fa
Feedback
Mark Tech Info | Mark Technology Information

Mark Tech Info | Mark Technology Information

رفتن به کانال در Telegram

Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot

نمایش بیشتر
6 211
مشترکین
-524 ساعت
-317 روز
-30430 روز
آرشیو پست ها
Freshman Course ✅ 1st year students ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

FRESHMAN MOJULES ✅ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

አዲሱ የአጠቃላይ ትምህርት የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ዝውውር መመሪያ (ረቂቅ) ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‼️የአዲስ አበባ ተወላጇ በአሜሪካ ' የመጀመሪያዋ ጥቁር ሴት ' ተባለች የ28 አመቷ ረድኤት አበበ በኒውዮርክ ከሚገኘው ኮርኔል ዩኒቨርስቲ በዶክትሬት ዲግሪ በመመረቅ የመጀመሪያዋ ጥቁር ሴት የሚል ታ
‼️የአዲስ አበባ ተወላጇ በአሜሪካ ' የመጀመሪያዋ ጥቁር ሴት ' ተባለች የ28 አመቷ ረድኤት አበበ በኒውዮርክ ከሚገኘው ኮርኔል ዩኒቨርስቲ በዶክትሬት ዲግሪ በመመረቅ የመጀመሪያዋ ጥቁር ሴት የሚል ታሪክ አስመዘገበች፡፡ የአዲስ አበባ ተወላጅ የሆነችው ረድኤት በዩኒቨርስቲው በዶክትሬት የተመረቀችው በኮምፒውተር ሳይንስ ነው፡፡ እንደአትላንታ ብላክ ስታር ዘገባ ይህች ወጣት ዶክትሬቷን የሰራችው የኮምፒውተር ቀመርንና ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በእኩልነትና በማህበራዊነት እንዴት መጠቀም እንደሚቻል ባተኮረ ምርምር ላይ ነው፡፡ ረድኤት ከዚህም በተጨማሪ በሰው ሰራሽ ክህሎት ላይ የሚሰራው ኤን አይኤች አማካሪ ኮሚቴ ውስጥ አባል ስትሆን ብላክ ኢን ኤአይ የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ከመሰረቱት መካከልም ናት፡፡ የመመረቂያ ስራዋን በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እኩልነት ላይ ለመስራት የተነሳሳችው በትውልድ አገሯ ካየችው እውነታ በመነሳት እንደሆነ ተናግራለች፡፡ በአዲስ አበባ ከትልቅ ቪላ አጠገብ የላስቲክ ቤት እንደሚታይና የገቢ እኩልነት እንደሌለ መታዘቧን የገለፀችው ረድኤት ይህ በመላው አለም ያለ መሆኑን ስትረዳ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መስክ እንዳይደገም በማሰብ መመረቂያዋን በዚህ ላይ መስራቷን አስረድታለች፡፡ ረድኤት የመጀመሪያ ዲግሪዋን በማቲማቲክስ ያገኘችው ከሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ ሲሆን በካምብሪጅ ዩኒቨርስቲ በዚሁ ትምህርት ማስተርሷን ሰርታለች፡፡ በተጨማሪም ከሀርቫድር ዩኒቨርስቲ በአፕላይድ ማቲማቲክስ ሌላ ማስተርስ ያላት ናት፡፡ ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

" በጦርነቱ ምክንያት ወደኃላ ባልቀር አሁን የ4ኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነበርኩ " - ተማሪ ሙሴ ኪዳነ በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ ከ9,000 በላይ ተማሪዎች 657 በማም
+1
" በጦርነቱ ምክንያት ወደኃላ ባልቀር አሁን የ4ኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነበርኩ " - ተማሪ ሙሴ ኪዳነ በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ ከ9,000 በላይ ተማሪዎች 657 በማምጣት ከፍተኛውን ውጤት ያስመዘገበው የቀላሚኖ ት/ት ተማሪ ሙሴ ኪዳነ " መድረስ ከነበረብኝ የትምህርት ደረጃ ባለመድረሴ ዓመታት ከእድሜ ላይ ተሰርቋል " ሲል ገልጿል። የትግራይ #ሃውዜን ነዋሪ የሆነው ተማሪ ሙሴ አሁን ላይ እድሜው 22 ሲሆን ፤ ባስመዘገበው ከፍተኛ ውጤት ደስ መሰኘቱን ለክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግሯል። አስከፊው ጦርነት በይከሰትና ወደኃላ ባይቅር ኖሮ አሁን ላይ የ4ኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ እንደነበርም ገልጿል። ሙሴ ኪዳነ ፥ " አሁን የመጣው የፈተና ውጤት ጥሩ ነው። ደስም ብሎኛል ከውጤቱ ጋር አያይዤ ማለት የምፈልገው ሁሉም ሰው ያሰበውን ደረጃ ለመድረስ የሚያስችለውን ጥረት ካደረገ ማሳካት እንደሚቻል ማሳያ ነው። " ብሏል። መድረስ ከነበረበት የትምህርት ደረጃ ባለመድረሱ ዓመታት ከእድሜው እንደተሰረቀበት የሚገልፀው ተማሪ ሙሴ አሁን የሚገባውን ሁሉ የሚማርበት እድል ሊመቻች ይገባል ሲል ለትግራይ ቴሌቪዥን ተናግሯል። በትግራይ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ ከ9,000 በላይ ተማሪዎች 73.09 በመቶ የሚሆኑት የተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም 51.38 በመቶ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች በአጠቃላይ 66.96 በመቶ ተማሪዎች 50 በመቶና በላይ ውጤት በማምጣት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ አግኝተዋል። ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‼️657 ከፍተኛው ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል። በትግራይ ክልል በተሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና ከተፈተኑ ተማሪዎች መካከል 657 ከፍተኛው ሆኖ መመዝገቡ ታውቋል። ይህንን ከፍተኛ ውጤት
+1
‼️657 ከፍተኛው ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል። በትግራይ ክልል በተሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና ከተፈተኑ ተማሪዎች መካከል 657 ከፍተኛው ሆኖ መመዝገቡ ታውቋል። ይህንን ከፍተኛ ውጤት ያመጣው ተማሪ ሙሴ ኪዳነ የሚባል ሲሆን የ " ቀላሚኖ " የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመመልከት ችሏል። እንደ ትግራይ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ኪሮስ ጉዑሽ መረጃ አጠቃላይ መስፈርቱን አሟልተው ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች  73.09 በመቶ የሚሆኑ የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች  እንዲሁም 51.38 በመቶ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች በአጠቃላይ 66.96 በመቶ ተማሪዎች 50 በመቶና በላይ ውጤት በማምጣት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ አግኝተዋል። በትግራይ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በኃላም በደም አፋሳሹ ጦርነት ምክንያት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ርቀው መቆየታቸው የሚዘነጋ አይደለም። ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‼️በትግራይ ክልል ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች ውጤት ይፋ ሆነ በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ውጤት ዛሬ ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ ተፈታኞች ው
‼️በትግራይ ክልል ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች ውጤት ይፋ ሆነ በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ውጤት ዛሬ ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ ተፈታኞች ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሰታወቀ። በድረ ገጽ  eaes.et ላይ የመታወቂያ ቁጥራቸውንና የመጀመሪያ ስማቸውን በማስገባት ማየት እንደሚችሉ ገልጿል። በውጤቱ ላይ ቅሬታ ያለው ተፈታኝ በአካል መምጣት ሳያስፈልግ ድረ ገጽ ላይ እስከ ጥቅምት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11:30 ድረስ ማቅረብ  ይቻላል። በተመሳሳይ መልኩ ምላሽም ማግኘት የምትችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል። በክልሉ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ ም ድረስ በመቀሌ፣ በአክሱም፣ በዓዲግራት እና በራያ ዩኒቨርሲቲዎች መሰጠቱ ይታወሳል። ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‼️በአማራ ክልል በቀጠለው ግጭት ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ መደበኛ ሥራቸው በቅርቡ #እንደማይመለሱ የክልሉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ገለፀ፡፡ አስር ዩኒቨርሲቲዎችን በአባልነት የያዘው 'በአማራ ክልል የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም'፤ በክልሉ ባለው የፀጥታ ሁኔታና የመማር ማስተማር ሒደቱን በማስመልከት ውይይት አድርጓል፡፡ በዚህም "በክልሉ የሚገኙ አስሩም ዩኒቨርሲቲዎች የክልሉ የፀጥታ ሁኔታ እስከሚሻሻል ድረስ ተማሪዎቻቸውን እንደማይጠሩ የጋራ መግባባት ላይ መድረሳቸውን" የፎረሙ ዋና ፀሐፊ አስማረ ደጀን (ዶ/ር) ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ በክልሉ የሚታየውን የፀጥታ ስጋት ያብራሩት ዋና ፀሐፊው፤ ተማሪዎችን ወደየተቋማት አስገብቶ ግጭት በሚከሰትበት ወቅት ዩኒቨርሲቲዎች ኃላፊነት እንደማይወስዱ አንስተዋል፡፡ ለዚህም ባለፈው ሐምሌ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና እየወሰዱ በነበረበት ወቅት ተፈጥሮ የነበረውን ችግር ጠቅሰዋል፡፡ ተፈታኝ ተማሪዎች ረጅም ርቀት በራሳቸው በእግራቸው ተጉዘው ወደየመጡበት መመለሳቸውን አስታውሰዋል፡፡ በክልሉ ባለው የፀጥታ ሁኔታ የተማሪዎች የምግብ አቅርቦት ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ማድረስ ፈተና እንደሆነም ዋና ፀሐፊው ጠቁመዋል። ከምግብ ጀምሮ ለዩኒቨርሲቲዎች ልዩ ልዩ ግብዓቶችን ያቀርቡ የነበሩ አካላት፣ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ እንደማይችሉ መግለጻቸው ለፎረሙ ውሳኔ መሠረት እንደሆኑ ፀሐፊው አስረድተዋል፡፡ በፎረሙ ውይይት የተሳተፉት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ታፈረ መላኩ (ዶ/ር)፤ "በክልሉ በቀጠለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ዘንድሮ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ #እንደማይቻል" ገልጸዋል። የዩኒቨርሲቲዎቹ የምግብ አቅርቦት ከወረዳዎችና ከአዲስ አበባ የሚመጣ በመሆኑ፥ ይህም ትልቅ ፈተና እንደሆነ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል። መንግሥት ፎረሙ የሚጠይቀውን ሁኔታ ማመቻቸት ከቻለ ዩኒቨርሲቲዎቹ ተማሪዎቻቸውን ለመጥራት እንደሚችሉ ከስምምነት መደረሱን ዋና ፀሐፊው አስረድተዋል። የአሜሪካ ድምፅ የትምህርት ሚኒስቴርን በጉዳዩ ላይ ለማናገር ያደረገው ጥረት አልተሳካለትም። #VOA ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‼️የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆኗል በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስሥት ዩኒቨርሲቲዎች በወጪ
‼️የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆኗል በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስሥት ዩኒቨርሲቲዎች በወጪ መጋራት ትምህርታቸውን ለምትከታተሉ የቅድመ-ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ሆኗል። የተመደባችሁቀትን ተቋም በተከታዮቹ አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል፦ Website: https://result.ethernet.edu.et/ Telegram bot: @moestudentbot ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

የሬሜዲያል መቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደረገ። የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያላስመዘገቡ ነገር ግን ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣቸውን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡ በዚህም መሰረት በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 30 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም (210 ከ 700፣ 180 ከ 600 እና 150 ከ500) የተቆረጠ መሆኑ ተመላክቷል። ከላይ በተራ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የRemedial ፕሮግራም የሚከታተሉት የሚከተሉትን መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ ብቻ እንደሚሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ☑ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 255 ያመጡ ☑ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 234 ያመጡ ☑ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 218 ያመጡ ☑ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 200 ያመጡ ☑ ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 224 ያመጡ ☑ ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 210 ያመጡ ☑ ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 192 ያመጡ ☑ ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 180 ያመጡ ☑ አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 210 ያመጡ ☑ አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ700 ነጥብ 210 ያመጡ ☑ አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 180 ያመጡ ☑ አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ600 ነጥብ 180 ያመጡ ☑ ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ500 ነጥብ 150 ያመጡ ☑ ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ500 ነጥብ 150 ያመጡ መሆን አለባቸው ተብሏል። መረጃውን ትምህርት ሚኒስቴርን ዋቢ በማድረግ ያሰራጨው ኤፍ ቢ ሲ ነው። ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‼️የዩኒቨርስቲ ምደባ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ የተሰጠ ማብራሪያ የተማሪ ምደባ መስፈርቶች፡- 1. 1000
‼️የዩኒቨርስቲ ምደባ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ የተሰጠ ማብራሪያ የተማሪ ምደባ መስፈርቶች፡- 1.  1000 ለሚሆኑ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች፡- የምደባ ስርዓቱ በተፈጥሮም ሆነ በማህበራዊ ሳይንስ መስኮች 1000 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን  በመጀመሪያ የዩኒቨርስቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸው ምደባ የሚካሄድ ይሆናል። 2. ውጤት፡- የምደባ ስርዓቱ እያንዳንዱ ተማሪ ያስመዘገበውን አጠቃላይ ውጤት በምደባ ስርዓት ሂደት ውስጥ መለያ አድርጎ ይጠቀማል፡፡የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ሌሎች ተፈጻሚ የሚሆኑ ህግና ደንቦችን ባልጣሰ መልኩ ምርጫቸውን በመጠበቅ ረገድ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡ 3. የዩኒቨርሲቲ ምርጫ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የቅበላ አቅም ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ተማሪዎች 46 ዩኒቨርሲቲዎች ለምርጫ ቀርበውላቸዋል፡፡ መረጃው የተሰበሰበው https://portal.etherenet.edu.et ላይ ነው፡፡ 4. በተማሪዎች የተመረጡ ተቋማት ያላቸው የትምህርት ፕሮግራሞች ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች እና የተመረጡት ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የትምህርት ፕሮግራም መሰረት ያደረገ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ 5. ጾታ ፡- በተቋማት የጾታ ተዋጽኦን ለመጠበቅ በሚኖረው የምደባ ስርዓት የጾታ ተዋጽኦና ሚዛን እንዲጠበቅ ተደርጓል፣ ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‼️በ2015 ሬሚድያል ፈተና ተፈትናችሁ ላለፋችሁ ተማሪዎች!! " ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ወደ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተዛውሮ መማር አይቻልም " - ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ሚኒስቴ
‼️በ2015 ሬሚድያል ፈተና ተፈትናችሁ ላለፋችሁ ተማሪዎች!! " ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ወደ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተዛውሮ መማር አይቻልም " - ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ጥቅምት 9 ቀን 2016 ዓ/ም ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ በ2015  ትምህርት ዘመን የሬሜዲያል ትምህርት ተከታትለው 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡ ተማሪዎች የፍሬሽማን ኮርስ እንዲማሩ መወሰኑን አስታውሷል። በዚህም መሰረት ተማሪዎች ፦ - ከመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዛውሮ መማር እንደሚችሉ፤ - ከአንድ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ወደ ሌላ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተዛውሮ መማር እንደሚችሉ፤ - ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ወደ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተዛውሮ መማር #የማይችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስገንዝቧል። ተማሪዎች ከአንድ ተቋም ወደ ሌላ ተቋም ሄደው መማር የሚፈልጉ ከሆነ መረጃቸው በአግባቡ ተደራጅቶ እንዲሰጣቸው ትምህርት ሚኒስቴር በፃፈው ደብዳቤ አሳስቧል። ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‼SCHOLARSHIP በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ያለፋችሁና በምደባ ወቅት
‼SCHOLARSHIP በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ያለፋችሁና በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለምትሹ ተማሪዎች ማመልከቻችሁን በ https://student.ethernet.edu.et በኩል እስከ ጥቅምት 16/2016 ዓ.ም እንድታመለክቱ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። ምንም አይነት ማመልከቻ በአካል #የማይቀበል መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል።   ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

የዘንድሮ የዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምደባ ችሎታና ፍላጎታቸውን መሰረት ባደረገ መልኩ ይከናወናል -ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የዘንድሮ የዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምደባ ችሎታና ፍላጎታቸውን መሰረት ባደረገ መልኩ የሚከናወን እንጂ በማንም ተጽዕኖ የሚቀየር አይደለም ሲሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።   በ2014 የትምህርት ዘመን በመንግስትና በግል የሪሚዲያል ፈተና ከወሰዱ 145 ሺህ ተማሪዎች መካከል 90 ሺህ ያህሉ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት አስመዝግበዋል።   እነዚህ ተማሪዎች በ2015 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ካመጡት ከ27 ሺህ በላይ ተማሪዎች ጋር ተደምረው በአጠቃላይ ከ117 ሺህ በላይ ተማሪዎች ወደ ተለያዩ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ይመደባሉ ተብሎ ይጠበቃል።   ፕሮፌሰር ብርሃኑ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ የዘንድሮ የተማሪዎች ምደባ ችሎታቸውንና ፍላጎታቸውን መሰረት ባደረገ መልኩ በፍትሐዊነት እንደሚከናወን ገልጸዋል።   ቀደም ሲል በተማሪዎች ምደባ ላይ ይነሱ የነበሩ ቅሬታዎችን ታሳቢ በማድረግ ክፍተቶች ተለይተው እንዲስተካከሉ መደረጉንም አብራርተዋል።   በመሆኑም በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ተማሪዎች በችሎታቸውና በፍላጎታቸው መሰረት እንዲመደቡ ይደረጋል ነው ያሉት።   የህክምና ክትትል እያደረጉ መሆኑን ትክክለኛ ማስረጃ ከሚያቀርቡ ተማሪዎች ውጪ የዝውውር ጥያቄ ተቀባይነት እንደሌለውም ተናግረዋል።     አንዳንድ ግለሰቦች ምደባ ለማስቀየር ጥያቄ እንደሚያቀርቡ የተናገሩት ፕሮፈሰሩ የተማሪዎቹ ምደባ በማንም ተጽዕኖ ምክንያት ሊቀየር አይችልም ብለዋል።   ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‼️ተጠናቋል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ጋር በተያያዘ የተማሪዎች ቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ መጠናቀቁን አረጋግጧል፡፡ በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል
‼️ተጠናቋል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ጋር በተያያዘ የተማሪዎች ቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ መጠናቀቁን አረጋግጧል፡፡ በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ውጤት ላይ በስልክና በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ቅሬታ ላቀረቡ ተማሪዎች አገልግሎቱ ባለፉት ቀናት ምላሽ ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሷል፡፡ ይሁን እንጂ በተለያዩ አስገዳጅ ምክንያቶች በወቅቱ ቅሬታ ማቅረብ ያልቻሉ ተፈታኞች በአገልግሎቱ ለዚህ ሥራ ለተመደበ ክፍል ማቅረብ የሚችሉ መሆኑን እናሳውቋል፡፡ ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዛሬው የፓርላማ ቆይታቸው ስለ ሬሜድያል ከተናገሩት👇 💥አምና በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች #105,000 የሬሜዲያል ተማሪዎች ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፤ #63,033 ተማሪዎች አልፈዋል። 💥አምና በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት #44,500 የሬሜዲያል ተማሪዎች ትምህርታቸውን ተከታትለው፥ #27,587 የሚሆኑት አልፈዋል። 💥በአጠቃላይ #145,500 ተማሪዎች በሬሜዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው #90,620 አካባቢ ተማሪዎች ከሬሜዲያል ወደ ፍሬሽማን አልፈዋል። 🛟በዚህ ዓመት ፍሬሽማን የሚኖረው አምና በሬሜዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያለፉት #90,620 ተማሪዎች እና በ#2015 የኢንትራንስ ፈተና 50% እና ከዚያ በላይ ያመጡት #27,200 ተማሪዎች ናቸው። 💥ዘንድሮ በዩንቨርሲቲዎች(በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት) ውስጥ በአጠቃላይ የሚመደቡት #191,509 ተማሪዎች ሲሆኑ ከነዚያ ውስጥ በሬሜዲያል #164,242 ተማሪዎችን ይቀበላሉ።( የመንግስት እና የግል ተቋማት ላይ) 💥የተማሪዎች ምደባን በተመለከተ በምንም አይነት መልኩ አግባብ ያልሆነ በአድሎ ላይ የተመሰረተ ምደባ ሚባል ነገር እንደማይኖር አስረግጠው ተናግረዋል። ብቸኛው ከምደባ አሰራር በተለየ መልኩ የሚስተናገደው የህክምና አስገዳጅ ጉዳይ ሲኖር ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። የፕሮፌሰሩን ሰፋ ያለ ማብራሪያ ያድምጡ👇 https://youtu.be/fvT_05aux4o ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

በ12ኛ ክፍል ውጤት “ራቁታችንን ምን እንደምንመስል አይተነዋል” - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፤ የመስሪያ ቤታቸውን የዘንድሮ እቅድ እና የበጀት ዓመቱን የሩብ ዓመት አፈጻጸም ለማቅረብ ዛሬ ረቡዕ በፓርላማ ተገኝተው ነበር። የዛሬውን ስብሰባ በጠራው የተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለሚኒስትሩ ካቀረባቸው ጥያቄዎች መካከል የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን የሚመለከት ይገኝበታል። ከፈተናው ውጤት ጋር በተያያዘ ለቀረበላቸው ጥያቄዎች የሰጡትን ምላሽ መስማት የምትፈልጉ 👇 https://youtu.be/fvT_05aux4o ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

የተማሪዎች ክፍፍል እና መማር የሚችሉት ‼️ ✅ ከ50% በላይ ያመጡ ተማሪዎች በሙሉ በባቻቸው ፍሬሽማን ኮርስ ይጀምራል። በቅርቡ ወደ ተመረጡ 15 ዩኒቨርስቲወች ይመደባሉ። ✅ ከ50% በታች ያመጡ ተማ
የተማሪዎች ክፍፍል እና መማር የሚችሉት ‼️ ✅ ከ50% በላይ ያመጡ ተማሪዎች በሙሉ በባቻቸው ፍሬሽማን ኮርስ ይጀምራል። በቅርቡ ወደ ተመረጡ 15 ዩኒቨርስቲወች ይመደባሉ። ✅ ከ50% በታች ያመጡ ተማሪዎች ሶስት አማራጭ አላቸው 1) መንግስት የሚሰጠውን ሁለተኛ ዕድል /Remedial Program/ በመጠቀም የማካካሻ ትምህርት መውሰድ እና አንድ ባች ዝቅ ብሎ ፍሬሽማን መጀመር።(መቁረጫ ነጥብ ለሚያሟሉ) 💠 ከመንግስት ዩንቨርሲቲ ውጭ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የማካካሻ ትምህርት ተምረው የድግሪ መማሪያ ውጤት አምጥተው ቀጣይ ድግሪ መማር ይችላሉ። 2) ከቀጣይ ተፈታኞች(2016 ባች) ጋር በግል ድጋሚ መፈተን ይችላሉ 3)ቴክኒክና ሙያ መሰልጠን ይችላሉ። (መቁረጫ ነጥብ በቅርቡ) 💠በመንግስት ስፖንሰርነት ማካካሻ የሚወስዱ #የ100ሺህ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ በቅርብ ቀን ይፋ ይደረጋል።  💠እንድሁም አጠቃላይ በ Remedial ፕሮግራም እና በ ቴክኒክ እና ሙያ የሚያስገባውን መቁረጫ ነጥብ በቅርቡ ይፋ ይሆናል። ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

#ጥቆማ የ12ኛ ክፍል ትምህርታችሁን አጠናቃችሁ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የሕክምና ትምህርት ለመማር የምትፈልጉ የመመዝገቢያ መስፈርት በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ ኮሌጁ አሳውቋል
#ጥቆማ የ12ኛ ክፍል ትምህርታችሁን አጠናቃችሁ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የሕክምና ትምህርት ለመማር የምትፈልጉ የመመዝገቢያ መስፈርት በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ ኮሌጁ አሳውቋል፡፡ እስከዛው በትዕግስት እንድትጠብቁ ኮሌጁ ጠይቋል፡፡ ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

ተሸለመች👏 የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዝግባለችው ሃናን ናጂ ሙለጌ ድርጅት ባለቤቱ ሀጂ ሙስጠፋ አህመድና betopia ፕሮፐርቲ ባለቤት አቶ ሙኒር በጋራ 200
+1
ተሸለመች👏 የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዝግባለችው ሃናን ናጂ ሙለጌ ድርጅት ባለቤቱ ሀጂ ሙስጠፋ አህመድና betopia ፕሮፐርቲ ባለቤት አቶ ሙኒር በጋራ 200 ሺህ ብር ሽልማት ሰጥተዋታል። በተጨማሪም የ betopia ፕሮፐርቲው ባለቤት አቶ ሙኒር ትምህርቷን ተምራ ጨርሳ ህዝቧን ማገልገል እስክትጀምር በየ ወሩ 10 ሺህ ብር ደምወዝ ተቆራጭ አድርጎላታል። ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች  ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈  ⭕️  ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●