fa
Feedback
Development Bank of Ethiopia (DBE)

Development Bank of Ethiopia (DBE)

رفتن به کانال در Telegram

The development bank of Ethiopia (DBE) is one of the financial institutions engaged in providing short, medium and long term development credits.

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Development Bank of Ethiopia (DBE)

کانال Development Bank of Ethiopia (DBE) (@dbe1900) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 22 822 مشترک است و جایگاه 5 453 را در دسته اقتصاد و امور مالی و رتبه 1 472 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 22 822 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 21 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -284 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -12 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.41% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.83% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 062 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 787 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 6 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
The development bank of Ethiopia (DBE) is one of the financial institutions engaged in providing short, medium and long term development credits.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 22 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اقتصاد و امور مالی تبدیل کرده‌اند.

22 822
مشترکین
-1224 ساعت
-897 روز
-28430 روز
آرشیو پست ها
ሚሽን 300 ዓለም ላይ 655 ሚሊየን ሰዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ አይደሉም። ከዚህ ውስጥ 560 ሚሊየኑ በአፍሪካ፣ በተለይም ከሰሃራ በታች ባለው ክፍል ይገኛሉ። የምድሪቱ 86 ከመቶ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እጦት መዳረሻው አፍሪካ ነው ይላል ከወር በፊት በዓለም ባንክ ገፀ-ድር ላይ የተነበበው ጥናታዊ አኃዝ ፡፡ የችግሩ ስፋት እና የመሠረተ ልማቱ ውድ መሆን ለመፍትሔው ተጨማሪ የፋይናንስ ምንጭ እንዲኖር የሚያስገድድ ነው። ከቁጥር በላይ የሆነው ይህ ችግር ለአንድ ውጥን መነሻ ሆኗል፤ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የዓለም ባንክ ደግሞ ባለቤቶቹ ናቸው። ባንኮቹ ከሁለት ዓመት በፊት መንግሥታት ይህን ችግር ለመቅረፍ ሲሠሩ "ፋይናንስ እናቅርብ" የሚል ሐሳብ ይዘው ብቅ አሉ፤ እቅዱ እ.ኤ.አ. እስከ 2030 ከሰሃራ በታች የሚኖሩ 300 ሚሊዮን ሰዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ማድረግ ነው። ለዚህም የዓለም ባንክ 250 ሚሊዮን፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ ደግሞ 50 ሚሊዮን ዶላር በማዋጣት ለ300 ሚሊየን ሰው ብርሃን የሚሆን በጀት ያዙ። የበጀቱም ሆነ የተጠቃሚው ቁጥር ስለገጠመ የፕሮጀክቱ ስያሜ «ሚሽን 300» ሆነ። በአፍሪካ ውስጥ ያለውን የኃይል አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ እና ለአነስተኛና መካከለኛ ቢዝነሶች፣ ትምህርት ቤቶች፣ እና ጤና ጣቢያዎች አስተማማኝ የመብራት አቅርቦት ማድረስ የፕሮግራሙ ዝርዝር ግብ ነው። የመብራት መስመር ዝርጋታ (Grid Expansion) እና የታዳሽ ኃይል አማራጮችን (እንደ የፀሐይ፣ የንፋስ እና አነስተኛ የኃይል ማመንጫዎች) ማካተት ደግሞ ቴክኒካዊ ሥራው ነው። በጀቱ ቅይጥ ፋይናንስ (Blended Financing) ዓይነት ሲሆን እርዳታን፣ ቀላል ብድርን እና የግል ኢንቨስትመንትን ያጣመረ ነው። የአፍሪካ ልማት ባንክ በዚህ ረገድ በዘላቂ ኃይል ፈንድ በኩል ለአፍሪካ አገራት የአረንጓዴ ሃይድሮጅን ፕሮጀክቶች ቅድመ-ኢንቨስትመንት ድጋፍ የሚውል 20 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ጥሪ አስተላልፏል። ለግብፅ ደግሞ ከፀሐይ ኃይል ማመንጫ እና ባትሪ ማከማቻ የሚሆን የ66 ሚሊዮን ዶላር ብድር አጽድቋል። ባንኩ ከሰሞኑ ለኢትዮጵያ የ110 ሚሊዮን ዶላር ብድር አጽድቋል። ገንዘቡ በግል እና በመንግሥት አጋርነት ማዕቀፍ ለሚገነባው ለአይሻ-1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሚውል ነው። ይህም በግሉ ዘርፍ የሚመራ የታዳሽ ኃይል ኢንቨስትመንት በመሆኑ በአይነቱ ቀዳሚ ያደርገዋል። ፕሮጀክቱ 300 ሜጋ ዋት ኃይል የሚያመነጭ ሲሆን፣ በ25 ዓመታት የአገልግሎት ዘመኑ 1.39 ሚሊዮን ቶን የሚጠጋ የካርቦን ልቀትን ይከላከላል ተብሎ ይጠበቃል። ኢትዮጵያ በውኃ፣ በፀሐይ፣ በንፋስ እና በጂኦተርማል የታዳሽ ኃይል ልማት መስክ ሰፊ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ያለች ሀገር ነች። ሀገራችን ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፕሮግራም ያላት ሲሆን፣ እ.ኤ.አ. በ2030 ሁሉን አቀፍ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ግብ ይዛ እየሠራች ነው። የአፍሪካ ልማት ባንክ የ110 ሚሊዮን ዶላር የብድር አቅርቦት ይህን ግብ ከማሳካት አኳያ ለመንግሥት ተጨማሪ አቅም ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ደግሞ ተጨማሪ አቅም ይዞ እየመጣ ነው። ባንኩ በሪፎርም ከያዛቸው አዳዲስ የፋይናንስ እሳቤዎች አንዱ ግሪን ፋይናንስ (Green Finance) ነው። ግሪን ፋይናንስ ለአካባቢ ጥበቃ፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት የሚደረግ የፋይናንስ አቅርቦት ነው። ታዳሽ ኃይል፣ አረንጓዴ ትራንስፖርት፣ ዘላቂ የደን ልማትና እንክብካቤ እንዲሁም የኃይል ቆጣቢነት ላይ ትኩረት ያደርጋል። ግሪን ፋይናንስ በአረንጓዴ ቦንዶች (Green Bonds) ፣ በአረንጓዴ ብድሮች (Green Loans) እና በካርቦን ገበያ (Carbon Markets) በተሰኙ ሦስት ዋና ዋና መንገዶች የፋይናንስ አቅርቦት ያደርጋል። ይህም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፣ የተፈጥሮ ሀብትን ለመጠበቅ እና በአረንጓዴ ቴክኖሎጂዎችና ኢንዱስትሪዎች ዙሪያ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር ሰፊ ዕድል የሚፈጥር የፋይናንስ አሰራር ነው። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ «የልማትዎ አጋር!» የሚለውን መሪ ቃል ሁልጊዜም በልኩ እና በደርዙ ይፈጽማል የሚባለው ለዚህ ነው። እንደ ጊዜው እና እንደ ቴክኖሎጂው እድገት ባንኩ ሪፎርም ያደርጋል። ለሀገር የሚገቡ አዳዲስ አሰራሮችና ቴክኖሎጂዎችን ያመጣል፣ ያላምዳል፤ የንግድ ባንኮች በማይደፍሯቸው የልማት መስኮች የስጋት አደጋዎችን ተቋቁሞ የረጅም ጊዜ የፋይናንስ ምንጭ ይሆናል። አሁንም ሀገር ለምትከተለው የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ግሪን ፋይናንስን ይዞ እየመጣ ነው። #DBE #greenenergy# #africandevelopentbank #bankloan #GreenBond

የጀርመን ልማት ባንክ (KfW) ከአረንጓዴ ቦንዶች ሽያጭ 12.6 ቢሊየን ዩሮ ገቢ አገኘ። ባንኩ ገቢውን ያገኘው በስድስት የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች ከሸጣቸው አስራ አንድ አረንጓዴ ቦንዶች ነው። እያ
የጀርመን ልማት ባንክ (KfW) ከአረንጓዴ ቦንዶች ሽያጭ 12.6 ቢሊየን ዩሮ ገቢ አገኘ። ባንኩ ገቢውን ያገኘው በስድስት የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች ከሸጣቸው አስራ አንድ አረንጓዴ ቦንዶች ነው። እያንዳንዳቸው 5 ቢሊየን ዩሮ መጠን ያላቸው ሁለት ትልልቅ ቦንዶች ለገቢው ማደግ ተጠቃሽ ናቸው። ባንኩ የፋይናንስ ማሰባሰብ ገቢውን በዓመቱ ሁለተኛ መንፈቅ እስከ 27 ቢሊየን ዩሮ ለማሳደግ ያቀደ ሲሆን፣ ዩሮ እና የአሜሪካ ዶላር ደግሞ ዋናውን ድርሻ ይይዛሉ። የጀርመን ልማት ባንክ የአረንጓዴ ቦንድ ስትራቴጂያዊ ማዕቀፉን እ.ኤ.አ. ከ2024 ጀምሮ አሻሽሎ ሥራ ላይ ያዋለ ሲሆን፣ ከገቢ ባለፈ ለአረንጓዴ ሀብቶች አጠቃቀም ሰፊ ዕድል እንደፈጠረ በድረ-ገጹ አስነብቧል። አረንጓዴ ቦንድ (Green Bond) ለአካባቢ ጥበቃ እና ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ለሚውሉ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ የሚሆን ገንዘብ ከባለሀብቶች ወይም ከኢንቨስተሮች ለመሰብሰብ የሚወጣ የብድር ሰነድ ነው። ቦንዱ በመንግሥታት፣ በልማት ባንኮች እና በግል ኩባንያዎች በኩል ሊቀርብ ይችላል። አረንጓዴ ቦንድ ዓላማው እንጂ ልዩ አሰራሩ እንደ መደበኛ ቦንድ ነው። ኢንቨስተሮች ቦንዱን ሲገዙ ለተወሰነ ጊዜ ገንዘብ ያበድራሉ፤ ሰጪው አካል ደግሞ በየጊዜው የተወሰነ የወለድ መጠን እየከፈለ የቦንዱ ጊዜ ሲጠናቀቅ ዋናው ገንዘብ የሚመለስ ይሆናል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አረንጓዴ ቦንድን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ይገኛል። ቦንዱ ሥራ ሲጀምር ሀገር ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ እና ለታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች ተጨማሪ የገንዘብ ምንጭ እንድታገኝ የሚያስችል ነው፡፡

Development Bank of Ethiopia Exchange rate, Applicable Wednesday , July 22, 2026 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚሰጣቸውን እለታዊ የውጭ ምንዛሪ አገልግሎት
Development Bank of Ethiopia Exchange rate, Applicable Wednesday , July 22, 2026 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚሰጣቸውን እለታዊ የውጭ ምንዛሪ አገልግሎት ለማግኘት ካዛንችስ ጆሴፍ ብሮዝ ቲቶ መንገድ በሚገኘው የዋና መስሪያ ቤት ኮርፖሬት ቅርንጫፍ ጎራ ይበሉ፡፡ ለተጨማሪ መረጃ፡- ዘወትር በስራ ሰዓት በስልክ ቁጥር 0115546495 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡ ከባንካችን የሚለቀቁ ማናቸውንም መረጃዎች ለማግኘት የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን:: ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/dbethiopia የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የልማት አጋርዎ! #exchangerate #DBE #Ethiopia

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የልማት አጋርዎ!
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የልማት አጋርዎ!

Development Bank of Ethiopia Exchange rate, Applicable Tuesday, July 21, 2026 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚሰጣቸውን እለታዊ የውጭ ምንዛሪ አገልግሎት ለማግ
Development Bank of Ethiopia Exchange rate, Applicable Tuesday, July 21, 2026 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚሰጣቸውን እለታዊ የውጭ ምንዛሪ አገልግሎት ለማግኘት ካዛንችስ ጆሴፍ ብሮዝ ቲቶ መንገድ በሚገኘው የዋና መስሪያ ቤት ኮርፖሬት ቅርንጫፍ ጎራ ይበሉ፡፡ ለተጨማሪ መረጃ፡- ዘወትር በስራ ሰዓት በስልክ ቁጥር 0115546495 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡ ከባንካችን የሚለቀቁ ማናቸውንም መረጃዎች ለማግኘት የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን:: ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/dbethiopia የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የልማት አጋርዎ! #exchangerate #DBE #Ethiopia

የጨረታ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90፣216/91 እና 1147/2011 መሰረት በብድር ዕዳ ምክንያት የተረከበውን ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተዘረዘረውን ንብረት በድርድርድ
+1
የጨረታ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90፣216/91 እና 1147/2011 መሰረት በብድር ዕዳ ምክንያት የተረከበውን ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተዘረዘረውን ንብረት በድርድርድ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። ዝርዝር መረጃውን እሁድ ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ/ም የወጣውን አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ያገኙታል፡፡

ግሪን ፋይናንስ (Green Finance) እንዴት? የአየር ንብረት ትንተና የሚሰራው ክላይሜት ፖሊሲ ኢኒሼቲቭ (CPI) አምና ባወጣው ሪፖርት ላይ፤ መላው ዓለም የኢኮኖሚ እድገቱን ከተፈጥሮ ጥበቃ ጋር ለማጣጣም 2.1 ትሪሊየን ዶላር አውጥቷል ይለናል። ይህ የገንዘብ መጠን «ግሪን ፋይናንስ» ወደሚል የመስኩ የላቀ ዕሳቤ እና ስያሜ ይመራናል። የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፣ አካባቢን ለመጠበቅ እና ዘላቂ ልማትን ለማምጣት ለሚሰሩ ፕሮጀክቶች የሚውል የገንዘብ አቅርቦት፤ አረንጓዴ ፋይናንስ (Green Finance) የዳቦ ስሙ ነው። ይህ አረንጓዴ መላ ወደ ፋይናንስ ዘርፍ ብቅ ያለባቸው ሦስት ዋና ዋና የታሪክ እጥፋቶች አሉ፡- 1. የ1970ዎቹ የስቶኮልም ኮንፈረንስ፡- ቀዳሚው ነው። በወቅቱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአካባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ እድገት መያያዝ ይኖርባቸዋል የሚል ምክክር ጀመረ። 2. የ2007ቱ የመጀመሪያው አረንጓዴ ቦንድ፡- የዓለም ባንክ ከስዊድን ባንኮች ጋር በመተባበር እ.ኤ.አ በ2007 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ "አረንጓዴ ቦንድ" (Green Bond) ለገበያ አቀረበ። ይህ ቦንድ የተዘጋጀው የአየር ንብረት ለውጥን ለሚቋቋሙ ፕሮጀክቶች የሚሆን ገንዘብ ለማሰባሰብ ነበር። 3. የ2015ቱ የፓሪስ የአየር ንብረት ስምምነት (Paris Agreement)፡- ነገሩን የውዴታ ግዴታ ሳያደርገው እንዳልቀረ ይታመናል። ስምምነቱ ሀገራት የዓለምን ሙቀት ለመቀነስ የገንዘብ ፍሰታቸውን ወደ አረንጓዴ ፕሮጀክቶች ለማዞር ፊርማቸውን አሳርፈውበታልና። የግሪን ፋይናንስ መተግበሪያ ሦስት ዋና መንገዶች በየትኛውም መመዘኛ ተመራጭ የሆነው ግሪን ፋይናንስ በሦስት ዋና መንገዶች ይሠራል፡- • አረንጓዴ ቦንድ (Green Bonds)፦ መንግሥታት ወይም ትልልቅ ኩባንያዎች ለአካባቢ ጥበቃ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ የሚሆን ገንዘብ ከባለሀብቶች የሚበደሩበት መንገድ ነው። • አረንጓዴ ብድር (Green Loans)፦ ባንኮች ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ ቤቶችን ለሚገነቡ፣ የፀሐይ ኃይል ለሚገጥሙ ወይም ለአረንጓዴ ቢዝነሶች የሚሰጡት ቅናሽ ያለበት ብድር ነው። • የካርቦን ገበያ (Carbon Market)፦ የካርቦን ልቀትን የቀነሱ አካላት (ከፍተኛ የደን ልማት ያካሄዱ) ያተረፉትን የካርቦን ክሬዲት ልቀት በመሸጥ ገንዘብ የሚያገኙበት ሥርዓት ነው። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና ግሪን ፋይናንስ ምንግዜም ለአዳዲስ እሳቤ እና ወቅቱን ለዋጀ አካሄድ ቀዳሚ የሆነው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣ ይህን ግሪን ፋይናንስ ለመተግበር ዝግጅት ላይ ነው። ባንኩ እያካሄደ ባለው ሪፎርም ግሪን ፋይናንስን አንደኛው ምሰሶ አድርጎታል። ይህ የገዘፈ ሐሳብ በዚህ አጭር መረጃ አዘጋጅ ዕይታ በአራት ነጥቦች ተገቢና ልክ ይሆናል፡- •ቀዳሚው ነገር ልማት ባንክ መቼም ቢሆን ተራማጅና መጪውን ጊዜ ግምት ውስጥ ያስገባ የሪፎርም የሥራ ባህል ያዳበረ መሆኑ። •ግሪን ፋይናስ ሐሳብ መቼም ቢሆን የማይነጥፍና ሉላዊ ተቀባይነቱ በኃያላን ሀገራት ጭምር በስምምነት መታቀፉ። •እንደ አንድ ቢዝነስ ገበያው በትሪሊየን ዶላር የሚቆጠር መሆኑና በማያቋርጥ ዕድገት መቀጠሉ፡፡ •ኢትዮጵያችን የምትከተለው የአረንጓዴ ዐሻራ እሳቤ እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እየተከተለችው ያለችው የግሪን ኢነርጂ ልማት ተጠቃሾች ናቸው ። #DBE #Ethiopia #GreenFinance #greenbonds

ኢትዮጵያ ልማት ባንክ ስፖርት ቡድን በኢሰማኮ የቼዝ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌድሬሽን (ኢሰማኮ) አገር አቀፍ የስፖርት ውድድር ትናንት ተጠናቋል።
+7
ኢትዮጵያ ልማት ባንክ ስፖርት ቡድን በኢሰማኮ የቼዝ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌድሬሽን (ኢሰማኮ) አገር አቀፍ የስፖርት ውድድር ትናንት ተጠናቋል። በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም በተካሄደው በዚህ ውድድር፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የስፖርት ቡድን በቼዝ ጨዋታ የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል። በባንኩ የሠራተኛ ማኅበር ሥር የተቋቋመው ይህ የጤና ስፖርት ቡድን፣ በቼዝ ካገኘው የዋንጫ አሸናፊነት በተጨማሪ በአትሌቲክስ የሜዳሊያ፣ እንዲሁም በእግር ኳስና በቴኒስ ውድድሮች የደረጃ ውጤቶችን በማስመዝገብ ውድድሩን በድል አጠናቋል። የባንኩ የሠራተኛ ማኅበር ፕሬዚዳንትና የጤና ቡድኑ መሪ አቶ ዮሴፍ ተስፋዬ እንደገለጹት፤ ይህ ዓመታዊ ውድድር በተለያዩ የሥራ ዘርፎችና ደረጃዎች ላይ ያሉ ሠራተኞችን በስፖርታዊ መንፈስ ከማሰባሰቡ ባሻገር፣ የባንኩን ስምና አርማ ከፍ አድርጎ ለማሳየት ትልቅ እገዛ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የልማት አጋርዎ! #DBE#Ethiopia#bankloan#Bank#ExchangeRate
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የልማት አጋርዎ! #DBE#Ethiopia#bankloan#Bank#ExchangeRate

Development Bank of Ethiopia Exchange rate, Applicable Monday, July 20, 2026 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚሰጣቸውን እለታዊ የውጭ ምንዛሪ አገልግሎት ለማግኘ
Development Bank of Ethiopia Exchange rate, Applicable Monday, July 20, 2026 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚሰጣቸውን እለታዊ የውጭ ምንዛሪ አገልግሎት ለማግኘት ካዛንችስ ጆሴፍ ብሮዝ ቲቶ መንገድ በሚገኘው የዋና መስሪያ ቤት ኮርፖሬት ቅርንጫፍ ጎራ ይበሉ፡፡ ለተጨማሪ መረጃ፡- ዘወትር በስራ ሰዓት በስልክ ቁጥር 0115546495 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡ ከባንካችን የሚለቀቁ ማናቸውንም መረጃዎች ለማግኘት የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን:: ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/dbethiopia የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የልማት አጋርዎ! #exchangerate #DBE #Ethiopia

መልካም የሥራ ሳምንት! ....... የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የልማት አጋርዎ! የኢትዮጵያ ልማት ባንክትክክለኛ የማሕበራዊ ትስስር ገጾች ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et (http://www.dbe.c
መልካም የሥራ ሳምንት! ....... የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የልማት አጋርዎ! የኢትዮጵያ ልማት ባንክትክክለኛ የማሕበራዊ ትስስር ገጾች ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et (http://www.dbe.com.et/? ለተጨማሪ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0115546495 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

ኢጃራ (ሊዝ) ፋይናንሲንግ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኢጃራ ፋይናንስ የሚያደርጋቸው የኢኮኖሚ ዘርፎች:-
ኢጃራ (ሊዝ) ፋይናንሲንግ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኢጃራ ፋይናንስ የሚያደርጋቸው የኢኮኖሚ ዘርፎች:-