1 199
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+27 روز
+830 روز
آرشیو پست ها
1 199
#ከኢፌዲሪ_ትምህርትና_ስልጠና_ባለሥልጣን_የተሰጠ_ማሳሰቢያ
===== ==== ===
በማንኛውም የትምህርት መስክ ከዲፕሎማ ጀምራችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ ለተማራችሁ የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ አገልግሎት ፈላጊዎች በሙሉ፤ በየካቲት 2016 ዓ.ም ጸድቆ ሥራ ላይ በዋለው የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥና የአቻ ግመታ መመሪያ ቁጥር 991/2016 መሠረት የሙያ ብቃት ምዘናን በተመለከተ፡-
1. እስከ 2009 ዓ.ም መጨረሻ ባለው ጊዜ ውስጥ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ተምረው የጨረሱ ያለ ብቃት ምዘና የትምህርት ማስረጃቸው ይረጋገጥላቸዋል፤
2. በ2008 ዓ.ም የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርታቸውን የጀመሩ ዲግሪያቸውን ከማረጋገጣቸው በፊት የደረጃ አራት የሙያ ምዘና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤ (በመማር ላይ እያሉ ያገኙት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት/COC/ ተቀባይነት ይኖረዋል)
3. ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬቶች ተማሪው የመጀመሪያ ዲግሪውን ለመማር ከመመዝገቡ በፊት የተጠናቀቁ መሆን አለባቸው፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
1 199
Genuine leadership and effective management are not founded on a foundation of fear or intimidation. Instead, they thrive in an environment of trust, respect, and open communication. True leaders inspire and motivate their team members by fostering collaboration and encouraging personal and professional growth.
They understand that a positive and empowering atmosphere leads to enhanced productivity and morale, ultimately resulting in a more cohesive and successful organization. Leadership should be about guiding others with empathy and integrity rather than controlling them through fear or coercion.
- Grab your copy of our new Amazon Bestseller, Inspirational Leadership Quotes, Finding The Courage To Lead.
https://t.me/Information_DM
1 199
ስኬትን ፍለጋ
“ስኬትን ከፈለክ ስኬትን ዓላማህ አድርገህ አትያዝ፡፡ የምታምንበትንና የምትወደውን ነገር ከልብህ ስታደርግ ስኬት ራሱ ይመጣል” - David Frost
ለትክክለኛ አላማ መቆም ስኬትን ይቀድማል እንጂ ስኬት አላማን አይቀድምም፡፡
አንዳንድ ሰዎች፣ “ቢሳካልኝ ኖሮ ይህንና ያንን አደርግ ነበር” በማለት በገንዘብና በተለያዩ አቅጣጫዎች “ቢሳካላቸው” ሊያደርጉ ስለሚፈልጉት የወደፊት አላማ ሲናገሩ ይደመጣሉ፡፡
አንድ ማስታወስ ያለባቸው እውነታ ግን አንድን አላማ ይዘው መስራታቸው ወደ ስኬት እንደሚወስዳቸው ነው፡፡ በሌላ አባባል፣ ተሳካላቸው በመባል የሚታወቁ ሰዎች ለስኬት የኖሩ ሰዎች ሳይሆኑ ለአንድ አላማ በጽንአት የኖሩ ናቸው፤ ያንን ሲያደርጉ ስኬት ተከተላቸው፡፡
ለስኬት የሚኖር ሰው ስኬት ያጣ ሲመስለው ያቆማል፡፡ ለአላማ የሚኖር ሰው ግን ስኬት ያላገኘ ቢመስለውም እንኳ ጉዞውን ይቀጥላል፣ ምክንያቱም አላማ የተሰኘውን የስኬቶችን ሁሉ ስኬት በእጁ ጨብጧልና ነው፡፡
“የምትወደውንና መልካም የሆነውን ነገር አድርግ፣ ያንን የምታደርገውን ነገር ደግሞ ውደደው” የሚለው አባባል እውነት ነው፡፡ ስኬትን ፍለጋ ከአላማህ ውጪ የሆነን “ታላቅ” ነገር ከማድረግ፣ አላማን በመከተል አስቸጋሪ ጎዳና መጓዝ ይመረጣል፡፡
1 199
የታክስ_ኦዲት_የሚከናወንበትን_ስርዓት_እና_የታክስ_ስሌት_ማስታወቂያ_የሚወጣበትን_አኳኋን_ስለመወሰን_የወጣ.pdf5.85 MB
1 199
የስራ ቋንቋ ይከበር
የሬድዮ ዝግጅት ላይ ነው ጋዜጠኛው ለደዋይ ደንበኛው "በስትክክል" አላዳመጡኝም ይላል
በስትክክል ወይ ጉድ በትክክል ጠፍቶ በስትክክል ሆነ
🙊🙊🙊
እንኳን ቋንቋው የማያውቀው በስትክክል ቀርቶ ሞክሼ ፊደላት ራሱ ትርጉም ይቀይራሉ
“ሞክሼ” ፊደላት
📌ምሁር፡- የተማረ፣ ሊቅ፤
✍️ምሑር፦ ምሕረት (ይቅርታ)
📌 መሳሳት፦ ትክክል ያለመሆን፤
✍️ መሣሣት፡- መቅጠን፣ ሥሥ መሆን ወይም በጥንቃቄ መያዝ፤
📌 መአት፦ እጅግ ብዙ፤
✍️ መዓት፦ ቍጣ፤
📌 ሳለ፦ በጉሮሮው ኡህ! ኡህ! አለ፤
✍️ሣለ - ሥዕልን (ምስልን) ሠራ።
📌 ሠራዊት፦ ወታደሮች፤
✍️ ሰራዊት፦ ዓምዶች፤
📌 ሕብር፦ ቀለም፤
✍️ ኅብር፦ የተባበረ፤
📌 አባይ፦ የሚዋሽ፣ የሚያብል፣ ቃሉን የሚለውጥ፤
✍️ ዓባይ፦ ትልቅ፣ ከፍ ያለ፣ የወንዝ ስም፤
📌 በአል፦ አይሁድ ያመልኩት የነበረ የጣዖት ስም፤
✍️ በዓል፦ ልዩ ቀን፣ የተከበረ ቀን፤
📌 አመት፦ አገልጋይ፤
✍️ ዓመት፦ 12 ወራት ከ 5/6 ቀን፤
📌 አራት፦ ቍጥር
✍️ ዐራት፦ መኝታ
1 199
ትርጓሜ ስም
ስም. ------------- ትርጉም
1 ፊላታዎስ፦የአምላክ ወዳጅ
2 ሮብዓም፦ሕዝብ ይብዛ
3 ቴዎድሮስ፦የእግዚአብሔር ስጦታ
4 ሮቤል፡-እነሆ ወንድ ልጅ
5 ማራናታ፦ጌታ ሆይ ና
6 ቤቴል፦የእግዚአብሔር ቤት
7 ቄርሎስ፦የተመረጠ ምርጥ
8 እስጢፋኖስ፦አክሊል
9 ሳውል/ሳኦል፡፦ከእግዚአብሔር የተለመነ
10 ሴዴቅያስ፦የእግዚአብሔር ጽድቅ
11 ፊቅጦር፦ኀዘኔን አራቀልኝ
12 ንፍታሌም፦ታጋይ የሚታገል
13 ዮርዳኖስ፦ወራጅ
14 ዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል
15 ገነት-የአትክልት ስፍራ
16 ፊልድልፍያ፦የወንድማማች ፍቅር
17 ዲና፦ፈረደ
18 ማኑሄ፦እረፍት
19 መልሕቅ፦ከብረት የተሠራ የመርከብ ማቆሚያ
20 ራማ-ከፍታ
21 ኤርምያስ፦እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል
22 ሐና፦ ስጦታ
23 ሕርያቆስ፦ኅሩይ
24 ፊልጶስ፦ወንድም ወዳጅ
25 ቶማስ፦ፀሐይ
26 ጎርጎርዮስ፡- ተመልካች እና ተያይዟል።
27 ማትያስ፦ፀሐይ
28 ቀሌምንጦስ፦ግንብ
29 አቤል፡-በግ ወይም ደመና
30 ኖኅ-ደስታ
31 ሴም፦ተሾመ
32 ይሥሐቅ፦ደስታ አንድም
33 ሙሴ፦የውሃ ልጅ
34 አሮን-የእግዚአብሔር ተራራ
35 ጌዴዎን-እግዚአብሔር ኃያል ነው
36 እሴይ፦ዋጋየ
37 አሚናዳብ፦መንፈስቅዱስ
38 ዳዊት-የተወደደ ልበ አምላክ
39 ዕንባቆም፦ጠቢብ አዋቂ አስተዋይ
40 ሄኤሜን-ምኞቴን አገኘሁ
41 አሞጽ-እግዚአብሔር ጽኑ ነው
42 ዮናስ-ርግብ
43 ሐጌ-የእግዚአብሔር መልእክተኛ
44 ራኄል-በግዕት
45 ዕዝራ፡-ረዳቴ
46 ሔርሜላ-ከክብር ዘመድ የተገኘች
47 መርቆሬዎስ፦የአባት ወዳጅ
48 ኤጲፋንዮስ፦ምስጢር ገላጭ
49 ሜሮን-የተባረከ ሽቱ
50 ሱላማጢስ፦ሰላማዊት
51 ሶምሶን፦ፀሐይ
52 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ
53 ማርታ፦እመቤት
54 ሊዲያ ፈራሂተ እግዚአብሔር
55 ኤፍሬም፦ፍሬያማ ፍሬው
56 ኤፍራታ-ክብርት የተከበረች
57 ታዴዎስ-ተወዳጅ
58 ኢየሩሳሌም፡-የሰላም ሀገር
59 ሄኖስ-ሰው
60 ሰሎሜ፦ሰላም
61 ሩሐማ ምሕረት
62 ዮዳሔ፦እግዚአብሔር ያውቃል
63 ቴዎፍሎስ-የእግዚአብሔር ወዳጅ
64 ኑኃሚን፦ደስታየ
65 ናትናኤል-የእግዚአብሔር ስጦታ
66 አዛሄል-እግዚአብሔር ያያል
67 ኢዮስያስ፦እግዚአብሔር ይደግፋል
68 ኢዩኤል-እግዚአብሔር አምላክ ነው
69 በርናባስ፡-የመጽናናት ልጅ
70 ሶፎንያስ፦እግዚአብሔር ሰውሯል/ጠብቋል
71 ሕዝቅኤል፦እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል
72 ኬልቅያስ፦እድል ፈንታየ እግዚአብሔር
73 ሳሙኤል፦እግዚአብሔር ሰማኝ
74 ሚኪያስ፦ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው!
75 ሆሴዕ፡-እግዚአብሔር ያድናል
76 ሔዋን-የሕያዋን ሁሉ እናት
77 ሕዝቅያስ፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው
78 መልከጼዴቅ፡-የሰላም ንጉሥ
79 ሚልኪያስ-መልእክተኛየ
80 ሣራ:-ልዕልት
81 ስምዖን፡-ሰማ
82 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ
83 ናሆም-መጽናናት ማለት ነው፡፡
84 ናታን፦ እግዚአብሔር ሰጥቷል
85 አልዓዛር፦ትርጉሙ እግዚአብሔር ረድቷል
86 አስቴር-ኮከብ
87 አቤሜሌክ፦የንጉሥ አገልጋይ
88 አቤሴሎም፦አባቴ ሰላም ነው
89 አብድዩ፦የእግዚአብሔር አገልጋይ
90 አብራም-ታላቅ አባት
91 አብርሃም፦የብዙዎች አባት
92 አኪያ-እግዚአብሔር ወንድሜ ነው
93 አክዐብ፦የአባት ወንድም
94 ባሮክ-ቡሩክ
95 አዳም፡-መልካሙ
96 ኢሳይያስ፦ እግዚአብሔር ደኅንነት ነው
97 ባርቅ፡-መብረቅ
98 ኢያሱ፦እግዚአብሔር አዳኝ ነው
99 ኢዮሳፍጥ፦እግዚአብሔር ፈርዷል
100 ኢዮራም-እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ
101 ኢዮርብዓም-ሕዝቡ እየበዛ ይሄዳል
102 ቤተልሔም፦የእንጀራ ቤት
103 ኢዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል
104 ኢዮአቄም፦እግዚአብሔር አቆመ
105 ኢዮአብ፦እግዚአብሔር አባት ነው
#Banna
1 199
አስቸኳይ፡- ውድ የመምህራንና ትምህርት አመራር ሙያ ፈቃድ የጹሁፍ ምዘና ተመዛኞች በሙሉ እንደሚታወቀው ምዘናችሁ ቅዳሜ 23/9/2017ዓ.ም በአዲስ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መሆኑን እየገለጽን፡-
1. ምዘና ጣቢያ መድረስ ያለብዎ 1፡00 ሰአት ላይ ነው፣
2. ለምዘና ሲመጡ አድሚሽን ካርድ እና መምህር ፣ ር/መምህር ሱፐርቫይዘር መሆንዎን የሚገልጽ መታወቂያ ይዘው መገኘት አለብዎት፣
3. ሰአት፣ስልክ፣ካልኩሌተር ፣ማስታወሻ ደብተር ወዘተ ይዞ ወደ ምዘና ጣቢያ መግባት አይቻልም፣
4. ምዘናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተመዛኝ መግባት አይችልም፣
5. ምዘናውን ሊጠናቀቅ 30 ደቂቃ ሲቀረው ሰርተው ቢጨርሱም ከክፍል መውጣት አይፈቀድም፡፡
‹መልካም ምዘና ይሁንልዎ›
1 199
+2
ሰው ሰራሽ አስተውሎትን የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየተጠቀምኩበት ነው፡- የትምህርት ሚኒስቴር
****
ሰው ሰራሽ አስተውሎትን (ኤ አይ) የትምህርት ጥራትንለማረጋገጥ በሁለንተናዊ መልኩ እየተጠቀምንበት ነው ሲል የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማሩን ሂደት በኤ አይ የተደገፈ በማድረግ ውጤት ማምጣት ጀምረናል ሲሉ በትምህርት ሚኒስቴር የአይሲቲ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) በኢቲቪ የአዲስ ቀን የሀገር ጉዳይ መሰናዶ በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ፣ የአስተዳደርና ምርምር ስራዎችን ለማሳለጥ እንዲሁም መረጃ ለማሰባሰብ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ላቅ ያለ አስተዋጽኦ እንዳለው ነው ያመላከቱት፡፡
አያይዘውም የኤ.አይ ውጤቶችን በቅንጅትና በስፋት መጠቀም ከተቻለ ከጉዳታቸው ይልቅ ፈጠራን በመጨመር እና ስራን በማቅለል ረገድ አበርክቷቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ቴክኖሎጂውን በዘላቂነት ለመተግበርም ለ34 ሺህ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ከአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
መምህራን እና ተማሪዎች በኤ አይ የመማር ማስተማር ዙሪያ ግንዛቤ ሊኖራቸው ይገባል የሚሉት ዶ/ር ዘላለም፤ ተማሪዎች የራሳቸው ያልሆነን ስራ ቀጥታ ገልብጠው እንዳይጠቀሙ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ክትትል እንደሚደረግ ነው የተናገሩት፡፡
ተማሪዎች በቴክኖሎጂው ላይ ብቻ ተደግፈው የፈጠራ እና የመመራመር ክህሎታቸው እንዳይቀንስ በዚህ ዙሪያ የወላጆች ሚናም ከፍተኛ ሊሆን እንደሚገባም ነው ያነሱት፡፡
እንደሀገርም ጤናማ በሆነ መልኩ ከኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጋር የተላመደ ማህበረሰብ ለመፍጠር ታቅዶ መሰራት እንዳለበት ተመላክቷል፡፡
አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሚለው ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ የተደረገው እ.አ.አ አቆጣጠር በ1956 በደርትማውዝ በተካሄዳ የአሜርካዊው የኮምፒዩተር ሳይንትስት ጆንማካርቲ ነው፡፡
ሰው ሰራሽ አስተውሎትን (ኤ አይ) ድህነትን ለመቀነስ፣ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ፣ ጥራት ያለውን የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እና ለሌሎች በርካታ አገልግሎቶች ብዙ ጥቅሞች እያስገኘመሆኑን ይገለጻል፡፡
በመሐመድ ፊጣሞ
#EBC
1 199
🚹🌀 በአንድ ትምህርት ቤት ውስጥ መምህሯ ክፍል ገብታ ስታስተምር ከተማሪዎቹ አንዱ ይነሳና "መምህር እቃ ተሰርቂያለሁ" ይላል። መምህሯም የተሰረቀው እቃ ምን እንደሆነ ካጣራች ቡኃላ ተማሪዎች ለፍተሻ እንዲዘጋጁ አደረገችና ፍተሻዋን ቀጠለች ።
በፍተሻው ሰአት ታዲያ አንዲት እድሜዋ 10 አመት እማይሞላ ተማሪ ተራዋ ደርሶ ቦርሳዋን እንድትከፍት ስትጠየቅ አሻፈረኝ ትላለች ። መምህሯም በንዴት ጦፋ አንቺ ሌባ አንቺ ነሽ የሰረቅሽው ፓሊስ ነው ምጠራልሽ እያለች ስትጮህ የሰሙት ዳይሬክተሯ ከተፍ ይላሉ ።
ይህን ጊዜ ልጅቷ የባሰ ድንጋጤና ፍርሃት እያንቀጠቀጣት እባክሽ ይቅር በይኝ እኔ ሌባ ኣደለሁም ከፈለግሽ እንኪ ፈትሽኝ ግን እዚህ ተማሪዎች ፊት አደለም እያለች መምህሯ እግር ስር ወድቃ ልመናዋን ቀጠለች ። መምህሯ ግን እየደነፋች ነው ።
በዚህ ጊዜ በእድሜ ጠና ያሉት ሴት ዳይሬክተር ቆይ እስቲ መምህር ምን እንደተፈጠረ ንገሪኝ ብለው ዳይሬክተሯ ወደቢሮ ወሰዷቸው ። ከዛም ልጅቷን በተረጋጋ ሁኔታ እንድትቀመጥ ቢያደርጉም መምህሯ ግን እስካሁን መረጋጋት አልቻለችም ። ዳይሬክተሯ መምህሯን ከገላመጡና ዝም እንድትል ካደረጉ ቡኃላ ልጅቷን እረጋ ብለው "ቦርሳው ውስጥ ምንድነው ያለው" ብለው ጠየቋት ።
ልጅቷም "ቦርሳው ውስጥ ያለው ተማሪዎች በልተው የጣሉት ትርፍራፊ ነው ያለው" አለች በህፍረት እየተሸማቀቀች። ሴትዮዋም በመገርምና ባለማመን ስሜት "እንዴት እንዲህ ይሆናል" ሲሉ ጠየቋት ።
እሷም "ለወንድሞቼ ልወስድላቸው ብየ ነው" አለች አንገቷን ደፍታ በሚያሳዝን ሁኔታ ቅስሟ ተሰብሮ ። ይህን ጊዜ ዳይሬክተሯ ከመቀመጫቸው ተነስተው ተጠጓትና ፀጉሯን እየደባበሱ "አይዞሽ የኔ ልጅ ተረጋግተሽ ስለ አባትሽና ስለ እናትሽ ንገሪኝ ኣሏት ።
ይቺ አንዲት ፍሬ ልጅ እንባዋ እየወረደ እንዲህ አለች" አባቴ በሹፍርና ነበር የሚያስተዳድረን በኋላ ግን በአደጋ ተለይቶናል ። እናቴም ብትሆን ምንም ገቢ ያልነበራት ስትሆን ያባቴን ሞት ስትሰማ እራሷን ስታ ሆስፒታል ገባች ። በዛው የተነሳ ሽባ ሁና ቀረች ። ታዲያ ሁለት ጨቅላ ወንድሞች አሉኝ ቤት ነው ጥያቸው የመጣሁት ዘመድ ስለሌለን ዘወር ብሎ እሚያየን የለም ።
እሚላስ እሚቀመስ የለንም ። ታዲያ ይችን ፍርፋሪ ወስጄ ሂወታቸውን ብታደጋት ብየ ነው ። እባካችሁ ለተማሪዎች እንዳትነግሩብኝ ። ትምህርቴንም ቢሆን አቋርጣለሁ። ብቻ አትናገሩብኝ እያለች አንጀት በሚያላውስ ሁኔታ ችግሯን ስትናገር ዳይሬክተሯ ልጅቷን አቅፈው አነቡ
ስለዚህ ከመፀፀት ይልቅ የሰዎችን ሁኔታ በእርጋታ ለመረዳት መሞሞከር ታላቅነት ነው።
1 199
ሪፖርተር ጋዜጣ 'እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ያለበት የውጭ ዕዳ መጠን ከ575 ዶላር መድረሱ ተነገረ' በሚል ርዕስ ይዞት የወጣው ዘገባ የተሳሳተ ነው"
ገንዘብ ሚኒስቴር
1 199
የአሜሪካ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት‼️
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የግንቦት 20ን 34ኛ የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ “የእንኳን ደስ አላችሁ” መልዕክት አስተላልፈዋል‼️
አሜሪካ“በጋራ ጉዳዮች ላይ አብሮ ለመስራት” ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ "ንግድና ኢንቨስትመንትን ለኢኮኖሚ ዕድገት ለማስተዋወቅ" እና "ሰላምን በውይይት ለማራመድ" በጋራ ጥረት ለማድረግ መዘጋጀቷን ገልጿል።
ሩቢዮ ለ"ኢትዮጵያ እና ለመላው ህዝቦቿ" የብሄራዊ ቀንን/ግንቦት 20ን/ ምክንያት በማድረግ "መልካም ምኞቱን" አስተላልፏል።
ግንቦት 20 ቀን 1983 በኢህአዴግ ጥላ ስር የታጠቁ ሃይሎች ጥምረት በደርግ ጊዜ ለ17 አመታት የዘለቀውን አረመኔያዊ አምባገነንነት አስወግዶ የአሁኑን የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ( #ኢፌዲሪ) መወለድን መንገድ በመክፈት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ወሳኝ ወቅት ነው"ብለዋል(አዩዘበሀሻ)።
1 199
ሚሽክን ኮሌጅ ህገወጥ ነው እርምጃ እወስዳለሁ እየተማራችሁ ያላችሁ አቋርጡ ምክንያቱም ፎርጅድ ነው የሚሰጣችሁ ዲግሪ ማንም የመንግስት ፈቃድ የለውም
Source academic
1 199
የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ (Mpox) መተላለፊያ እና መከላከያ መንገዱ
****************
የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ (Mpox) “ክሌድ 1” እና “ክሌድ 1ቢ” በሚባሉ በሁለት ዋነኛ የቫይረስ ዝርያዎች አማካይነት ሲሠራጭ ቆይቷል።
“ክሌድ 1” የሚባለው የቫይረሱ ዓይነት በማዕከላዊ አፍሪካ በስፋት የሚገኝ ሲሆን፣ “ክሌድ 1ቢ” የተባለው ደግሞ ከ“ክሌድ 1” ኋላ እየተስፋፋ ያለ እና በጣም አደገኛ መሆኑ ይነገራል።
በፈረንጆቹ 2022 ቀለል ያለው እና በምዕራብ አፍሪካ የሚገኘው “ክሌድ 2” የተባለው የበሽታው ዝርያ በዓለም ዙሪያ በወረርሽኝ መልክ ተከስቶ እንደነበር መረጃዎች ያመላክታሉ።
በወቅቱ በሽታው ቫይረሱ ተከስቶባቸው የማያውቁት የአውሮፓ እና የእስያ አገራትን ጨምሮ 100 በሚጠጉ አገራት ውስጥ ተከስቶ ነገር ግን ለበሽታው ተጋላጭ የሆኑ ሰዎችን በመከተብ ወረርሽኙ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የበሽታው ምልክቶች
በዝንጀሮ ፈንጣጣ በተያዘ ሰው ላይ መጀመሪያ የሚታዩት ምልክቶች ትኩሳት፣ ራስ ምታት፣ እብጠት፣ ጀርባ ህመም እና የጡንቻ ህመምን ያካትታል።
ትኩሳት ከተከሰተ በኋላ ከፊት ጀምሮ ቀሪውን የሰውነት ክፍልን የሚያዳርስ ሽፍታ የሚከሰት ሲሆን፣ በአብዛኛው በእጅ መዳፍ እና በእግር መረገጫ ላይ ይከሰታል።
በሰውነት ላይ የሚያጋጥመው ሽፍታ በጣም የሚያሳክክ እና የሚቆጠቁጥ ሲሆን፣ በተለያዩ የለውጥ ደረጃዎች ውስጥ አልፎ በመጨረሻም እብጠት በመፍጠር ኋላ ላይም ይከስማል። ቁስለቱም ጠባሳን ትቶ ሊያልፍ ይችላል።
በሽታው በአብዛኛው ከሁለት እስከ ሦስት ሳምንት ባለው ጊዜ ውስጥ በራሱ የሚጠፋ ይሆናል።
በበሽታው የተያዘው ሰው በጣም የተጎዳ ከሆነ፣ ቁስለቱ አጠቃላይ ሰውነቱን፣ በተለይ አፍ፣ ዐይን እና የመራቢያ አካላት ላይ ከባድ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል።
የበሽታው ከሰው ወደ ሰው የመተላለፊያ መንገድ
በሽታው ቤተ ሙከራ ውስጥ በሚደረግ ምርመራ የሚገኝ ቫይረስ ሲሆን፣ በሰውነት ንክኪ ይተላለፋል።
የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወሲባዊ ግንኙነትን፣ የቆዳ ንክኪን እና በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ማውራትን ወይም መተንፈስን ጨምሮ በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር በሚኖር የቀረበ ግንኙነት ከሰው ወደ ሰው ይተላለፋል።
የበሽታው ቫይረስ ወደ ሰውነት በቆሰላ ቆዳ፣ በመተንፈሻ አካላት፣ በዐይን፣ በአፍንጫ ወይም በአፍ በኩል ሊገባ ይችላል።
በቫይረሱ የተበከሉ የመኝታ አልባሳት፣ በልብሶች እና በፎጣዎች አማካይነት በሚኖር ንክኪም በሽታው ሊተላለፍ ይችላል።
ቫይረሱ ካለባቸው ዝንጀሮ እና አይጦችን ከመሳሳሉ ጋር የሚኖር ንክኪም ሌላኛው የበሽታው መተላለፊያ መንገድ ነው።
ከሁለት ዓመት በፊት የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዓለም ዙሪያ በበርካታ ሀገራት ውስጥ በተከሰተበት ጊዜ ቫይረሱ በዋናነት በወሲባዊ ግንኙነት በሚፈጠር ንክኪ አማካይነት ነበር የተሠራጨው።
ባለፈው ዓመትም በዲሞክራቲክ ኮንጎ ውስጥ የተከሰተው የበሽታው ወረርሽኝ የተስፋፋው በወሲባዊ ግንኙነት በሚፈጠር ንክኪ ሲሆን፣ ነገር ግን በሌሎችም አካባቢዎች ተመሳሳይ ቫይረስ ሊገኝ ችሏል።
መከላከያ እና ህክምናው
የዝንጀሮ ፈንጣጣን ለማከም የተዘጋጀ ህክምና የታመሙ ሰዎችን ለማዳን በጣም ጠቃሚ ቢሆንም፣ ነገር ግን ህክምናው ምን ያክል ውጤታማ እንደሆነ የሚያሳይ ውስን ጥናት እንዳለ ነው የሚገለጸው።
የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወረርሽኝን፣ በሽታውን በመከላከል መቆጣጠር የሚቻል ሲሆን፣ ይህንንም ለማድረግ ተመራጩ መንገድ የመከላከያ ክትባት መስጠት ነው።
በአሁኑ ጊዜ ሦስት በሽታውን መከላከያ የክትባት ዓይነቶች ቢኖሩም፣ ክትባቶቹ የሚሰጡት ለበሽታው ተጋላጭ ለሆኑ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር የቀረበ ንክኪ ላላቸው ብቻ ነው።
ይሁንና ያሉት የክትባት ዓይነቶች አዲስ ከተከሰተው የበሽታው ዝርያ አንፃር ምን ያክል የመከላከል አቅም አላቸው የሚለውን ለማወቅ ተጨማሪ ሙከራዎች ማድረግ ስለሚያስፈልግ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ሁሉም ሰው መከተብ አለበት ብሎ አይመክርም።
ባለፈው ዓመትም የአፍሪካ ህብረት ለኮቪድ ተመድቦ ከነበረ ገንዘብ ላይ 10.4 ሚሊየን ዶላር ለሲዲሲ በመስጠት የዝንጀሮ ፈንጣጣን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት መደገፉን የቢቢሲ ዘገባ አመላክቷል።
የአፍሪካ ሲዲሲ እንደሚለው ካለፈው ዓመት ጥር መጀመሪያ አንስቶ እስከ ሐምሌ መጨረሻ ድረስ ባሉት ሰባት ወራት ውስጥ ከ14 ሺህ 500 በላይ በዝንጀሮ ፈንጣጣ የተያዙ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ከ450 በላይ ሰዎች ደግሞ በበሽታው ህይወታቸው አልፏል።
የበሽታው ክስተት 96 በመቶው በዲሞክራቲክ ኮንጎ ውስጥ የተመዘገበ ሲሆን፣ ጎረቤት ወደሆኑት እና የዝንጀሮ ፈንጣጣ እምብዛም ወደ ማይታወቅባቸው ቡሩንዲ፣ ኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ኡጋንዳ ተስፋፍቶ እንደነበርም ይታወሳል።
1 199
ትናንት ወ ዛሬ
🙏🙏🙏🙏🙏
📌📌📌📌📌
✍️✍️✍️✍️
🙏 በፊት፡ ልጆች በማኅበረሰቡ ይታነጹ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ልጆች ማኅበረሰቡን ይፈራሉ
🙏በፊት፡ ግንኙነቶች በፍቅር ላይ ይመሠረቱ ነበር
📌 ዛሬ ግንኙነቶች በገንዘብ ላይ ይመሠረታሉ
🙏 በፊት፡ ስኬት የሚለካው በጠንካራ ሥራ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ስኬት የሚለካው በትውውቅ ነው
🙏 በፊት፡ ሰዎች ለመኖር ይሠሩ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ሰዎች ለመሥራት ይኖራሉ።
🙏 በፊት፡ ሰዎች ለቤተሰብ ዋጋ ይሰጡ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ሰዎች ለግለኝነት ዋጋ ይሰጣሉ
🙏 በፊት፡ ጤና ቅድሚያ ይሰጠው ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ሀብት ቅድሚያ ይሰጠዋል።
🙏 በፊት፡ ሰዎች ትዕግስት ነበራቸው
📌 ዛሬ ግን፡ ሰዎች ፈጣን እርካታን ይፈልጋሉ።
🙏 በፊት፡ ትምህርት ስለ ዕውቀት ነበር
📌 ዛሬ ግን ትምህርት ስለ ወረቀት ነው
🙏 በፊት፡ የምንግባባው ፊት ለፊት ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ የምንግባባው በስልኮችና ኮምፒውተሮች ነው።
🙏 በፊት፡ ህይወት ቀለል ያለች ነበረች
📌 ዛሬ ግን፡ ህይወት የተወሳሰበች ናት።
🙏 በፊት፡ ሰዎች ተፈጥሮን ለማድነቅ ጊዜ ይወስዱ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ሰዎች ችላ ይሏታል።
🙏 በፊት፡ ሰዎች ከባህላቸው ጋር የተቆራኙ ነበሩ
📌 ዛሬ ግን፡ ባህል እየደበዘዘ ነው።
🙏 በፊት፡ ቤተሰቦች በጋራ ይጸኑ ነበር
📌ዛሬ ግን፡ ቤተሰቦች እየፈራረሱ ነው
🙏 በፊት፡ መተማመን በጊዜ ሂደት ይገነባ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ መተማመን በቀላሉ ይሰበራል።
🙏 በፊት፡ ሰዎች ለታማኝነት ዋጋ ይሰጡ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ሰዎች ለማስመሰል ዋጋ ይሰጣሉ።
🙏 በፊት፡ ሽማግሌዎችን እናከብር ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ጥበባቸውን እንጠራጠራለን።
🙏 በፊት፡ ደግነት የተለመደ ነበር፤
📌 ዛሬ ግን፡ ደግነት ብርቅ ሆኗል።
🙏 በፊት፡ ሰዎች በረጅም ጊዜ ግቦች ላይ ያተኩሩ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ በአጭር ጊዜ ትርፍ ላይ ያተኩራሉ
🙏 በፊት፡ ሀብታችንን እንካፈል ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ለብቻችን እናከማቻለን።
🙏 በፊት፡ ሰዎች የቤተሰብ ወጎችን ከፍ ያደርጉ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ወጎች እየተረሱ ነው።
🙏 በፊት፡ ሰዎች በህብረት ይሠሩ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ሰዎች እርስ በርስ ይቃረናሉ።
🙏 በፊት፡ በቀላል ነገሮች እንደሰት ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ውስብስብ ፍላጎቶችን እናሳድዳለን።
🙏 በፊት፡ ሰዎች በእድገት ሂደት ላይ ትዕግስት ነበራቸው
📌 ዛሬ ግን፡ ሰዎች ፈጣን ስኬትን ይፈልጋሉ።
🙏 በፊት፡ ሰዎች የውስጥ ስሜታቸውን ያምኑ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ሰዎች ቴክኖሎጂን ያምናሉ።
🙏 በፊት፡ ከስህተቶቻችን እንማር ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ችላ እንላቸዋለን።
🙏 በፊት፡ የማኅበረሰብ ድጋፍን ከፍ አድርገን እንመለከት ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ በራስ መቻልን እናደንቃለን።
🙏 በፊት፡ የምንኖረው በመርህ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ የምንኖረው እንደ ምቾታችን ነው።
🙏 በፊት፡ ግንኙነቶች እንክብካቤ ይደረግላቸው ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ግንኙነቶች እንደማይፈለግ ዕቃ ይጣላሉ
🙏 በፊት፡ ሰዎች ለወደፊቱ ይሠሩ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ሰዎች ለቅጽበት ይኖራሉ።
🙏 በፊት፡ አካባቢያችንን እንንከባከብ ነበር
📌 ዛሬ ግን፡ ቸል ብለነዋል
👉 Tewanay
1 199
አዲሱ የእነ አቶ ጌታቸው ረዳ "ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ" ፓርቲ ጊዜያዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ ፈቃድ ተሰጠው
ግንቦት 18/2017 (አሐዱ ሬዲዮ)
