮሐንስ 3:7-10 ሐዋ.ሥራ 19:1-11
ቅዳሴ ዘወልደ ነጎድጓድ                          
    ምስባክ                          መዝሙር 21:9-10
ወተወከልኩከ እንዘ ሀሎኩ ውስተ አጥባተ እምየ ላእሌከ ተገደፍኩ እማኅፀን አምከርሠ እምየ አንተ አምላኪየ
ትርጉም
በእናቴ ጡት ሳለሁም በአንተ ታመንሁ ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ