Mark Tech Info | Mark Technology Information
رفتن به کانال در Telegram
Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot
نمایش بیشتر6 211
مشترکین
-524 ساعت
-317 روز
-30430 روز
آرشیو پست ها
‼የቅሬታ ምላሽ
በ2015 ት/ት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ለይ በአካል በመምጣት ቅሬታ ላቀረባችሁ በስልክ ወይም በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ምላሽ ተሰጥቷል። እየተሰጠም ይገኛል።
በበይነ መረብ(Online) ቅሬታ ያቀረባችሁ ምላሹም በበይነ መረብ የተሰጠ በመሆኑ ከዚህ በፊት ውጤት ባያችሁበት መልኩ በድረ ገጽ eaes.et ላይ ምላሹን ማየት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
በቁጥር የተወሰኑ ቅሬታዎች በምላሽ ሂደት ላይ ያሉ በመሆኑ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን።
የት/ት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ብሔራዊ ፈተና
ባለፉት ሁለት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናዎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ተፈትነው ያለፉት ግን እጅግ በጣም ጥቂት ናቸው።
ምን የተቀረ ነገር ኖሮ ነው ? የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ከሰሞኑን በብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው ማብራሪያ ሰጥታዋል።
ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦
" የፈተናው ክብደ እና ቅለት ከሆነ ምንም የተቀየረ ነገር የለም።
የፈተና አሰጣጥ እና ዝግጅት ሂደት አለ፤ እራሱን የቻለ ሳይንስ አለው በጣም እንዳይከብድም በጣም እንዳይቀልም።
እስከ ዛሬ ሲሰራ ከነበረው ምንም የተለየ ነገር የለም። የተለየው ፈተና አሰጣጡ ነው።
ፈተና አሰጣጡ ያመጣው ለውጥ ምንድነው ከተባለ ፤ ከዚህ በፊት ፈተናዎች በየትምህርት ቤት ነው የሚሰጡት ፈተና መታተም ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ ፣ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ ፈተናዎቹ ይሰረቃሉ።
ፈተና ሲሰረቅ የነበረው በተደራጀ መልክ ነው በክልሎች ፈታኞች በየክልሉ ሲሄዱ ትልቅ ግብዣ ተደርጎ ጉቦ ተሰጥቷቸው ተማሪዎቹ እንዲኮራረጁ ይደረጋል። ውጤቱ ትርጉም ያለው አልነበረም።
እኔ ትምህርት ሚኒስቴር የመጣሁ ጊዜ በሁለተኛው ሳምንት ፈተና ሰጥተን ነበር በድሮው አሰጣት ፎርማት ያኔ ነው የማለፊያ ውጤት 50 በመቶ ነው ብለን ፖሊሲ ያደረግነው ፣በወቅቱ ፈተና አሰጣጡን አልቀየርንም ነበር ያኔ ያለፈው 48% ነው። አንዳንድ ክልሎች 70-80 በመቶ አሳልፈዋል።
በምንም አይነት የተማሪዎቹ ችሎታና ብቃት አይደለም። ... መሰረቅ መኮረጁን ለማወቅ ዳታውን ከተታትሎ ማግኘት ይቻላል፤ ግልፅ ነው።
ፈተናው እራሱ የተማሪዎች ችሎታና ብቃት መለኪያ አልነበረም። ያንን ነው የቀየርነው። ከምንም በፊት የሰራነው በተማሪዎች ጭንቅላት ውስጥ በስርቆት፣ በማጭበርበር ፣ ሌላ ሰው በማስፈተን ፣ በመኮረጅ የሚገኝ ትምህርት የለም የሚል ነው። ይሄን አውቀው እንደ ችሎታቸው እንዲያጠኑ ነው ያደረግነው።
የዛ ውጤት፣ እንደ ሀገር ያለንበትን ልክ ነው ያሳወቀን። በዚህም ይሄ ነው የትምህርት ስርዓቱ ካልን በኃላ ሪፎርሞችን በተግባር አውለን አንድ ትውልድ ቢበላሽብን ቀጣዩን እንዴት እናድናለን ብለን ነው እየሰራን ያለነው። "
እንደ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ፤ በ2014 እና በ2015 በድምሩ 1,741,619 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውስደዋል። ከነዚህ ውስጥ ያለፉት በድምሩ 57,301 ተፈታኞች ናቸው።
በዚህ ልክ ተፈታኝ ተማሪዎች መውደቃቸው ዜጎችን ያስደነገጠ ቢሆንም ከነዚህ ተማሪዎች በፊትም ፈተናው አሰጣጡ በዚህ መንገድ ቢሆን ውጤቱ ከዚህ እንደማይለይና የትምህርት ስርዓቱ ውድቀት ከታች ጀምሮ የመጣ እንደሆነ የሚገልጹ በርካቶች ናቸው።
ለዚህ ውድቀት ደግሞ ሁሉም ባለድርሻ ኃላፊነት እንዳለበትና ተማሪዎቹን ከሚያስተምሯቸው መምህራን ብቃት አንስቶ ፣ የትምህርት ቤቶች የጥራት ጉዳይ፣ የግብዓት አቅርቦት ሁሉ ሊፈተሽ የሚገባው እንደሆነ የሚያመላክት መሆኑ ይነሳል።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
"በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የያዝነው አቅጣጫ የሚቀጥል ነው። ወደኋላ የምንመልሰው አይደለም።"
- የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
የትምህርት ዘርፍ ማሻሻያዎች እና የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን አስመልክተው የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከኢቢሲ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
መንግሥት በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ላይ የያዘውን አቅጣጫ አጠናክሮ እንደሚቀጥልበት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
"የመልቀቂያ ፈተና አሰጣጡን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ይሠራል" ብለዋል።
በዚህም በግንቦት ወር መጨረሻ የሚከናወነው የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ድብልቅ / Hybrid በሆነ መልኩ እንደሚሰጥ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።
ፈተናው በከፊል በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በአካል፥ በከፊል ደግሞ በኦንላይን (በተለይ የኢንተርኔት ችግር ባለባቸው አካባቢዎች) የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ፈተናውን መስጠት የመንግሥትን ወጪ ይቀንሳል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ይህን ለማሳካት ለፈተናው የሚሆኑ ታብሌቶችን የማሰባሰብ ሥራ መጀመሩን ጠቁመዋል።
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምዝገባም በኦንላይን ይከናወናል ብለዋል።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
ዘንድሮ ከ100 ሺህ በላይ ተማሪዎች በሬሜዲያል ፕሮግራም እንደሚታቀፉ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገልጸዋል።
የኢቢሲ ብርቱ ወግ ፕሮግራም እንግዳ የነበሩት ሚኒስትሩ፤ የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፍ ያልቻሉ ተማሪዎች በTVET ተቋማት እንዲሁም በሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ጠቁመዋል።
ከ1,200 በላይ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ተቋማት በሀገሪቱ እንዳሉ የገለጹት ሚኒስትሩ፤ የ12ኛ ክፍል ፈተናን ማለፍ ያልቻሉት ተማሪዎች ወደእነዚህ የስልጠና ተቋማት ገብተው የሚያስፈልጋቸውን ክህሎት እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከ100 ሺህ በላይ ተማሪዎች በ2016 ዓ.ም በሬሜዲያል ፕሮግራም የሚታቀፉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
እነዚህ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ ብቃት ያላቸው ተማሪዎች እንዲሆኑ የሚያዘጋጃቸውን የማጠናከሪያ ትምህርት ለአንድ ዓመት እንደሚወስዱ ገልጸዋል።
ባለፈው ዓመት በሬሜዲያል ፕሮግራም ታቅፈው የነበሩ ተማሪዎች ላይ በተሠራ የማብቃት ሥራ የመልቀቂያ ፈተና በድጋሜ ከወሰዱ ተማሪዎች 70 ከመቶ የሚሆኑት ማለፋቸውን ሚኒስትሩ አስታውሰዋል።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
"መንግሥት ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባውን ተማሪ ቁጥር ሆን ብሎ የመቀነስ ምንም ፍላጎት የለውም።"
-የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
መንግሥት በትምህርት ዘርፍ እየወሰዳቸው ስላሉ ማሻሻያዎችና የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን አስመልክተው የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያው ጋር ቆይታ አድርገዋል።
መንግሥት ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባውን ተማሪ ቁጥር ሆን ብሎ የመቀነስ ምንም ፍላጎት እንደሌለው ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
"ችሎታ ያላቸው ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲገቡ ነው የሚጠበቀው" ያሉት ሚኒስትሩ፤ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ መማር የሚችሉ ወጣቶችን ለማፍራት እየተሠራ ነው ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችል አቅም የሌላቸው ተማሪዎች ህብረተሰቡን በማገልገል ራሳቸው የሚጠቀሙባቸው ሌሎች ሥራዎች ላይ የሚሰማሩበት ዕድል መኖሩን ጠቁመዋል። በዚህም የTVET ተቋማትን በማስፋፋት ወጣቶቹ የሚያስፈልጋቸውን ክህሎት እንዲያገኙ የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል።
"በጣም የተወሳሰበና በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ዓለም እየተፈጠረ ነው" ያሉት ሚኒስትሩ፤ "ብዙ የተማሩና ብዙ ክህሎት ያላቸው ወጣቶች ቢኖሩ የመንግሥት ፍላጎት ነው" ብለዋል።
"ተማሪዎች እንዲያልፉ ነው የምንፈልገው። ተማሪዎች በመውደቃቸው የሚገኝ ምንም ጥቅም የለም። እየሆነ ያለው ያሳዝናል። ነገር ግን የሰጠናቸው ፈተናዎች ያለብንን የትምህርት ጥራት ጉድለት፣ የበሽታችንን ጥግ አሳይተውናል።"
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️የ6 ተማሪዎች ህይወት አልፏል
በትግራይ የ12ኛ ክፍል ፈተና ጨርሰው ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲመለሱ የነበሩ ተማሪዎች በደረሰባቸው የመኪና አደጋ ህይወታቸው አለፈ።
በርካቶችም ቀላል እና ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ፈተናቸውን ጨርሰው ወደ ተንቤን እና አካባቢው ሲጓዙ የነበሩ ተማሪዎችን አስፋሮ የነበረ ኣውቶብስ በሀውዜን ወረዳ " ደብረ ሰላም " የሚባል አካባቢ ተገልብጦ የ6 ተማሪዎች ህይወት አልፏል።
በአደጋው ከሞቱት 6 ተማሪዎች በተጨማሪ 53 ተማሪዎች ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው የሀውዜን መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አሳውቋል።
የሀውዜን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እና የመጋብ ጤና ጣቢያ የህክምና እና የአምቡላንስ ባለሙያዎች ተጎጂዎች ህክምና እንዲያገኙ ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸው ተነግሯል።
ጉዳት የደረሰባቸው 29 ተማሪዎች በሀውዜን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እና መጋብ ጤና ጣቢያ በህክምና ላይ ሲሆኑ ፤ 24ቱ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች ወደ አይደር ሪፈራል ሆስፒታል መላካቸውን ከቴሌቪዥን ትግራይ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
#Update
በትግራይ ሲሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ተጠናቀቀ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል አገራዊ ፈተና በተረጋጋ እና ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ ተጠናቋል ሲል አሳውቋል።
በተመሳሳይ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ትምህርት ቢሮው ፈተናው በተረጋጋ ሁኔታ መጠናቀቁ አሳውቋን።
የቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ኪሮስ ጉዑሽ ፤ዥ አገር አቀፍ ፈተናው በተያዘለት ዕቅድ እንዲጠናቀቅ ያደረጋችሁ ከፌደራል እስከ ትምህርት ቤቶች እና ዩንቨርሲቲዎች ያላችሁ ተቋሞች፣ የትምህርት ኣመራሮች እና መምህራን፤ ከፌደራል እስከ ወረዳ ያላችሁ የፀጥታ እና ደህንንት ተቋሞች እና ኣመራሮች፤ ከተለያዩ ኢትዮጵያ ዩንቨርሲቲዎች የተውጣጣችሁ ፈታኞች የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን " ብለዋል።
ሃላፊው " ፈተናው በተረጋጋ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ተፈታኝ ተማሪዎቻችን ከናንተ የሚጠበቀው ሁሉ ስለደረጋችሁ ለናንተም የላቀ ምስጋና ይገባቹሃል " ሲሉ አክለዋል።
ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 02/2016 ዓ/ም ለአራት ተከታታይ ቀናት በትግራይ ክልል ሲሰጥ የቆየውን የ12 ክፍል አገራዊ ፈተና ከ9,000 በላይ ተማሪዎች መፈተናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ መረጃ ያሳያል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የፈተና ውጤቱን ባጠረ ጊዜ ለማሳወቅ እንደሚሰራ ገልጿል።
የትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መስከረም 28 /2016 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ የትግራይ ተፈታኞቹን ውጤት በአንድ ሳምንት ውስጥ ለማሳወቅ ይሰራል።
የሚያልፉ ተማሪዎች በአገር አቀፍ ደረጃ ውጤታቸው ከተገለጸ ተማሪዎች ጋር አብረው ወደ ዩኒቨርሲቲ እንዲገቡ ለማድረግ ጥረት እንደሚደረግ መግለፃቸው አይዘነጋም።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
በ2016 ዓ.ም በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሦስት ዙር ይሰጣል።
በ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪ የነበሩና የመልቀቂያ ፈተናውን ያልወሰዱ 9,514 ተማሪዎች በመጀመሪያ ዙር ፈተናውን ከመስከረም 29/2016 ዓ.ም ጀምሮ እየወሰዱ ይገኛሉ።
በ2012 ዓ.ም የ11ኛ ክፍል ተማሪ ለነበሩ ተማሪዎች በጥር 2016 ዓ.ም የመልቀቂያ ፈተናው ይሰጣል።
በ2012 ዓ.ም የ10ኛ ክፍል ተማሪ ለነበሩ ተማሪዎች በግንቦት 2016 ዓ.ም መጨረሻ መልቀቂያ ፈተናው እንደሚሰጥ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።
የ12ኛ ክፍል ፈተና በዚህ ዓመት በሦስት ዙር መሰጠቱ በክልሉ ለአራት ዓመታት የትምህርት ጊዜ ያለፈባቸውን ተማሪዎች ለማካተት በማሰብ መሆኑን የቢሮው ኃላፊ ኪሮስ ጉዕሽ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
የ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ግንቦት ወር ላይ እንዲሰጥ ከወዲሁ ዝግጅቶች እየተደረጉ ይገኛል።
የአሁኑ ፈተና ድብልቅ / ሃይብሪድ መሆኑን ከቀናት በፊት መግለጫ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።
ድብልቅ ፈተና ማለት ግማሹ ኦንላይን (የኢንተርኔት ችግር የሌለባቸው አካባቢዎች) ፤ የኢንተርኔት ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ደግሞ ከዚህ ቀደም ሲሰጥ በነበረበት አካሄድ በወረቀት ነው የሚሰጠው።
ይህ የፈተና አሰጣጥ አካሄድ በዩኒቨርሲቲዎች ላይ ፣ በመንግሥት በጀት ፣ በትምህርት ቢሮዎች ላይ ጫናውን እንደሚቀንስ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ምንም እንኳን የመግዛት አቅም ባይኖረውም ለፈተናው የሚሆኑ #ታብሌቶችን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመነጋገር ለፈተናው ጊዜ በመውሰድ ፈተናውን በድብልቅ እንደሚሰጥ አመልክቷል።
የተሻሉ የፈተና አዘጋጆች፣ ፈተናዎች እንዳይሰረቁ የሳይበር ጥበቃ፣ የደህንነት ካሜራዎች ፣ የተቋማት ትብብር (ኢንሳ፣ ፈተናዎች አገልግሎት) ፣ ጥንቃቄ የተሞላበት የፈተና ህትመት ዝግጅት ከዚህ ቀደሙም በተሻለ መልኩ ጠንካራ ስራ በጋራ እንደሚሰራ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
በ2014 ፈተና 896,520 ተማሪዎች ተፈትነው ያለፉት 30,034 ወይም 3.3 በመቶ ብቻ ሲሆኑ በ2015 ፈተና 845,099 ተማሪዎች ተፈትነው ማለፍ የቻሉት 27,267 ወይም 3.2 በመቶ ብቻ ናቸው።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️አማራ
በ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙ ካሳለፉ 5 ትምህርት ቤቶች 3ቱ በአማራ ክልል የሚገኙ ናቸው።
ሶስቱ ትምህርት ቤቶች ፦
- ደሴ ልዩ የአዳሪ ትምህርት ቤት፣
- ሐዲስ ዓለማየሁ ልዩ የአደሪ ትምህርት ቤት
- ባሕር ዳር ስቴም ትምህርት ቤት ናቸው።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በማኅበራዊ ሳይንስ ከፍተኛውን ውጤት ያስመዘገበው ተማሪም የሐዲስ ዓለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ነው።
እንደ አማራ ክልል ትምህርት ቢሮ መረጃ በሐዲስ ዓለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት እና በደሴ ልዩ የአዳሪ ትምህርት ቤት በድምሩ 32 ተማሪዎች 600 እና ከዚያ በላይ ውጤት አስመዝግበዋል፡፡
የአማራ ክልል ተማሪዎች የጥይት ድምጽ እየሰሙ ተምረዋል፤ የጥይት ድምጽ እየሰሙ ተፈትነዋል፡፡ አብዘኛዎቹ የክልሉ ተማሪዎች በጦርነት ምክንያት በወደሙ እና በተዘረፉ ትምህርት ቤቶች ለመማር ተገድደዋል፡፡ በፈተና ወቅት በተፈጠረ አለመረጋጋት ፈተናውን አቋርጠው የወጡ ተማሪዎችም ነበሩ።
ቢሮው እንደ ሀገር የተዘመገበው ውጤት ዝቅተኛ መሆኑን ገልጾ በትምርት ስርዓቱ ላይ በርካታ ስራ መስራት ያስፈልጋል ብሏል።
በአማራ ክልል ጦርነት እና ግጭት በፈጠሩት ሥነ ልቦናዊ ጫና ውስጥ ሆነው የተፈተኑ ተማሪዎች መኖራቸው ያስታወሰው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ተማሪዎች ጫናውን ተቋቁመው ያስመዘገቡት ውጤት ጥሩ መሆኑን አመልክቷል።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
የ12ኛ ክፍል ውጤት ለማየት መቸገራቸውን በርካታ ተማሪዎች እና ወላጆች አስተያየታቸውን ለቲክቫህ ሰጥተዋል።
የ2015 ዓም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ውጤት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት 6284፣ በዌብሳይት eaes.et እንዲሁም በቴሌግራም ቦት @eaesbot የሬጅስትሬሽን ቁጥር በማስገባት ማየት እንደሚቻል መገለጹ ይታወቃል።
ነገር ግን በርካታ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ውጤት ለማየት መቸገራቸውን ለቲክቫህ ገልጸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በውጤት መመልከቻ አማራጮቹ ላይ ምንም አይነት ቴክኒካል ችግር እንደሌለና መጨናነቅ ብቻ መኖሩን ለቲክቫህ ገልጿል።
ሙራድ ታደሰ የተባሉ የቲክቫህ ቤተሰብ ውጤት ለማየት የተቸገሩ ተማሪዎች ሊጠቀሙት የሚችሉ አማራጭ መፍትሔ ጠቁሞናል።
ውጤት የመመልከቻ አማራጮች ላይ ማለትም eaes.et ፣ eaes.gov.et ፣ eaes.edu.et ከገባችሁ በኋላ Forgot Admission Number የሚለውን በመጫን፣ Your Name, Father's Name, Grand Father's Name በሚሉት ላይ ስማችሁን እስከአያት ስትሞሉ ካለምንም ID ይሠራል።
ተማሪዎች በትዕግስት በመሞከር ውጤታቸውን እንዲያዩ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መክሯል።
በተጨማሪ ቅሬታ ማቅረቢያው ቅፅ እየሰራ እንዳልሆነ በርካታ ተማሪዎች አስተያየታቸውን ለቲክቫህ አድርሰዋል።
በነዚህ ጉዳዮች ላይ የሚመለከታቸውን አካላት በማናገር ተጨማሪ የምናደርሳችሁ ይሆናል።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
" የተፈታኞቹን ውጤት በአንድ ሳምንት ውስጥ ለማሳወቅ ይሰራል ፤ የሚያልፉ ተማሪዎችም በሀገር አቀፍ ደረጃ ውጤታቸው ከተገለፁት ጋር ወደ ዩኒቨርሲቲ እንዲገቡ ለማድረግ እንጥራለን " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
" ፈተናው ዛሬ በአራቱም ዩኒቨርሲቲዎች በሰላም ተጀምሯል። " - የትግራይ ትምህርት ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና በትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።
ፈተናው በክልሉ በሚገኙ አራቱ የፌደራል ዩኒቨርስቲዎች በተመሳሳይ ጊዜ በሰላማዊ ሁኔታ መሰጠት መጀመሩ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አረጋግጠዋል።
በቢሮው የግንኙነት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ሰለሞን ገ/ታትዮስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፦
- በራያ ዩኒቨርስቲ 1561
- በመቐለ ዪኒቨርስቲ 2280
- በዓዲግራት ዩኒቨርስቲ 2382
- በኣክሱም ዩኒቨርስቲ 3291 በአጠቃላይ ከዘጠኝ ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን ዛሬ ጀምረዋል።
ፈተናው ጥቅምት ሁለት ይጠናቀቃል።
የትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መስከረም 28 /2016 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳሉት ፤ የትግራይ ተፈታኞቹን ውጤት በአንድ ሳምንት ውስጥ ለማሳወቅ ይሰራል።
የሚያልፉ ተማሪዎች በአገር አቀፍ ደረጃ ውጤታቸው ከተገለጸ ተማሪዎች ጋር አብረው ወደ ዩኒቨርሲቲ እንዲገቡ ለማድረግ ጥረት ይደርጋል ብለዋል።
ፎቶ፦ TIGRAY TV
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
የ2014 አመት የሬሚዳል(remedial) የመቁረጫ ነጥብ ይሄን ይመስል ነበር ።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
Abdulrehman Shikur 👏👏👏👏🙌
#624 👏👏👏👍
HAYRANZI SPECIAL SCHOOL👏👏👏
በ 12ኛ ክፍል ከ መላው ደቡብ ክልል አንደኛ ውጤት
ከ ኢትዮጵያ ደሞ 3ኛው ውጤት የተመዘገበው ስልጤ ክልል ወራቤ ከተማ ሃይረንዚ አዳሪ ት/ቤት ነው።
አብዱረህማን ሽኩር👏👏 624
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
637, 630 እና 622👏👏👏👏
ODA SPECIAL BOARDING SCHOOL (ኦዳ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት)
ኦዳ ትምህርት ቤት ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ካስመዘገቡ አስር ትምህርት ቤቶች መካከል 6ኛ ደረጃ አጊኝቷል።
ትምህርት ቤቱ በ2015 ዓ.ም ካስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል 20 ተማሪዎች • ከ600-623 ማስመዝገባቸውን ተገልጿል።
በትምህርት ቤቱ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 637 መሆኑ ተግልጿል፡፡
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
የ12ኛ ክፍል ውጤት ለማየት መቸገራቸውን በርካታ ተማሪዎች እና ወላጆች አስተያየታቸውን ለቲክቫህ ሰጥተዋል።
የ2015 ዓም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ውጤት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት 6284፣ በዌብሳይት eaes.et እንዲሁም በቴሌግራም ቦት @eaesbot የሬጅስትሬሽን ቁጥር በማስገባት ማየት እንደሚቻል መገለጹ ይታወቃል።
ነገር ግን በርካታ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ውጤት ለማየት መቸገራቸውን ለቲክቫህ ገልጸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በውጤት መመልከቻ አማራጮቹ ላይ ምንም አይነት ቴክኒካል ችግር እንደሌለና መጨናነቅ ብቻ መኖሩን ለቲክቫህ ገልጿል።
ሙራድ ታደሰ የተባሉ የቲክቫህ ቤተሰብ ውጤት ለማየት የተቸገሩ ተማሪዎች ሊጠቀሙት የሚችሉ አማራጭ መፍትሔ ጠቁሞናል።
ውጤት የመመልከቻ አማራጮች ላይ ማለትም eaes.et ፣ eaes.gov.et ፣ eaes.edu.et ከገባችሁ በኋላ Forgot Admission Number የሚለውን በመጫን፣ Your Name, Father's Name, Grand Father's Name በሚሉት ላይ ስማችሁን እስከአያት ስትሞሉ ካለምንም ID ይሠራል።
ተማሪዎች በትዕግስት በመሞከር ውጤታቸውን እንዲያዩ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መክሯል።
በተጨማሪ ቅሬታ ማቅረቢያው ቅፅ እየሰራ እንዳልሆነ በርካታ ተማሪዎች አስተያየታቸውን ለቲክቫህ አድርሰዋል።
በነዚህ ጉዳዮች ላይ የሚመለከታቸውን አካላት በማናገር ተጨማሪ የምናደርሳችሁ ይሆናል።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ቅሬታ
በ2015 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተያ ውጤት ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተፈታኞች eaes.et ላይ እስከ ጥቅምት 05/2016 ዓ.ም ከቀኑ 11:30 ድረስ ቅሬታችሁን በኦንላይን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አግልግሎት ገልጿል።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
ጀግኒት👏👏👏 #645
Rekik Ashenafi
ከ ሀዋሳ "COMBONI" ትምህርት ቤት 3ኛውን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችሁ ወጣት Rekik አሸናፊ 👏👏👏
ሴቶቻችን አልተቻሉም ✌️👏✌️👏 ሞራል እስኪ👌
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ውጤታችሁን እስካሁን ያላያችሁ ተማሪዎች በቴሌግራም ቦት 👉 @Eaesbot ማየት ትችላላችሁ።
ቦቱ ትንሽ ያስቸግራል ቀስ እያላችሁ ሞክሩት፣ እንዲሁም በ ዌብሳይት 👉 eaes.edu.et ተጠቀሙ፣ #Vpn ግዴታ ነው።
ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
⭕️ 👉 t.me/grade12results 👈 ⭕️
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
