ፀዊረ መስቀል
የየእለቱ ወንጌል ክፍል የየበዓላቱ ሥርዓተ ዋዜማ ፤ ሥርዓተ ማኅሌት ፤ #ወረብ፤ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርበት ቻናል ነው ሼር እያደረጉ ሃይማኖታዊ ድርሻዎን ይወጡ። https://t.me/tsewire @tsewire DM @faya6
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ፀዊረ መስቀል
کانال ፀዊረ መስቀል (@tsewire) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 19 643 مشترک است و جایگاه 4 085 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 715 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 19 643 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 11 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -125 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -11 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 0.99% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 0.59% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 194 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 116 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 2 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የየእለቱ ወንጌል ክፍል የየበዓላቱ ሥርዓተ ዋዜማ ፤ ሥርዓተ ማኅሌት ፤ #ወረብ፤ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርበት
ቻናል ነው ሼር እያደረጉ ሃይማኖታዊ ድርሻዎን ይወጡ።
https://t.me/tsewire
@tsewire
DM @faya6”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 12 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
ያለአንተ ምንም ማድረግ ስለማይቻለኝ በሕይወቴ ጣልቃ እንድትገባ እፈልጋለሁጌታ ሆይ ወደገንዳው የሚያስገባኝ ሰው የለኝም፡፡ /ዮሐ ፭፯ ሰው ስለሌለኝ ወደ አንተu ሳበኝ፡፡ ራሴን መቆጣጠር አልተቻለኝም። ጻድቅ እንድሆን የጽድቅን ሥራ እንድሠራ ጠየቅከኝ ስለዚህ ሳበኝ የሚለው የመለኮትን እርዳታ የሚፈልግ ሰው የጩኸት ድምፅu ነው:: እመኑኝ ወደ ንስሐ እንዳንመጣ አቅም ያጣነው የጸሎት አለመኖር ችግር ነው:: እግዚአብሔር ወደ ሕይወቴ ጣልቃ እንዲገባና ወደ ንስሐ እንድመጣ እፈልጋሁ፡፡ ንስሐ መግባትን ስንፈልግ በራሳችን ማስተዋልና ጉልበት ግን እንመካለን፡፡ ንስሐ መግባትን ስንፈልግ የእግዚአብሔን እርዳታ ግን አንፈልግም፡፡ ይህ የማይቻል እንደሆነ ቅዱስ ይስሐቅ ሦርያዊ እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ «ከጸሎት ሕይወት ውጭ ሌላ ወደ ንስሐu ሕይወት የሚመራ ኃይል፤ በእርሱ ውስጥ እንዳለ የሚያምን ወገን ቢኖር በሰይጣን የተታለለና የታወረ ነው» በእውነት ንስሐ ለመግባት ከፈለግክ ራስህን በጸሎት ውስጥ አድርገህ ጌታን ሳበኝ ከአንተ ኋላ እንሮጣለንu ልትለው ይገባል፡፡ በራሴ ፈቃድ ውስጥ አትተወኝ፡፡ የኔ ደካማ ባሕርይ ወደ አንተ ሊያቀርበኝ አልተቻለውምና ሳበኝ። ከሰዎች መካከል አንዱ ተይዞ ነበር፡፡u በገመድ ታስሮ ቢላዋ ተዘጋጅቶለት ነበር፡፡ መሥዋዕትም ሆኖ ሊሠዋ ነበር፡፡ እርሱም የአብርሃም ልጅ ይስሐቅ ነው:: ራሱን ማዳን እንደምን ይቻለዋል? ሳበኝ ከኋላህ እንሮጣለንy ከማለት ውጭ ሌላ ሊያድነው የሚቻለውu አልነበረም:: ጌታ ከመሠዊያው ጫፍ ሳበው ጌታ ባይስበው በሕይወትም እንዲቆይ ባይፈቅድለት ኑሮ ራሱን ማዳን ባልተቻለውም ነበር፡፡ 🙏💒💙አቡነ ሺኖዳ፫
ያም ከሳምንቱ የመጀመሪያው ቀን በመሸ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ አይሁድን ስለፈሩ ተሰብስበው የነበሩበት ቤት ደጁ ተቈልፎ ሳለ ጌታችን ኢየሱስ መጥቶ በመካከላቸው ቆመና፥ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” አላቸው። ይህንም ብሎ እጆቹንና ጎኑን አሳያቸው፤ ደቀ መዛሙርቱም ጌታችንን ባዩት ጊዜ ደስ አላቸው። ጌታችን ኢየሱስም ዳግመኛ እንዲህ አላቸው፥ “ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ አብ እኔን እንደ ላከኝ እንዲሁ እኔ እናንተን እልካችችኋለሁ።” ይህንም ብሎ እፍ አለባቸው፤ እንዲህም አላቸው፥ “መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ። ኀጢአታቸውን ይቅር ያላችሁላቸው ይሰረይላቸዋል፤ ይቅር ያላላችኋቸው ግን አይሰረይላቸውም።”
ጌታችን ኢየሱስ በመጣ ጊዜ ዲዲሞስ የሚሉት ከዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ ቶማስ ከደቀ መዛሙርቱ ፤ሌሎች ደቀ መዛሙርትም፥ “ጌታችንን አየነው” አሉት፤ እርሱ ግን፥ “የችንካሩን ምልክት በእጁ ካላየሁ፥ ጣቴንም ወደ ተቸነከረበት ካልጨመርሁ፥ እጄንም ወደ ጎኑ ካላገባሁ አላምንም” አላቸው።
ከስምንት ቀን በኋላም ዳግመኛ ደቀ መዛሙርቱ በውስጡ ሳሉ፥ ቶማስም አብሮአቸው ሳለ በሩ እንደ ተዘጋ ጌታችን ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆመና፥ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” አላቸው። ከዚህም በኋላ ቶማስን፥ “ጣትህን ወዲህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና ወደ ጎኔ አግባ፤ እመን እንጂ ተጠራ ጠራጣሪ አትሁን” አለው። ቶማስም፥ “ጌታዬ አምላኬም” ብሎ መለሰ። ጌታችን ኢየሱስም ስለአየኸኝ አመንህን? ብፁዓንስ ሳያዩ የሚያምኑ ናቸው” አለው።
ጌታችን ኢየሱስም በዚህ በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ብዙ ሌላ ተአምራት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ። ነገር ግን ይህ የተጻፈ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እናንተ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ የዘለዓለም ሕይወትን ታገኙ ዘንድ ነው.....
1 ጢሞቴዎስ 5:1-18 1 ጴጥሮስ 3:1-7 ሐዋ፡ሥራ 9:36-ፍጻሜቅዳሴ ዘኤጲፋንዮስ (ዐቢይ)
ምስባክ መዝሙር 18:12-13ለስሒት መኑ ይሌብዋ አምኅቡዓትየ አንጽሐኒ ወእምነኪር መሐኮ ለገብርከ
ትርጉምስሕተትን ማን ያስተውላታል? ከተሰወረ ኀጢአቴ አንጻኝ ከልዩ ሰው ባሪያህን አድነው
የኤልሳቤጥም የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ፥ ወንድ ልጅም ወለደች። ጎረቤቶችዋም ዘመዶችዋም ጌታ ምሕረቱን እንዳገነነላት ሰምተው ከእርስዋ ጋር ደስ አላቸው። በስምንተኛውም ቀን ሕፃኑን ሊገርዙት መጡ፥ በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ወደዱ። እናቱ ግን መልሳ፦ “አይሆንም፥ ዮሐንስ ይባል እንጂ፡” አለች። እነርሱም፦ “ከወገንሽ ማንም በዚህ ስም የተጠራ የለም፡” አሉአት። አባቱንም ማን ሊባል እንዲወድ ጠቀሱት። ብራናም ለምኖ፦ “ስሙ ዮሐንስ ነው፡” ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያንጊዜም አፉ ተከፈተ መላሱም ተፈታ እግዚአብሔርንም እየባረከ ተናገረ። ለጎረቤቶቻቸውም ሁሉ ፍርሃት ሆነ፤ ይህም ሁሉ ነገር በይሁዳ በተራራማው አገር ሁሉ ተወራ፤ የሰሙትም ሁሉ፦ “እንኪያ ይህ ሕፃን ምን ይሆን?” እያሉ በልባቸው አኖሩት፤ የጌታ እጅ ከእርሱ ጋር ነበረችና። አባቱ ዘካርያስም መንፈስ ቅዱስ ሞላበትና ትንቢት ተናገረ እንዲህም አለ፦ “የእስራኤል ጌታ አምላክ ይባረክ፥ ጐብኝቶ ለሕዝቡ ቤዛ አድርጎአልና፤ ከጥንት ጀምሮ በነበሩት በቅዱሳን ነቢያት አፍ እንደ ተናገረ፥ በብላቴናው በዳዊት ቤት የመዳን ቀንድን አስነስቶልናል፤ ‘ማዳኑም ከወደረኞቻችንና ከሚጠሉን ሁሉ እጅ ነው፤ እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ፤ “በእርሱም ከጠላቶቻችን እጅ ድነን በዘመናችን ሁሉ ያለ ፍርሃት በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ እንድናገለግለው ሰጠን። ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤ “እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤ ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፤ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል።” ሕፃኑም አደገ በመንፈስም ጠነከረ፥ ለእስራኤልም እስከ ታየበት ቀን ድረስ በምድረ በዳ ኖረ.....
ሮሜ 7:14-ፍጻሜ 1 ዮሐንስ 3:7-10 ሐዋ.ሥራ 19:1-11ቅዳሴ ዘወልደ ነጎድጓድ
ምስባክ መዝሙር 21:9-10ወተወከልኩከ እንዘ ሀሎኩ ውስተ አጥባተ እምየ ላእሌከ ተገደፍኩ እማኅፀን አምከርሠ እምየ አንተ አምላኪየ
ትርጉምበእናቴ ጡት ሳለሁም በአንተ ታመንሁ ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ
