fa
Feedback
MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩‍🎓👨‍🎓

MTULSU(Mizan Tepi University Law students Union👩‍🎓👨‍🎓

رفتن به کانال در Telegram

A channel that aims to connect MTU law students of all years with a sense of unity and to exchange information. contact us Dawit Amanuel(MTULSU president) 👉0983225745 Dirshaye kida (Vice president) 👉 0965754565 Please join and Invite others too @MTULSU

نمایش بیشتر
557
مشترکین
+124 ساعت
+47 روز
+2530 روز
آرشیو پست ها
🧬 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ በቤተሰብ እና ማስረጃ ሕግ: ቁልፍ የሰበር ውሳኔ መርሆዎች ⚖️  1. 🛡 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ እንደ መከላከያ ማስረጃ እንጂ እንደ ፍርድ ቤት ግዴታ ያለመወሰዱ ➡️ በአባትነት ማረጋገጫ ክስ ላይ ዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ አባትነትን ለማረጋገጥ የሚቀርብ የመከላከያ ማስረጃ እንጂ፣ ፍርድ ቤቱ በራሱ አነሳሽነት ሊያዝ የሚገባው አይደለም። የአባትነት ክስ ሲቀርብ ተከሳሹ መጥሪያ ደርሶት ለመቀበል ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቶ የመከራከር መብቱን ራሱ የተወ ከሆነ፣ ቀርቦ የመከላከያ መብቱን ስላልተጠቀመ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ የመጠየቅ መብቱን ከክሱን ከመከላከል ጋር እንደተወ ይቆጠራል [ሰ/መ/ቁ 154767]። በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በሌለበት ውሳኔ መስጠቱ ስነ ስርዓታዊ አግባብን የጣሰ አይደለም [ሰ/መ/ቁ 154767]። 2. 📜 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ትዕዛዝ በሦስተኛ ወገን (ኑዛዜ ተጠቃሚ) ሲጠየቅ ❌ የቤተሰብ ሕግ የአባትነት መካድ ክስ ሊያቀርቡ የሚችሉ ወገኖችን ማንነት ይገድባል። የኑዛዜ ተጠቃሚ የሆነ ሦስተኛ ወገን፣ የመካድ ክስ ለማቅረብ ከተፈቀደላቸው ሰዎች ውስጥ የማይካተት በመሆኑ፣ እንዲሁም የመካድ ክስ ለማቅረብ የሚያስፈልገውን የፍርድ ቤት ፈቃድ አስቀድሞ ባለማግኘቱ፣ ያለምንም ሕጋዊ መሠረት የዘረመል (D.N.A) ምርመራ እንዲደረግ ማዘዙ ከመነሻው በሕጉ የተመለከተውን ሥርዓት ያልተከተለ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው [ሰ/መ/ቁ 152719]። 3. 🔨 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ትዕዛዝ ባለመፈጸሙ ምክንያት በፍሬ ነገር ላይ መወሰን ⏳ ለቀጠሮ ምክንያት የሆነው ጉዳይ (እንደ ዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ውጤት) ሳይፈጸም የቀረው ከተከራካሪ ወገኖች በአንዱ ጉድለት ከሆነ፣ ፍርድ ቤቱ የጉዳዩን መፈጸም ሳይጠብቅ የመሰለውን ውሳኔ ለመስጠት ይችላል [ሰ/መ/ቁ 152100]። በመሆኑም፣ ፍርድ ቤቱ ዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ፣ ትዕዛዙን አልፎ በሌሎች ማስረጃዎች (ለምሳሌ በሰው ምስክር ቃል) ላይ ተመስርቶ የሟች ልጅነትን ማጽናቱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት አይደለም [ሰ/መ/ቁ 152100]። 4. ⚖️ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ እንደ ገዥ (Conclusive) ማስረጃ አለመቆጠሩ እና ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር መመዘን 🔬 የዘረመል (DNA) ምርመራ ውጤት ብቻውን ፍፁማዊ ገዥ (conclusive) ማስረጃ አይደለም ። አባትነትን የማረጋገጥ ዓላማ ሲኖር፣ የምርመራ ውጤቱ በሌሎች የማስረጃ ዓይነቶች (ለምሳሌ ልጁን እንደ አባት በመንከባከብ፣ የሰው ምስክር ቃል ወይም የልጅነት ሁኔታ) ሊረጋገጥ ከሚችለው ፍሬ ነገር ጋር ተመዝኖ መታየት አለበት ። 5. 👂 የሳይንሳዊ ማስረጃን የመስማት ግዴታ (ለማስተባበል) 🚨 ፍርድ ቤቶች በተከራካሪ ወገኖች የልጅነት ግምትን ለማስተባበል ሲባል የዘረመል ምርመራ እንዲደረግ የቀረበውን አቤቱታ በአግባቡ ማስተናገድ አለባቸው ። 🛑 አንድ ወገን የልጅነት ግምትን ለመቃወም የዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቆ እያለ ፣ የስር ፍርድ ቤት ጥያቄውን ሳይመረምር ወይም ውድቅ ያደረገበትን ምክንያት ሳይገልጽ ውሳኔ መስጠቱ ፣ እንዲሁም በሰው ምስክሮች ቃል ላይ ብቻ ተመርኩዞ አባትነትን ማረጋገጡ የሰበር ሰሚ ችሎት ገዥ ትርጉም የሚፃረር መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው ። 📝 በልደት ምስክር ወረቀት ወይም በልጅነት ሁኔታ (circumstantial evidence) የተረጋገጠ የሕግ ግምት በሳይንሳዊ ማስረጃዎች እንደ ዲ.ኤን.ኤ ምርመራ ሊስተባበል ይችላል ። 6. 💵 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ወጪ እና የፍትሕ አሰጣጥ 💰 ምንም እንኳን ምርመራውን የጠየቀው ወገን ወጪ የመሸፈን ኃላፊነት ቢኖርበትም ፣ የገንዘብ አቅም አለመኖር ፍትሕን ሊያጓድል አይገባም። ፍርድ ቤቱ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ወጪው በማን ይሸፈን የሚለውን ከሕግ አኳያ አይቶ መወሰን ሲገባው፣ ይህን አለማድረጉ ስህተት ነው ። 7. ⭐️ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ጥራት እና ተጨማሪ የባለሙያ አስተያየት ⚰️ ከሟች አስክሬን የተወሰደ የዘረመል (DNA) ናሙና በብክለት ምክንያት አስተማማኝ ውጤት መስጠት ባልቻለበት ሁኔታ፣ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን የበለጠ ግልጽ ለማድረግ ተጨማሪ የልዩ አዋቂ ባለሙያ አስተያየት መስማቱ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 136ን የተከተለ በመሆኑ የሚነቀፍ አይደለም ። 8. 👰‍♀️ በጋብቻ ውስጥ ለተወለደ ልጅ የአባትነት ግምት እና የመካድ ክስ 💍 በጋብቻ ውስጥ የተወለደ ወይም የተጸነሰ ልጅ የአባትየው ነው ተብሎ በሕግ ይገመታል ። አባትነት በሕግ በተሰጠው ግምት መሠረት የተረጋገጠ እንደሆነ፣ አመልካች የምርመራውን ውጤት ከመጠየቅ በፊት በቤተሰብ ሕጉ በሚፈቅደው አግባብ የመካድ ክስ ማቅረብ ይኖርባታል ። በፍሬ ነገር ደረጃ በጋብቻ ውስጥ መወለድ መረጋገጡ፣ የዘረመል (DNA) ምርመራ ይደረግ የሚለውን ክርክር ተቀባይነት ያሳጣዋል ። 9. 🗑 በሌላ ማስረጃ አባትነት ሲረጋገጥ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራን ውድቅ ማድረግ 📄 በልደት ምስክር ወረቀት ወይም በቂ የሰነድና የሰው ማስረጃዎች በመመርመር እናትነት ወይም ልጅነት የተረጋገጠ እንደሆነ ፣ ፍርድ ቤቶች ተጨማሪ የዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ የቀረበው ክርክር ተቀባይነት የለውም በማለት ውድቅ ሊያደርጉ ይችላሉ ።

የመከላከያ ሠራዊት አዋጅ 1286 -2023.pdf5.48 KB

በጣም አመሰግናለሁ! የእናንተ ድጋፍና አድናቆት ለቀጣይ ሥራዬ ትልቅ መነሳሳት ይፈጥርልኛል። ፈጣሪ ያክብርልኝ።

እንኳን ደስ አለህ አቶ ፋሲል! ፋሲል የእኛ ኩራት፣ የእኛ አርያ እና የብዙዎች ተነሳሽነት ምንጭ ነህ። በትምህርት ሕይወትህ ያሳየኸን ንቁ ተሳትፎ፣ ጥሩ የስም ማስጠራት፣ እንዲሁም አርያነትህ እስካሁን ድረስ ልባችንን ሲነካ ኖሯል። ስለ አንተ አውርተን ሳንጨርስ፣ ያለህን ብቃትና ትጋት አድንቀን ሳናበቃ፣ ዛሬ ደግሞ በአዲስ የድል ዜና እና በታላቅ ክብር ስምህን ስንሰማ በእውነት ልባችን በደስታ ተሞልቷል። ይህ ታላቅ ትርጉም ያለው የኩራት ዜና ነው። ይህ ለእኛ እንቅስቃሴን የሚጨምር፣ ተስፋን የሚያበራ እና ማንኛውም ሰው ለአላማው በትጋት ከሰራ ወደ ስኬት እንደሚደርስ በግልጽ የሚያሳይ ታላቅ የምሳሌነት መልዕክት ነው። አንተ ያሳካኸው ድል የአንተ ብቻ ሳይሆን፣ እኛም በአንተ ውስጥ የምንመለከተው የትጋት፣ የትዕግስት፣ የእምነት እና የቆራጥነት ውጤት ነው። እውነት ለመናገር፣ አንተን ስናይ ሰው በጥረት ከተጓዘ የሚደርስበት ከፍታ ምን ያህል ውብ እንደሆነ እንረዳለን። በድጋሚ ከልብ እንኳን ደስ አለህ! ይህ ስኬት የብዙ ታላላቅ ድሎች መጀመሪያ ይሁንልህ። አንተ የእኛ ኩራት ነህ!

የፅናትና የእምነት ውጤት! ​በህይወት ውስጥ ትልልቅ ህልሞችን ማለም ብቻ በቂ አይደለም፤ ለህልም የሚከፈል ዋጋና የማይናወጥ እምነት ያስፈልጋል። ዛሬ፣ በፅናት የታጀበ ስኬት እንዴት ድልን እንደሚያጎናጽፍ በአንድ  ጓደኛዬ ታሪክ ላሳያችሁ ወደድኩ። ​ፋሲል ዘለቀ ይባላል። በ2017 ዓ.ም ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በህግ ትምህርት የተመረቀ፣ የቀድሞው የህግ ተማሪዎች ህብረት የኮሙኒኬሽን ዘርፍ መሪ (Spokesman) ነበር። በዩኒቨርሲቲ ቆይታችን በነበረን ቆይታ ሁሌም የሚነግረኝ አንድ ትልቅ ህልም ነበረው  የፍትህ ሚኒስቴርን መቀላቀል! ታድያ ህልሙን እንደ ሩቅ ተራራ ዝምብሎ እየተመልከተ አልተቀመጠም ነበር። ​ያንን ህልሙን እውን ለማድረግ ሌት ተቀን ይተጋ፣ ያነብና በፈጣሪውም ይተማመን ነበር። ዛሬ ያ ጥረት ፍሬ አፍርቶ በተግባር አየነው! የፍትህ ሚኒስቴር በ2018 ዓ.ም ባወጣው የደረጃ 3 አቃቤ ህግነት የቅጥር ማስታወቂያ ላይ፣ የመግቢያ መስፈርቱ minimum requirementቱ (Exit Exam) 80% እና ከዚያ በላይ በመሆኑ ብዙዎች ገና ከጅምሩ አልተመዘገቡም ፣ ፋሲል ግን ያንን ተሻግሮ የጽሁፍ እና የቃል ፈተናው ወስዶ በፈተናው ታሪክ ተሰምቶ በማይታወቅ ውጤት 100% / 100% በማምጣት ህልሙን በድል ተቀላቅሏል! ይህ ውጤት የተገኘው በአጋጣሚ ሳይሆን፣ በቆራጥነት እና በእምነት ነው። ​ይህንን አጋጣሚ ተጠቅሜ ታድያ ​በቅርቡ ብሔራዊ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ለምትወስዱ፣ እንዲሁም ገና በየደረጃው ላላችሁ የህግ ተማሪዎች መልእክት ማስተላለፍ ፈለኩኝ ከተመረቃችሁ በኋላ ያለው አለም የውድድር አለም ነው በውድድሩ ውስጥ ለማለፍ ደግሞ ጥሩ ውጤት እና ጥሩ ስኪል ያስፈልጋችኋል ይህን ደግሞ ማድረግ እምትችሉት ዛሬ ያላችሁበት ላይ ሁናችሁ ጠንክራችሁ ስት ሰሩ ነው። አስማቱ ያለው በእጃችሁ ባለው እስክሪብቶ ሳይሆን፣ በውስጣችሁ ባለው እምነትና በምታፈሱት ላብ ነው! ​ህልም በቀላል አይገኝም። ከፈጣሪ እገዛ ቀጥሎ የእናንተ ጥረትና ልፋት ወሳኝ ነው። በቅርቡ exit ለምትፈተኑ ሃሪፍ ውጤት ለማምጣት ከወድሁ እራሳችሁን በደንብ አዘጋጁ 1ኛ፣2ኛ ፣3ኛ እና 4ኛ አመት ላላችሁ ተማሪዎች ደግሞ ባላችሁ የጊቢ ቆይታ ለፈተና ማለፍ ብቻ ሳይሆን በዩኒቨርስቲ ቆይታችሁ፣ በጽሁፍ፣ በንግግር፣ በሊደርሺፕ እና በተለያዩ የፈጠራ ክህሎቶች ራሳችሁን ለማብቃት ቆራጥ ሁናችሁ የተሟላ ባለሙያ ለመሆን ስሩ። ለዚህ ​ፋሲል ህያው ምሳሌያችን ነው ፋሲል በዩኒቨርስቲ ቆይታው ከትምህርቱ ጎን ለጎን  በንግግር፣ በጽሁፍ፣ በሊደርሺፕ እና በተለያዩ ክህሎቶች ራሱን አብቅቷል ነ እነዛ ክህቱሎች ተደማምረው ለዛሬ ስኬቴ አብቅተውታል ።ማንም ሰው ፈጣሪን ይዞ፣ በራሱ ላይ እምነት ኖሮት ከሰራ የማይደርስበት የላቀ ደረጃ የለም።ህልም ይኑራችሁ ከዚያን ለህልማችሁ ኑሩ የትኛውም ከባድ የሚመስል ፈተና በቆራጥነትና በእምነት ይታለፋል። ፋሲሎ ወንድሜ! እንኳን ደስ አለህ። ፈጣሪ ለዚህ ታላቅ ክብር ስላበቃህ እጅግ ደስ ብሎኛል። ይህ ገና የጅማሬህ ስኬት እንደሆነና ከዚህ በላይ ለአገራችን የፍትህ ስርአት ትልቅ አሻራ እንደምታስቀምጥ ሙሉ እምነት አለኝ። መልካም የስራ ዘመን ይሁንልህ! ​ሁላችሁም እንደ ፋሲል የህልማችሁ ባለቤት፣ የድላችሁም ነጋሪ እንድትሆኑ እመኛለሁ። ​መልካም እለተ ሰንበት! ​© ስኡድ አህመድ (የቀድሞው የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት)

+7
Snapchat-1154726147.jpg1.81 KB

Our Half Life Day: A Celebration of Joy, Unity, and Unforgettable Memories CONGRATULATIONS Today, we successfully celebrated our Half Life Ceremony in a beautiful, honorable, and unforgettable way. This special day was not only a celebration, but also a true reflection of our unity, friendship, and shared journey. We extend our heartfelt gratitude to everyone who contributed through their ideas, effort, time, and dedication to make this event successful. Your support made this day more meaningful and memorable than words can express. This beautiful moment of togetherness will forever remain in our hearts as a cherished memory. Thank you all for making our Half Life Celebration successful, memorable, and truly special. May our unity and friendship continue to grow stronger.

Dear students who took photos during Today’s program, Please send the pictures to me via @Dirshu65 Thank you !!🙏🙏

🌙 EID MUBARAK 🌙 ✨As we mark the end of the holy month, I extend my warmest wishes to the entire MTULSU community and Mizan Tepi university Muslim students. ✨ In a field that demands so much of our time and intellect, it is important to cherish these moments of celebration and togetherness. ✨ May this Eid bring you all a sense of peace and accomplishment, and may it inspire continued dedication and integrity in your legal journeys. Eid Mubarak to every member may your holiday be restful and your year ahead be successful. 🌙 EID MUBARAK 🌙 Dawit Amanuel Mizan Tepi law students union president @MTULSU

🌙 Eid Mubarak!🌙 On this blessed occasion, MTULSU extends its warmest wishes to all students, partners, and all Muslim communities of Mizan Tepi university. May Eid inspire renewed commitment to justice, unity, and service, values that define our community and guide our journey in the legal profession. ✨ As we celebrate this special occasion, may we continue striving for a more equitable and compassionate society. Wishing you a peaceful and fulfilling Eid!🌙 Dawit Amanuel MTULSU President

መቅረት አይቻልም ይላሉ 3ተኛ አመት የህግ ተማሪዎች @MTULSU
መቅረት አይቻልም ይላሉ 3ተኛ አመት የህግ ተማሪዎች @MTULSU

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው ዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ዒድ ሙባረክ! @MTULSU
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው ዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ዒድ ሙባረክ! @MTULSU

Attention Everyone:Guys, many Telegram accounts are being hacked recently. Please do not click on suspicious links, even if they are sent by people you know. Join us : @MTULSU

#MizanTepiUniversity ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ከወሰዱ የተቋሙ ተማሪዎች ከ95% በላይ የሚሆኑት ተፈታኞች ማለፋቸውን አሳውቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በ2018 ዓ.ም
#MizanTepiUniversity ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ከወሰዱ የተቋሙ ተማሪዎች ከ95% በላይ የሚሆኑት ተፈታኞች ማለፋቸውን አሳውቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በ2018 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ በህክምና ዶክትሬት ዲግሪ የሚያስመርቃቸው ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100 %) የመውጫ ፈተናውን ማለፋቸውን ገልጿል፡፡ በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲው የስነ-ዓዕምሮ ትምህርት እና የሚድዋይፈሪ ትምህርት ክፍሎች ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100 %) ፈተናውን እንዳለፉ ተገልጿል፡፡

2018 E.c Mizan Tepi University remedial students' mid examination schedule. Wishing you all the best! From. Mtu students unio
+2
2018 E.c Mizan Tepi University remedial students' mid examination schedule. Wishing you all the best! From. Mtu students union office Join us. @MTULSU

#NGATResult የካቲት 04/2018 ዓ.ም የተሰጠው 2ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ተለቋል። ውጤትዎን ለማየት 👇 https://result.eth
+1
#NGATResult የካቲት 04/2018 ዓ.ም የተሰጠው 2ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ተለቋል። ውጤትዎን ለማየት 👇 https://result.ethernet.edu.et ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'NGAT Results' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ። @MTULSU