fa
Feedback
Ethiopian Lecturers Voice

Ethiopian Lecturers Voice

رفتن به کانال در Telegram
9 638
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-117 روز
-5330 روز
آرشیو پست ها
ኢትዮጵያ ቀይ ባህርን (በአሰብ በኩል) በየትኛውም አማራጭ ማግኘት
Anonymous voting

የቤት ኪራይ‼️ የኤሌክትሪክ ክፍያ ጨምሯል በሚል ምክንያት የቤት ኪራይ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተከራዮች ቅሬታ አሰሙ‼️ በአዲስ አበባ ከተማ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጭማሪ እያሳየ የመጣዉ የቤት ኪራይ ዋጋ ንረት ስጋት እንደፈጠረባቸዉ ነዋሪዎች ይናገራሉ ። በአሁኑ ወቅት የቤት ኪራይ ጭማሪ ከማሳየቱ በተጨማሪ በምንፈልገዉ ሰፈርና ለስራ ቦታችን ቅርብ በሆኑ አከባቢዎች ላይ ቤት ማግኘት ባለመቻላችን ከፍተኛ ለሆነ የትራንስፖርት ወጪ ተዳርገናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገልፀዋል ። ከኢኮኖሚ አቅማችን እና ከስራ ቦታችን ጋር ቅርበት ያለዉ ቤት ለማግኘት ተቸግርናል የሚሉ ቅሬታ አቅራቢዎች እንደተናገሩት የኤሌክትሪክ ክፍያ ጨምሯል በሚል ምክንያት አከራዮች ለስቶቭና ለምጣድ የምንከፍለዉን ክፍያ ከፍ አድርገዉብናል ይላሉ ። በዚህም የተነሳ  በአዲስ አበባ መሀል ከተማ በሚገኙ ሰፈሮች ቤት በጣም ዉድ በመሆኑ በተለይም ዝቅተኛ ገቢ ላላቸዉ ሰዎች የማይታሰብ ነዉ ሲሉ ገልጸዋል ። የቤት ኪራይ ዋጋ ከቦታ ቦታ ልዩነት ቢኖረውም የተሻሉ ናቸዉ ከሚባሉ አከባቢዎች አንዱ በሆነዉ በጎሮ አከባቢ ስቶቭ መጠቀም የሚቻልበት አንድ ትንሽ ክፍል ቤት እስከ 5ሺህ 500 ብር እንደሚጠየቁ የሚናገሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ እስቶቭና ምጣድ ለመጠቀም እስከ 7ሺህ ብር እንጠየቃለን ሲሉ ገልፀዋል ። ሌላኛዉ አስተያየት ሰጪ አንደሚሉት ከሆነ የምንጠየቀዉን ክፍያ ከፍለን እንኳን በእረፍት ቀን አብዛኛዉ ሰዉ ቤት በሚቀመጥበት ቀን ከቆጣሪ መብራት የሚያጠፉ አከራዮች መኖራቸዉን ይናገራሉ ። የቤት የዋጋ ንረት እየተባባሰ መምጣት ከፍተኛ የኑሮ ጫና አሳድሮብናል የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቸ የሚመለከተዉ አካል የዋጋ ማረጋጋት ሲራ እንዲሰራ ጠይቀዋል ። Bisratfm

ከደመወዝ የጭማሪ ዜና በኃላ የቤት ኪራይዎ ላይ ስንት ብር ተጨመረ?
Anonymous voting

✋

አዲሱ የደመወዝ ስኬል‼️
አዲሱ የደመወዝ ስኬል‼️

#የደመወዝ_ጭማሪ! መስከረም ወር ሲጠናቀቅ;- 👉የደሞዝ ጭማሪው ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል፤ 👉ክልሎች መረጃ አሟልተው ባለማድረሳቸው መክፈል      አልተቻለም፤ 👉መረጃ ስላልተሟላ በቀጣይ ወራት ይከፈላል፤ 👉በቀጣይ ወራት ከነውዝፉ ተፈፃሚ ይሆናል፤... ወዘተ የሚሉ ዘገባዎችን የመንግስት ተሿሚዎችን ጨምሮ ሁሉም የመንግስት ተቀጣሪዎች መስከረም ወር 2018 ሲጠናቀቅ መስማት አይፈልጉም። ስለዚህ የደመወዝ ጭማሪውን መንግስት ማንም ሳይጠብቅ ድንገት ይፋ እንዳደረገው ሁሉ የተናገረው ጊዜ ምንም ሳይሸራርፍ እና ምክንያት ሳይደረድር ተፈፃሚ እንደሚያደርግ ሁሉም የመንግስት ተቀጣሪዎች በእምነት ይጠባበቃሉ። Source https://t.me/ethio_first1

photo content

ነጭ አብዮት እንጀምራለን ! ** ‎#የመምህራን #ደመወዝ #ከሁሉም #በላይ #ልዩ #ትኩረት #የሚሻው #ለምንድን #ነው? ‎➨ክቡር የመንግስት አካላት እና ውድ የሀገራችን መሪዎች ሆይ :-እኔ መምህር ተማም እንደሻው (28 አመት የማስተማር ልምድ ያለኝ ) ‎ዛሬ ይህንን መልእክት ለመጻፍ የተነሳሁት፣ የሀገራችንንና የትውልድን እጣ ፈንታ የሚወስነው ትልቁ ሙያ፣ የመምህርነት ሙያ፣ አሁንም ድረስ የሚገባውን ክብርና የኢኮኖሚ ድጋፍ እያገኘ ባለመሆኑ ነው። የመምህራን ደመወዝ፣ ከሌሎች የመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ በተለየ መልኩ ሊታይ የሚገባው ጉዳይ መሆኑን በብርቱ ለማሳሰብ እወዳለሁ። ‎1. የመምህሩ ሚና ልዩ ነው፦ ‎መምህር በቀላሉ ደመወዝ የሚቀበል የመንግስት ሰራተኛ ብቻ አይደለም። መምህር የሀገር አሰልጣኝ፣ የትውልድ ቀራጺ፣ የዕውቀት ምንጭ፣ የክህሎት ሰጭና የመልካም ስነ-ምግባር አርአያ ነው። የሀኪም፣ የኢንጂነር፣ የገበሬ፣ የፖለቲከኛና የማንኛውንም ባለሙያ መሠረት የሚጥለው መምህር ነው። መምህር ለሀገሩ እድገት የላቀ ዋጋ የሚከፍል እንጂ የደመወዝ ቆጠራ ብቻ የገባ አይደለም። ‎2. የመምህሩ የገንዘብ ችግር የሚያስከትለው አደጋ፦ ‎አንድ መምህር ለቤተሰቡ የሚያስፈልገውን መሰረታዊ ነገር እንኳን ማሟላት ሲሳነው፣ ትምህርቱን በሙሉ ልቡና በሙሉ ሀሳቡ ማስተማር ይሳነዋል። በኑሮ ጫና ተጠምዶ ተማሪዎቹን በሚገባ ለማገልገል ይቸገራል። ይህም በትምህርት ጥራት ላይ ቀጥተኛና አደገኛ ተጽእኖ ይፈጥራል። ደካማ ደመወዝ ጥሩና ብቁ የሆኑ ተማሪዎች የመምህርነት ሙያን እንዳይመርጡ ያደርጋል፣ በዚህም የትምህርት ጥራቱ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየወረደ ይሄዳል። ‎3. ኢንቨስትመንት ለትውልድ እንጂ ለግለሰብ አይደለም፦ ‎የመምህር ደመወዝ ጭማሪ እንደ ተራ የመንግስት ወጪ መታየት የለበትም። ይልቁንም፣ በመጪው ትውልድ ላይ የሚደረግ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው። አንድን ሀገር ወደፊት ለማስኬድ የሚደረጉ ጥረቶች ሁሉ የሚቀመሱት በመምህሩ የትምህርት ጥራት ነው። መምህሩ ደመወዙ በቂ ሆኖለት ሙያውን በሙሉ ልቡ ሲያገለግል፣ የሚፈጥረው ትውልድ ብቁ፣ የተማረና ምርታማ ይሆናል። ይህ ደግሞ የሀገርን ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ መሰረት ያጠናክራል። ‎4. የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ፦ ‎በአለም ላይ በጥራትና በኢኮኖሚ የላቁ ሀገራት መምህራንን ከሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በተለየ መልኩ እንደሚያከብሩና ከፍ ያለ ደመወዝ እንደሚከፍሉ ታሪክ ይመሰክራል። መምህራንን መደገፍና ማበረታታት የሀገራቸውን እድገት ዋስትና ለማድረግ እንደ ትልቅ ስትራቴጂ ይወስዳሉ። ይህ ተሞክሮ ለኛም ትልቅ ትምህርት ነው። ‎ስለዚህ፣ የመምህራን ደመወዝ ጭማሪ ከተራ የደመወዝ ማሻሻያ አልፎ፣ ለሀገር ህልውናና ዘላቂ ብልጽግና እንደ ትልቅ ስትራቴጂያዊ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ እንዲሆን አጥብቄ አሳስባለሁ። መንግስት ይህንን ጉዳይ ከሌሎች በተለየ ሁኔታ በመመልከት የመምህራንን የኑሮ ሁኔታ በማሻሻል ለትውልድ የተሻለ መሰረት እንዲጥል ጥሪዬን አቀርባለሁ። ‎በአክብሮት፣ ‎👆ነጭ አብዮት ከመጀመራችን በፊት ጥያቄዎቻችን ይመለሱልን ዘንድ በታላቅ አክብሮት፣ፍፁም ሰላማዊና ፍቅር በተሞላበት አክብሮት እንጠይቃለን ! የኢትዮጵያ መምህራን ነሃሴ 22/2017 ዓ.ም Join us :https://t.me/ethio_first1

የጤና ሚኒስቴር፣ በመላው ሀገሪቱ ላሉ የጤና ባለሙያዎች ነጻ የህክምና እና የትራንስፖርት አገልግሎትን ጨምሮ የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን የያዘ አዲስ ፓኬጅ ይፋ አደረገ። ይህ እርምጃ፣ የጤና ባለሙያዎች ከሶስት ወራት በፊት አድማ ከመቱ እና በመጪው መስከረም ወር ሌላ አድማ ለመጥራት በዝግጅት ላይ ባሉበት ወቅት የመጣ ነው። በጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ በኩል ለክልሎች እና ለከተማ አስተዳደሮች በተላለፈው መመሪያ መሰረት፣ ከመስከረም 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆኑ ከታዘዙት ሰባት ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል፦ 1ኛ. ሁሉም የጤና ተቋማት ለሰራተኞቻቸው እና ለቤተሰቦቻቸው ብቻ የሚያገለግል "የሰራተኛ ክሊኒክ" በማቋቋም ነጻ ህክምና እንዲሰጡ ታዟል። የረጅም ጊዜ መፍትሄው ደግሞ የጤና መድን ሽፋን እንዲያገኙ ማድረግ ነው። 2ኛ. የጤና ተቋማት "ያላቸውን ተሽከርካሪ በመጠቀም" በስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት ለሰራተኞቻቸው የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያቀርቡ መመሪያ ተሰጥቷል። 3ኛ. በእረፍት ቀናት እና በበዓላት ለሚሰሩ የትርፍ ሰዓት ስራዎች ክፍያ፣ በ2014 ዓ.ም. በወጣው የሲቪል ሰርቪስ መመሪያ መሰረት በተሻሻለው ስሌት እንዲፈጸም ታዟል። ይህ የመንግስት ምላሽ፣ የጤና ባለሙያዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ከተወያዩ በኋላ የመጣ ሲሆን፣ 'የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ንቅናቄ' የተባለው ስብስብ ውሳኔዎቹን "እንደ ጥሩ ጅምር" እንደሚመለከተው ገልጿል። ይሁን እንጂ ንቅናቄው፣ የማሻሻያዎቹን ተግባራዊነት በተመለከተ ከባድ ጥያቄዎችን አንስቷል። ለትራንስፖርት አገልግሎት "አብዛኞቹ የጤና ተቋማት ከአምቡላንስ ውጪ ሌላ ተሽከርካሪ የላቸውም" በማለት የአፈጻጸሙን አዳጋችነት ጠቁሟል። ነጻ ህክምናው ባለሙያዎች በሚሰሩበት ክልል ብቻ የተወሰነ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው ገልጸው፣ ይህም እንደ ጥቁር አንበሳ ያሉ ትላልቅ ሆስፒታሎችን ተደራሽነት ሊገድብ እንደሚችል አስረድተዋል።  👊 @EUASAs @EUASAs @EUASAs @EUASAs @EUASAs @EUASAs

#ዜናመሠረት ከሀምሌ 1 ጀምሮ ከ20 አመት በላይ ያገለገሉ የመንግስት ሰራተኞች ጨምሮ የአስር ሺዎች እጣ ፈንታ ታውቋል (ይህ ከትናንት በስቲያ በመሠረት ሚድያ የቀረበ መረጃ በብዙ አንባቢዎች ጥያቄ መ
#ዜናመሠረት ከሀምሌ 1 ጀምሮ ከ20 አመት በላይ ያገለገሉ የመንግስት ሰራተኞች ጨምሮ የአስር ሺዎች እጣ ፈንታ ታውቋል (ይህ ከትናንት በስቲያ በመሠረት ሚድያ የቀረበ መረጃ በብዙ አንባቢዎች ጥያቄ መሰረት ለሁሉም አንባቢዎች ክፍት ተደርጎ በድጋሜ ቀርቧል) (መሠረት ሚድያ)- ከጥቂት ወራት በፊት የፀደቀው የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ "ተቋማት ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲፈፅሙ የሚያስችል ነው" ቢባልም ከአዋጁ ጋር ተያይዞ በርካታ የመንግስት ሰራተኞች ከስራ ሊቀነሱ እንደሚችሉ መሠረት ሚድያ ከወራት በፊት መዘገቡ ይታወሳል። አሁን የደረሰን መረጃ እንደሚጠቁመው ደግሞ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት ሰራተኞች ከሀምሌ 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ ከስራ ሊቀነሱ እንደሆነ ታውቋል። በዚህም ሁሉም የመንግስት ተቋማት 'ሪፎርም' በሚል አሰራር ከ20 አመት በላይ ያገለገሉ ሰራተኞችን ጨምሮ ከሀምሌ 1 ጀምሮ ውላቸው እንዲቋረጥ ከወዲሁ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን መሠረት ሚድያ ከመንግስት ምንጮች አረጋግጧል። ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣ ከፓርላማ ፅህፈት ቤት እስከ ዩኒቨርስቲዎች፣ ከክፍለ ከተማዎች እስከ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ወዘተ ይተገብሩታል በተባለው በዚህ የሰራተኛ ቅነሳ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞች ከስራቸው ይሰናበታሉ ተብሎ ይጠበቃል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ በአዋጁ አላማና አስፈላጊነት ዙሪያ ከወራት በፊት ማብራሪያ ሰጥተው በነበሩበት ወቅት በቀጥታ ስለ ሰራተኛ ቅነሳው ያነሱት ነገር ባይኖርም በመንግስት አቅጣጫ ከተያዘባቸው ጉዳዮች አንዱ "ከሚያስፈልገው በላይ የመንግስት ሰራተኛ አለ" የሚለው ዋናው መሆኑን ጠቅሰው ነበር። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚንስትር አቶ ተስፋዬ በልጅጌም ሂደቱ የግለሰቦችን መብት ያለአግባብ እንዳይጎዳ ሚዛኑን አስጠብቆ በመሄድ ረገድ ተገቢው ጥንቃቄ ይደረጋል ቢሉም በርካቶች ከስራቸው መቀነሳቸው እንደማይቀር ታውቋል። የረቂቅ አዋጁን ይዘት በአግባቡ ባለመረዳት በአንዳንድ የሚዲያ ተቋማት የተዛቡ መረጃዎች እየተላለፉ እንደሆነ የሚናገሩት ዶ/ር ነገሪ በበኩላቸው ግልፀኝነት በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ በመወያየት ረቂቅ አዋጁን የበለጠ ለማዳበር እና ህዝቡ ትክክለኛ መረጃ እንዲያገኝ ለማድረግ ይደረጋል ብለዋል። አዋጁ እንደ ፍርድ ቤት፣ አቃቤ ህግ፣ ፖሊስ፣ መከላከያ፣ እና ደህንነትን የመሳሰሉ ተቋማት ውስጥ የብሄር ስብጥር ለማድረግም ያለመ መሆኑን የጠቁሙት ምንጮቻችን አዋጁ "የብሔር ብሔረሰቦች ብዙሃነት እና አካታችነት ስርዓትን ይገነባል" በሚል በመንግስት እንደታሰበ አስረድተዋል። የዚህን የመንግስት ሰራተኞች ቅነሳ የሚጠቁም ነገር ግን ብዙ ሰው ልብ ያላለው አንድ መረጃ በአንድ የመንግስት ሚድያም ተለቆ ነበር። "ሲቪል ሰርቪሱ ሀገሪቷ ከምትሸከመውና አገልግሎቱ ከሚፈልገው በላይ የበዛ መሆኑ ተጠቆመ" የሚል መረጃ በቅርቡ በኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት ተሰራጭቶ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ያለው የሲቪል ሰርቪሱ ቁጥር ሀገሪቷ ከምትሸከመውና አገልግሎቱ ከሚፈልገው በላይ የበዛ መሆኑን ዶ/ር ነገሪ መናገራቸውን ዘግቦ ነበር። ዶ/ር ነገሪ በዚህ ንግግራቸው እንደጠቀሱት "በየመንግሥት መሥሪያ ቤቱ ያለው የሠራተኛ ቁጥር በጣም በርካታ ነው። ሀገሪቷ ከምትሸከመውና አገልግሎቱ ከሚፈልገው በላይ የበዛ ነው። ከአደረጃጀት አንጻር ሲታይም በአንድ መሥሪያ ቤት ውስጥ መዋቅሩ የሚሸከመው ብዙ የሰው ኃይልን ነው፤ በተሸከመ ቁጥር ደግሞ የሚያገኘው ጥቅም አናሳ ነው" ብለው ነበር። ሀላፊው አክለውም "የመንግሥት ሠራተኞች የብዛታቸውን ያህል የሚሠሩት አገልግሎት የሚያረካ አይደለም፣ የተወሰኑ ይሠራሉ፤ ሌሎቹ ግን የተወሰኑ ሠራተኞች በሠሩት ትከሻ ላይ ተንጠላጥለው ይኖራሉ" በማለት የሰራተኛ ቅነሳ መኖሩን በተዘዋዋሪ መንገድ ጠቁመዋል። ይሁንና ይህ መረጃ መሠረት ሚድያ ላይ ከወጣ በኋላ ለመንግስት ሚድያዎች በሰጡት ሌላ ማብራርያ “አዋጁ በብቃትና በውድድር ላይ የተመሠረተ ነጻና ገለልተኛ ሲቪል ሰርቪስ ይፈጥራል” በማለት አዋጁ የሠራተኛውንም ጥቅማጥቅም ያካተተ እንደሆነም ተናግረዋል። ሀላፊው አክለውም አዋጁ የመንግሥት ሠራተኛው በብቃትና ውድድር ላይ ተመስርቶ ተገቢ የሆነ ጥቅም እንዲያገኝ የወጣ እንጂ መንግሥት ሠራተኛውን ለመቀነስ ያለመ እንዳልሆነ እና መረጃን በማጣመም ሕዝብን ለማደናገር የሚደረገው ጥረትም መሠረተ ቢስ ነው በማለት ተናግረዋል። ዶ/ር ነገሪ ይህን ማስተባበያ ቢያቀርቡም መሠረት ሚድያ አሁንም የሠራተኛ ቅነሳውን በተመለከተ የሰራው ዘገባ ትክክለኛ እንደሆነ እንደሚያምን ለተከታታዮቹ ለመግለፅ ይወዳል። በአሁን ሰአት በርካታ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በየማስታወቂያ ቦርዶቻቸው የስራ ድልድል እየለጠፉ መሆኑን እና ከስራቸው የተቀነሱ ሰዎች ከወዲሁ እጣ ፈንታቸውን እያወቁ መሆኑን ያሰባሰብናቸው መረጃዎች ያሳያሉ። መረጃን ከመሠረት! @MeseretMedia

የአሜሪካ ቀጣይ የቪዛ ክልከላ መምህራንን ብሎም የሀገራችንን ኢኮኖሚ ይጎዳል። በተለይ Scholarship ማግኘት አይቻልም ማለት ነው። መምህራን በዲፕሎማሲ ማሳመን አለብን ብለው ያምናሉ?
Anonymous voting

ኢትዮጵያ በቀጣይ ቪዛ ከሚከለከሉ 36 ሀገራት ተርታ ተመዝግባለች። የአሜሪካን ኤምባሲ በተለያዩ የመገናኛ አማራጭ መጠየቅ አለብን ብለው ያምናሉ? ሀሳብዎን በኮሜንት ላይ ያስቀምጡ።
Anonymous voting

የደሞዝ ጥያቄ ህጋዊ ነው አጣጥመን ለመሔድ እንሞክራለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ******** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ መምህራን ጋር በ
+1
የደሞዝ ጥያቄ ህጋዊ ነው አጣጥመን ለመሔድ እንሞክራለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ******** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ መምህራን ጋር በተወያዩበት ወቅት የደሞዝ ጥያቄ ህጋዊ ነው አጣጥመን ለመሔድ እንሞክራለን ብለዋል፡፡ ለመምህራን ትልቅ ክብር እንዳላቸው የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እኔ በህይወት እያለሁ መኪናቸውን ነድተው ሃይስኩል በር ላይ አቁመው ሲያስተምሩ ከማየት በላይ ደስታ የለኝም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ሰዎች በፖለቲካው መንደር፣ በፌስ ቡክ እንዲሁም በፓርላማ ነገሮችን አዛብተው ቢያመጡ የሚጠበቅ ነው፤ መምህራን ጋር ግን ነገር ከተበላሸ የሀገር ጉዳት ነው ብለዋል። በመሆኑም የመምህራን ሐሳብ የፖሊሲ ግብዓት ጭምር በመሆኑ እያንዳንዱ የሚነሡ ጉዳዮችን በጥንቃቄ እንደሚያዩት ተናግረዋል። አሁን የሚደረገው ውይይትም የይስሙላ ሳይሆን ከልብ የመነጨ እና ጥቅም የሚገኝበት ይሆናል ብለው እንደሚያምኑም ነው የገለጹት። ደመወዝ ቢጨመር ቤት ቢኖር የሰው ልጅ ፍላጎት ገደብ የለውም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ነገር ግን ለማደግና ለመሻሻል መጓጓት ተገቢ ስለሆነ ሁለቱን አጣጥሞ መሄድ እንደሚገባ ገልጸዋል። በለሚ ታደሰ #EBC #ebcdotstream #PMAbiy #Teachers

#ዜናመሠረት "የጤና ሚኒስቴር በድጋሚ ከድቶናል ስለዚህ የስራ ማቆም አድማው ይቀጥላል"- የኢትዮጵያ ጤና ባለሞያዎች ንቅናቄ ቦርድ "እኛ እንደ ቦርድ ይህንን ቀውስ በውይይት ለመፍታት ሃላፊነት፣ ትዕግስት እና እውነተኛ ፈቃደኝነት አሳይተናል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ግን በድርጊቱ እና በዝምታው በግልጽ እንዳሳየው የሀገሪቱን የጤና ስርዓትን የሚያገለግሉ ባለሙያዎችን ለመጠበቅ፣ ለማዳመጥ ወይም ለመደራደር ፈቃደኛ አለመሆኑን በግልጽ አሳይቷል። ስለዚህ በመላ አገሪቱ የምትገኙ የጤና ባለሙያዎች ይህን ጥሪ እናቀርባለን" https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/bb9?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g

(መሠረት ሚድያ)- የኢትዮጵያ ጤና ባለሞያዎች ንቅናቄ ቦርድ አባላት ከቀናት በፊት ከጤና ሚኒስቴር አማካሪ ጋር ይፋዊ ያልሆነ ንግግር አድርገው ነበር። በዚህም መሰረት የጤና ባለሞያው ሰኞ ወደ ስራ እንዲመለስ ቦርዱ በመግለጫ የሚያሳውቅ ከሆነ የታሰሩት ባልደረቦቻቸውን እስከ ማክሰኞ ድረስ ለማስለቀቅ እናም ህጋዊ ጥያቄዎቻቸው ብዙም ሳይቆይ በጥቂት ጊዜ እንደሚመለስ እና ለተግባራዊነታቸውም መግለጫው በወጣ ማግስት ተገናኝቶ ለመወያየት በቃል ደረጃ ተስማምተው ነበር። ይሁንና "ለዚህም 10 ባለሞያዎችን ለውይይት አዘጋጅተን ነበር። የታሰሩት ባልደረቦቻችንን በልባችን በመያዝ እና መልካም ፈቃድና ኃላፊነት  ለማሳየት፣ ከሰኞ ጀምሮ ወደ ሥራ መመለሳችንን በማስታወቅ መግለጫ በማውጣት ጥያቄያቸውን አክብረናል" የሚለው ዛሬ ቦርዱ ያወጣው እና ለመሠረት ሚድያ የደረሰው መግለጫ ንቅናቄው መግለጫውን ይፋ ባወጀ ማግስት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አቋሙን ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል ብሏል። የታሰበውን ቀጣይ ውይይት በመሰረዝ መስሪያ ቤቱ በራሱ አማካሪ በኩል ለጤና ባለሙያዎቹ ቦርድ የሚከተለውን መረጃ መስጠቱ ታውቋል: 1) የባልደረባዎቻቸውን ከእስር ነፃ የማድረግ ዋስትና እንደማይሰጥ። 2) ጥያቄዎቻቸውም እየታዩ ሊመለሱ የሚችሉ እንጂ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የሚሰጥ መልስ እንደማይኖር:: 3) ወደ ስራቸው ቢመለሱም ለደህንነታቸው እና ላለመታሰራቸው፣ ለማስፈራሪያዎች፣ ቅጣቶች እና ዛቻዎች ምንም ማስተማመኛ እንደማይሰጥ አስታውቋል። "ይህ አስደንጋጭ ክህደት እኛ ላሳየነው መልካም እምነትና አክብሮት ንቀትን የሚያሳይ ብቻ አይደለም፣ ነገር ግን መብቶቻቸውን የጠየቁ የጤና ባለሙያዎችን ለማዳከም እና ለአደጋ ለማጋለጥ ሆን ተብሎ የተደረገ ጥረትንም ያመለክታል" ያለው ቦርዱ ከዚህ የከፋው ደግሞ በአሁኑ ወቅት በእስር ላይ ባሉ ባልደረቦቻቸው ላይ ከተፈፀመው በደል በተጨማሪ ሌላ ማስፈራራት እና አዲስ እስራት ሊደረግ እንደሚችል እና እየተደረገ እንዳለም መረጃ ተሰጥቶናል ብለዋል። "እኛ እንደ ቦርድ ይህንን ቀውስ በውይይት ለመፍታት ሃላፊነት፣ ትዕግስት እና እውነተኛ ፈቃደኝነት አሳይተናል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ግን በድርጊቱ እና በዝምታው በግልጽ እንዳሳየው የሀገሪቱን የጤና ስርዓትን የሚያገለግሉ ባለሙያዎችን ለመጠበቅ፣ ለማዳመጥ ወይም ለመደራደር ፈቃደኛ አለመሆኑን በግልጽ አሳይቷል። ስለዚህ በመላ አገሪቱ የምትገኙ የጤና ባለሙያዎች ይህን ጥሪ እናቀርባለን" በማለት የስራ የስራ ማቆም አድማው እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። "ይህ ክህደት መንፈሳችንን እንዳያደፈርስ ሆኖም  ቁርጠኛነታችንን እንዲያንቀሳቅስ እናድርግ። የምንታገለው ለራሳችን ብቻ አይደለም - የምንታገለው ለፍትህ፣ ለክብር እና  የጤና ባለሞያው ትክክለኛ መብቱን በመጠየቁ የማይቀጣበት ወደፊትን ለመፍጠር ነው። የታሰሩት ባልደረቦቻችን አሁንም በእስር ላይ ናቸው፣ ብቸኛው 'ወንጀላቸው' ለእውነት መቆማቸው ብቻ ነው። አሁን ደግሞ እነሱ ብቻ ሳይሆኑ እስር እና ማንገላታት እንደሚቀጥሉ ተነግሮናል። ይህ ከአሁን በኋላ ስለ ፍትሃዊ ደመወዝ ወይም የሥራ ቦታ ክብር ብቻ አይደለም:: ይህ ስለደህንነታችን፣ ስለነፃነታችን እና ስለወደፊት ሕይወታችን ነው። የጤና ሚኒስቴር የገባው ቃል  ዋጋ እንደሌለው አሳይቶናል። ውይይት ያለ  መተማመን ምንም ትርጉም የለውም። በሐቀኝነት ቀርበን በከሃዲነት ተከፍለናል። እኛ ግን ወደዚህ ትግል የገባነው በስነምግባር እና በታማኝነት ነው። ስለዚህም የስራ ማቆም  አድማው እንዲቀጥል ወስነናል" በማለት መግለጫው አስታውቋል። አክሎም "በእኛ ጥሪ መሰረት ሰኞ ስራ ልትጀምሩ ያሰባችሁ ውድ ባልደረቦቻችን ከላይ በዘረዘርናቸው መከዳቶች ምክንያት የተነሳ ስራ ከመጀመር እንድትቆጠቡ አበክረን እናሳስባለን" ብሏል። መረጃን ከመሠረት!

ባለፈው በገባነው ቃል መሰረት የመምህራንን መብት ለማስከበር ያለመ ማንኛውንም ገፅ እናስተዋውቃለን። በትንሹ ከአስር በላይ ተመጋጋቢ ገፆች ያስፈልጉናል። ተቀላቀሉ 1. https://www.facebook.com/ethiopia.lecturers?mibextid=ZbWKwL 2. https://t.me/+nqZomRhDtnFmY2Zk (በዚህ ገፅ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። Be a leader there. Join now or on Saturday!)

ባለፈው በገባነው ቃል መሰረት የመምህራንን መብት ለማስከበር ያለመ ማንኛውንም ገፅ እናስተዋውቃለን። በትንሹ ከአስር በላይ ተመጋጋቢ ገፆች ያስፈልጉናል። ተቀላቀሉ https://www.facebook.com/ethiopia.lecturers?mibextid=ZbWKwL