ሁዘይፋ ኢብኑል የማን የሴቶች ጀመዐ
ይህ ቻናል የሁዘይፋ ኢብኑል የማን የሴቶች ጀመዐ ትክክለኛ ቻናል ነው:: በዚህ ቻናል ጀመዐው በምግብ, በገንዘብም ሆነ በቁሳቁስ ለሚረዳቸው ሰዎች የሚያግዙ አህለል ኸይሮች መረጃ የሚያገኙበት ነው::
نمایش بیشتر199
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-330 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
🌟الله اكبر 🌟الله اكبر 🌟الله اكبر
🌟ولله الحمد
🌙تقبل الله منا ومنكم جميع صالح الأعمال
وتجاوز ما كان من تفريط ونقصان
وجمعنا في الجنة مع النبيين والأبرار
✨عيدكم مبارك .💫 عيد سعيد✨
Eid Mubarak.
Photo unavailableShow in Telegram
🌟ረመዷን 21,1445ዓ.ሂ🌙
✨መጋቢት 22,2016E.C
✨march 31,2024G.C
✨أسلام عليكم ورحمة الله وبركاته
🌺ምስጋና ለአለማቱ ጌታ የተገባ ነው። እንደሚታወቀው የሁዘይፋ ኢብኑል የማን የሴቶች ጀመዐ በውስጡ ባቀፋቸው ዘርፎች አማካኝነት የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል። በዚህ በተከበረው የረመዷን ወር እንዲሁም በረከቱ ሰፊ በሆነበት በአስርቱ ቀናት ጅማሬ ላይ ደግሞ ለ130 ምስኪኖች ኢፍጣርን በማዘጋጀት ተደራሽ አድርጓል።
✨قال رسول اللهﷺ
"مَن فَطَر صاٸمًا کانَ لَهُ مثلَ أجرِهِ غیرَ أنَّهُ لا ینقُصُ من أجرِ الصَّاٸمِ شیٸًا"
✨"አንድን ፆመኛ ያስፈጠረ ሰው ከጿሚው አጅር(ምንዳ)ምንም ሳይቀነስ ልክ እንደ ጿሚው አጅር ይኖረዋል"
( ሀቢቡና ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም )
✨ ለዚህ መልካም ስራ ትልቁን ድርሻ የወሰደው እና ለዚህ መልካም ስራ ምክንያት ለሆነልን አህለል ኸይር ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን፣መልካም የሆነን ምንዳ ይመንዳው፣ዱንያውን አበጃጅቶ አኼራውን ያሳምርለት።አሚንን
✨ይህንን ስራ ሀላፍትናውን በመውሰድ፤ጊዜ እና ጉልበታቹን መስዋዕት በማድረግ በሰዐቱ እንዲደርስ ደፋ፣ቀና ላላቹ የሁዘይፋ ኢብኑል የማን የሴቶች ጀመዐ አባላት ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳቹህ፤በመልካሙም ይመንዳቹህ።
✨በዚህ መልካም ስራ ላይ መሳተፍ ለምትፈልጉ በራችን ክፍት ነው።
✨ለበለጠ መረጃ @Niemtullah ላይ ጥያቄያችሁን እንዲሁም ሀሳብ አስተያየታችሁን ማካፈል ትችላላቹህ።
✅قال رسول الله ﷺ اتقوا النار ولو بشق تمرة.
🌟በተምር ክፋይም ቢሆን እሳትን ተጠንቀቁ (ረሱል ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም)
👍 6
የኛ በሆነው umma life መጥተናል በኛው በኛው በተሰራው umma life ብዙሀንን ምንዳ እናቋድስ
ፎሎው በማድረግ የበኩልዎን ይወጡ
https://ummalife.com ይህን ሊንክ ተጠቅመው አካውንት በመክፈት ፎሎው ያድርጉን👇👇
https://ummalife.com/HuzeyfaIbnulYemanYesetochJemma
#umma life
#muslim's social midea
#umma life for all muslims
Muslim Social Web | Muslim Social Network
One Ummah — One Network - was created as a response to the Internet technology needs of Muslims and all adherents of traditional value
Repost from 🇸🇦يونس ابن حسن🇸🇦
Photo unavailableShow in Telegram
#የማይቀርበት_ቀጠሮ!
🌸የፊታችን እሁድ ቀራንዮ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ የሚገኘው #ሁዘይፈቱ_ኢብነል_የማን መስጂድ ከጠዋቱ 3፡00 ሰአት ጀምሮ በተወዳጅ ኡስታዞቻችን ዳዕዋ ትደምቃለች።
🌸ተወዳጆቹ ኡስታዝ #ሙባረክ_ኑሪና ኡስታዝ #አብዱራህማን_ዒልማ በሚጣፍጠው አንደበታቸው የዳዕዋ ፕሮግራም በአሏህ ፈቃድ ያቀርባሉ።
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
🌺ለሴቶች ምቹና በቂ ቦታ ተዘጋጅቷል።
https://t.me/abufurat
https://t.me/abufurat
🌙رمضان مبارك⭐
اسأل الله أن یجعله شهر الرحمة ومغفرة لنا ولکم
ویبارك لنا فیه ویتقبل منا أعمالنا وصیامنا وقیامنا
☀شهرکم مبارك⭐
ረመዳን ሙባረክ!
የታላቁ የመረዳን ፆም ነገ ሰኞ MARCH11 አንድ ብሎ እንሚጀመር ተገለፀ
እንኳን ለታላቁ የረመዳን ወር በሰላም አደረሰን
በሳውዲ አረቢያ የረመዳን ወር መግቢያ ጨረቃ በመታየቷ የረመዳን ወር ነገ ሰኞ march 11 እንደሚጀምር ታውቋል::
ረመዳን ሙባረክ!
አላህ ሃቁን ጠብቀው የሚፆሙት ያድርገን!
አሚን!
Photo unavailableShow in Telegram
በስራ ውጥረት ጊዜ በማጣት፣ በመዘናጋትና በተለያዩ ምክንያቶች ቁርዐንን ከማንበብ ተዘናግተን ይሆናል። ግን ምን ያህሎቻችን ነን ቁርዐንን ስናነብ ትርጉሙን አወቅንም አላወቅንም በእያንዳንዱ ሀርፍ(ፊደል) ሀሰናት እንደሚፃፍልን የምናውቀው????
እኔ ግን ዛሬ እናንተ ሳታነቡ አጅር የምታፍሱበትን መንገድ ልጠቁማችሁ ነው ...
አሽረፈል ኸልቅ ነቢዩና ሰለላሁ ዐለይሂ ወሠለም እንዳሉት
من دل على خير فله مثل أجر فاعله.
ትርጉሙ: ወደመልካም ያመላከተ ለአመላካቹ የሠሪው አጅር ከሠሪው ሳይቀነስ ይፃፍለታል።
በወለጋ የሚገኙ ቁርዐንን ማግኘት እየናፈቁ ላላገኙ ወንድሞች እና እህቶች የምንችለውን መጠን ያህል ቁርዐን በመነየት እነሱ ቁርዐንን ባነበቡ ቁጥር እኛም እጥፍ ድርብ የሆነን ምንዳ ብንሸምትስ???
በገንዘብ ለመነየት
አዋሽ ባንክ: 01425674688200 ረሂማ ሙስጠፋ, ሂክማ መሀመድ, ሙና ሁሴን
ንግድ ባንክ: 1000569560617 ሂክማ ቶፊቅ ለጋ
አቢሲኒያ ባንክ: 87006921 ነኢማ ነስሩ ጀማል
የላካችሁበትን ደረሰኝ :- @Sualihattt ወይም @a_metl ወይም @NimetGraphics ላይ ይላኩ
በአካል ለመስጠት
አድራሻ: ቀራንዮ የሺደበሌ ከፍ ብሎ በሚገኘው ሁዘይፋ ኢብኑል የማን መስጂድ ብቅ ብለው የበኩልዎን ያበርክቱ
የእህታችን መኖሪያ ይህን ይመስላል ምናልባት ይህን ቤት ቀና ለማድረግ አንድ ሠው ሊበቃ ይችላል ከቻልን እየነየትን ካልቻልን ለሚችሉ ሼር በማድረግ የበኩላችንን እንወጣ
ሁዘይፋ ኢብኑል የማን የሴቶች ጀመዐ
✨أسلام عليكم ورحمة الله وبركاته
🌺ምስጋና ለአለማቱ ጌታ የተገባ ነው። እንደሚታወቀው የሁዘይፋ ኢብኑል የማን የሴቶች ጀመዐ በውስጡ ባቀፋቸው ዘርፎች አማካኝነት የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል ከነዚህ ዘርፎች መሀከል ዚያራ ሴክተር ግንባር ቀደሙ ነው።
#⃣ይህ ሴክተር በተለያዩ ቦታ የሚገኙ፤የሰው ፊትን ፈርተው ቤት ውስጥ ለተሸሸጉ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ድጋፍን ያደርጋል።50 ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ ለ 50 ሰው ግን ጌጡ ነው እና ከተባበርን ኢንሻአላህ ለብዙዎች እንደርሳለን።
#⃣ዕለተ ቅዳሜ የካቲት 16, 2016 በተደረገው ዚያራ ላይ የተሳተፋቹ የሁዘይፋ ኢብኑል የማን የሴቶች ጀመዐ አባላት በአጠቃላይ ከልብ እናመሰግናለን።
የዛሬው ባለታሪካችን እህት ፈቲያ ስትሆን የ4 ልጆች እናት ናት።አባታቸው ጥሏቸው በመሄዱ ልጆቿንም ለብቻዋ በማሳደግ ላይ ትገኛለች፤ በዚህ ጊዜ ኑሮ በከበደበት ሰዐት ያለ ደጋፊ ኑሮን መምራት በመክበዱ ሶስቱ ልጆቿ ትምህርታቸውን አቋርጠዋል፤ይህም የሆነበት ምክንያት ደግሞ የእናታቸው በተደጋጋሚ መታመም ነው።ሁለተኛ ልጇ የ14 አመት ታዳጊ እና የ 6ተኛ ክፍል ተማሪ ነበር።ነገርግን በእናቱ ተደጋጋሚ ህመም ምክንያት እና አሁን ያሉበት ቤት ለመውደቅ የተቃረበ በመሆኑ ከትምህርት ገበታው ርቆ ስራ በመፈለግ ላይ ነው፤
ከእናታቸው መታመም ሰበቡ ላያቸው ላይ ሊውድቅ የደረሰው በሸራ ከታጠረው መኖሪያ ቤታቸው የሚገባው ብርድና ውርጭ ነው።የሌሊቱን ብርድ ችለው በጋውን እንደምንም ተቋቁመው ያልፉታል፤ክረምቱ ግን በጣም ከባድ እና አሳሳቢ ነው።የሚጠለሉበት ሸራ ቤት ለመውደቅ ከመቅረቡም ጋር ጎርፍ ያስገባል፣ከእናት ህመም ጋር ተጨምሮ የክረምት መምጣት የልጆች አንድ ሀሳብ ሆኗል።ህመሟን የምታስታምምበት፣ልጆቿን ሰብስባ እረፍት የምታደርግበትን ለሷም ለልጆቿም ሰላም የሚሆናትን ማረፊያ ታገኝ ዘንድ ሁላችንም የበኩላችንን እንወጣ።
እንደሚታወቀው ከቀናቶች በኋላ ታላቅ እንግዳን እንቀበላለን።ይህ ወር ምንዳዎች በእጥፍ የሚባዙበት ነው፤ታዲያ በዚህ ወር እኛም ከምንዳው ተቋዳሽ እንሆን ዘንድ፤ልጆቿም ወደ ትምህርት ገበታቸው ይመለሱ ዘንድ፣ለእናታቸውም እረፍት ይሰማት ዘንድ በምንችለው እንረባረብ፣
እህት ፈቲያን
✅በገንዘብ
✅በእህል
✅በአልባሳት
መደገፍ ለምትፈልጉ +251930594583 በመደወል የጀመዐውን በይተል ማል ማናገር ትችላላቹህ።
➡️ለበለጠ መረጃ @Niemtullah ላይ ጥያቄያችሁን ማቅረብ ትችላላቹህ፤
➡️በአካል መጥታቹም፣ያሉበት ሁኔታን አይታቹ ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉም በራችን ክፍት ነው።
#⃣ስለምታደርጉትም ድጋፍ በአላህ ስም እናመሰግናለን።
✅قال رسول الله ﷺ اتقوا النار ولو بشق تمرة.
በተምር ክፋይም ቢሆን እሳትን ተጠንቀቁ ። (ረሱል ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም)
Photo unavailableShow in Telegram
እንኳን ለ 1445ዓ.ሂ ወርሀ ረመዷን በሰላም አደረሳቹህ፣ወሩ የቁርዐን፣የሰደቃ፣የኢባዳ መሆኑ ይታወቃል።በወለጋ የሚገኙ ሙስሊሞች ቁርዐንን እየናፈቁ 1 ቁርዐን እንኳን ማግኘት የህልም እንጀራ ሆኖባቸዋል
ለነዚህ ወንድሞች እና እህቶች የምንችለውን መጠን ያህል ከቻልን በመግዛት ካልሆነ ደግሞ ቤት ካሉን ቁርዐኖች በመስጠት እጥፍ ድርብ የሆነን ምንዳ እንሸምት።
በገንዘብ ለመነየት
አዋሽ ባንክ: 01425674688200 ረሂማ ሙስጠፋ, ሂክማ መሀመድ, ሙና ሁሴን
ንግድ ባንክ: 1000569560617 ሂክማ ቶፊቅ ለጋ
አቢሲኒያ ባንክ: 87006921 ነኢማ ነስሩ ጀማል
የላካችሁበትን ደረሰኝ :- @Sualihattt ወይም @a_metl ወይም @NimetGraphics ላይ ይላኩ
በአካል ለመስጠት
አድራሻ: ቀራንዮ የሺደበሌ ከፍ ብሎ በሚገኘው ሁዘይፋ ኢብኑል የማን መስጂድ ብቅ ብለው የበኩልዎን ያበርክቱ
ለበለጠ መረጃ
+251 912 784 898 / +251 912 932 100
قال رسول الله ﷺ : من دل على خير فله مثل أجر فاعله.
ወደመልካም ያመላከተ ለአመላካቹ የሠሪው አጅር ከሠሪው ሳይቀነስ ይፃፍለታል:: (ረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሠለም)
ሁዘይፋ ኢብኑል የማን የሴቶች ጀመዐ
👍 3
یک طرح متفاوت انتخاب کنید
طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.