cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

U.S.A United Students Of Amhara አ.ተ.ህ አማራ ተማሪዎች ህብረት

#አምሓራዊነት፦ የአዲሱ ትውልድ፣ ንቃት ምልክት! የህልውናችን ዋስትና መስመረ ርዕዮት…

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
1 478
مشترکین
+424 ساعت
+267 روز
+15930 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

መልካም ዜና! ፍርክስክሱ እየወጣ ያለው የአብይ ወንበር ጠባቂ ሀይል ዛሬ በቃኝ ከህዝብ ጋር አንዋጋም ብለው ፋኖን ተቀላቀሉ። ከደቡብ ወሎ ቦረና ሳይንት ደገር ከተማ  ተነስተው ሸዋ ጠቅላይ ግዛት መረሃቤቴ አውራጃ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በዚህም 1ብሬን እና 1 እስናይፐር 4 ባለሀዲዱ ጥቁር ክላሽ በመያዝ አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አፄ ዳዊት ክፋለጦርን ተቀላቅለዋል 💪ይ ቀ ጥ ላ ል። https://t.me/Beteamharavoice
نمایش همه...
U.S.A United Students Of Amhara አ.ተ.ህ አማራ ተማሪዎች ህብረት

#አምሓራዊነት፦ የአዲሱ ትውልድ፣ ንቃት ምልክት! የህልውናችን ዋስትና መስመረ ርዕዮት…

👍 3
~ሰበር ዜና‼️~ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዘድንት ዶናልድ ትራምፕ ላይ የግድያ ሙከራ መደረጉ ተሰምተል:: ትራምፕ በፔንስልቬንያ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ከተኩስ በኋላ ከመድረክ ወጡ አሜሪካ ውስጥ በፔንስልቬንያ ቅዳሜ ምሽት በቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የድጋፍ ሰልፍ ላይ በተተኮሰ ጥይት ትራምፕ ከጥቃቱ ተርፈዋል።  ከፍተኛ ድምጽ ካሰሙ በኋላ በፍጥነት ከመድረክ እንዲለቁ ተደርገዋል። በትለር ካውንቲ አውራጃ አቃቤ ህግ ሪቻርድ ጎልዲገር እንደተናገሩት አንድ ታዳሚ እና ታጣቂው ከተኩሱ በኋላ ሞተዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል። https://t.me/Moamediamoresh
نمایش همه...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

⭐️⭐️⭐️💡ዓውደ ፋኖ💡⭐️⭐️⭐️ 🫵 🫵 "#አይበገሬው ሰሜናዊ ኮከብ" ዝና፣ እና ክብር ዓለም ዓቀፍም ሽልማት በተገቢው ስፍራ እና ቦታ፣ በፍትሃዊ ማደሪያው ይገኝ ዘንድ ምድሪቷ በሀቅ መንገድ ብትራመድ ይሄን ብርቱ ከዐለት የጠነከረው #ሰው የሚያልፈው አንዳች ክብረ ሞገስ ባልኖረ… #ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ… አዎ፣ ስለርሱ ላወራችሁ ነው። የዛሬው የዓውደ ፋኖ ገፅ እንግዳዬ ነው። ስለዚህ፣ መንጋ እና ቲፎዞ አልባ ታጋይ ጥቂት ልል ብችል እንጅ… የዘመኑን ምልዐት፣ የትውልድ ውርስ በደም ዋጋ የታጀበ በሰቆቃ አመታት ውስጥ የተሻገረ፣ ዛሬው በተጋድሎ ዐውድ ላይ ስለሚገኘው መራራ መርህ መር ታጋይነቱን በዚህች ቅፅበት አትቼ አልጨርሰውም። እርሱ ግን፣ ፍፁም ትሁት ነው። እጁን ጨብጦ ከፍ በማድረግ "ትግልን ከኔ በላይ ለዐሳር" ሲል አታዩትም። ሲበዛ አይን አፋር እና የደግነት ባለ ፀጋ ነው። በጋዜጠኝነት ደሞዙ… 4 በኦሮሚያ ቤተሰቦቻቸው በግፍ የተገደሉባቸው ወላጅ አልባ ህፃናትን ያሳድጋል፣ እጅ ሲያጥረው በስሙ ይለምንላቸዋል። ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ፣ ያልተገለጠ መፅሀፍ ነው። ይህ፣ ሰው… ለውጥ የተባለው ጎርፍ ገፍቶ ያመጣው ሰሞነኛ ፖለቲከኛ፣ የዩቲዩብ አማላይ ክፍያ ወደ ሜዳ ያወጣው ጋዜጠኛም አይደለም። ከዚህ በታች… የማወጋላችሁ በጀብዱ የተሞላው ታሪከ ማስታወሻው… ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ ያልተዘመረለት ካባ ያልደረብንለት ፣ የሰራን ቆፍረን አክባሪ ያለመሆናችንን ያሳብቅብናል። አባይ ዘውዱ… ሰሜናዊ ነበልባል #ፋኖ ኮከባችን… በኦህዴድ መራሹ የብልጽግና አገዛዝ ዳግም በግፍ እስር ላይ የሚገኘው ዓባይ ዘውዱ ማን ነው⁉️ ስለ ዓባይ ዘውዱ አጠር ያለ መረጃ ለማጋራት ወደናል። ዓባይ ዘውዱ ደመቀ የተወለደው በድሮው አጠራር በሰሜን ጎንደር ዞን በጭልጋ ወረዳ ዳዋ ዳንጉራ ልዩ ስሙ መንደር ጊዮርጊስ በተባለ ለማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ አዋሳኝ በሆነውና መዳረሻውን ሱዳን ድረስ ያደረገው የጓንግ ወንዝ በሚለዬው ቀበሌ ነው። ዓባይ ምንም እንኳ በጭልጋ ወረዳ መንደር ጊዮርጊስ ይወለድ እንጅ እድገቱን ያደረገውና እስከ 6ኛ ክፍልም የተማረው በድሮው አጠራር ታች አርማጭሆ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ለአስተዳደር ያመች ዘንድ በሚል ማዕከላዊ አርማጭሆ ተብሎ ራሱን በቻለው ወረዳ ማሰሮ ደንብ ነው። ዓባይ በልጅነቱ ወደ ማዕከላዊ አርማጭሆ የተወሰደው አባቱ አቶ ዘውዱ ደመቀን እና ቤተሰቦቹን "ለለውጥ እየታገሉ ነው፣ እምቢተኛ ናቸው፣ እየተገዙን አይደለም" በሚል ደርግ አባቱን ወደ ጭልጋ አፍኖ በመውሰድ ማሰር እና ማንገላታቱን ተከትሎ ነው። በወቅቱ ዘውዱ ደመቀ ብቻ አልነበረም ከመንደር ጊዮርጊስ ቀበሌ የታፈነው ምንም እንኳ ከአጭር ጊዜ የእስር ቆይታ በኋላ ከዳንጉራ እስር ቤት የተለቀቁ ቢሆንም አባቱ ደመቀ ሁነኛው፣ ታላቅ ወንድሙ መልካሙ ደመቀ እና ታናሽ ወንድሙ ጌጡ ደመቀም አብረው ታስረው ነበር። ዘውዱ ደመቀ ግን 'ይህ ነው ዋናው' በሚል ተፈርጆ ወደ ጭልጋ ወረዳ አይከል ማ/ቤት ተወስዶ ከ6 ወራት የግፍ እስር በኋላ መፈታቱን ተከትሎ ነው ባለቤቱን ባንች አምላክ በለጠን እና ልጆቹን ይዞ የጓንግን ወንዝ ከማዶ እና ማዶ ሶስትና አራት ረዣዥም እንጨት ጣል በማድረግ በሰራው ጊዜያዊ መሻገሪያ ድልድይ ተሻግሮ ወደ ማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ማሰሮ ደንብ ያቀናው። የመጀመሪያ ወይም የበክር ልጅ የሆነው ዓባይ ዘውዱ በጭልጋ ወረዳ መንደር ጊዮርጊስ ተወልዶ በአርማጭሆ ማሰሮ ደንብ ወረዳ ሳንኪ ሚካኤል ነው እድገቱን ያደረገው። ዓባይ የተወለደበት ብቻ ሳይሆን ያደገበት አካባቢም በአብዛኛው በተራራ ሰንሰለት እና በተፈጥሮ የታደለ አካባቢ ነው። ዓባይ የት ተማረ? የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን እስከ 6ኛ ክፍል የተከታተለው በማሰሮ ደንብ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ሲሆን የ7ኛ ክፍል ትምህርቱን ደግሞ በታች አርማጭሆ ወረዳ ሳንጃ ት/ቤት ነው። ዓባይ ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን የተከታተለው በባህር ዳር ነው። ይኸውም፦ 1) 8ኛ ክፍል_በባህር ዳር ቁልቋል ሜዳ ት/ቤት፣ 2) 9ነኛ እና 10ኛ ክፍል_በባህር ዳር ፋሲሎ ት/ቤት፣ 3) 11ኛ እና 12ኛ ክፍል ትምህርቱን በባህር ዳር መሰናዶ ት/ቤት እንዲሁም 4) የዩኒቨርስቲ ትምህርቱንም በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ፔዳ ካምፓስ የተከታተለ ሲሆን በጋዜጠኝነትና ግንኙነት (Journalism and Communications) ትምህርት ዘርፍ 3.66 በማምጣት በከፍተኛ ማዕረግ እና በሽልማት ተመርቋል። የትግል ሁኔታን በተመለከተ? በተለያዩ ጊዜያት በልዩ ልዩ በመድረክ እና በጽሁፍ ሲያደርገው የነበረው ትግል እንዳለ ሆኖ በዋናነት ከ2005 ዓ/ም ጀምሮ ነው የህወሀት እና ህወሀት ተሸናፊ እና ተንበርካኪ አድርጎ የሰራውን የብአዴን ስርዓትን አምርሮ በመጥላት አንድነት ለፍትህ እና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት)ን ተቀላቅሎ ታግሏል። በተለይ በህወሀት በሀይል ከአማራ የተወሰደው የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እና ራያ እንዲሁም በሱዳን በጎንደር በኩል የሀገር ሉኣላዊነት ተደፍሮ የተወሰደው ሰፊ ለም መሬት እና በተለያዩ አካባቢዎች በአማራ ህዝብ ላይ ይደርስ የነበረው ሁለንተናዊ ግፍ እና በደል ወደ አንድነት ትግሉ በመግባት ከብርቱ ለውጥ ፈላጊ እና የነቁ ጓደኞቹ ጋር በመሆን በአብርሃጅራ ከተማ ቢሮ በመክፈት ጭምር አገዛዙን እንዲታገል ገፋፍቶታል። በለውጥ ትግሉ መስዋዕት ከሆኑት ነፍሳቸውን ይማርና ከእነ ደስታው ተገኘ፣ አንጋው ተገኘ እና ታናሽ ወንድማቸው ባበይ ተገኘ ጋር በመናበብ አገዛዙን ይታገል ነበር። ደስታው ተገኘ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ አገዛዙን ለመታገል ሲመለስ በአብደራፊ/ምድረገነት አካባቢ ባጋጠማቸው ውጊያ ዶ/ር ብርሃኑ ከተባለ የትግል ጓዱ ጋር ስለ አማራ ህዝብ እና ስለ ሀገር ሲል በጀግንነት በክብር የተሰዋ ሲሆን ወንድሞቹ አንጋው ተገኘ እና ታናሻቸው ባበይ ተገኘ ደግሞ እምብኝ ለወገኔ በማለት በመጋቢት 2016 ዓ/ም ኦህዴድ መራሹን የብልጽግና አገዛዝ በነፍጥ ሲፋለሙ በክብር የተሰው ጀግኖች ናቸው። ዓባይ ከእነ እንግዳው ዋኘው፣ ስርዓቱ ለሰላማዊ ትግል ዝግጁ አይደለም በማለት ወደ ኤርትራ በማቅናት የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባርን ተቀላቅለው ሲታገሉ ከነበሩት ከእነ አብርሃም ልጃለም፣ ከአለልኝ እና ከሌሎችም ጋር በመሆን በምዕራብ ጎንደር ዞን አብርሃጅራ ሲታገሉ ነበር። ከእነ አለላቸው አታለል፣ ቀለብ ስዩም፣ ተገኘ ሲሳይ፣ በላይነህ ሲሳይ፣ አለባቸው ማሞ፣ ፈረጃ ሙሉ፣ ሰጠኝ ቢልልኝ፣ አወቀ፣ እንዲሁም ከአነ አግባው ሰጠኝና ከሌሎች ጀግኖች ጋርም በመናበብ አብሮ ለእውነተኛ እና ስር ነቀል ለውጥ ይታገል ነበር። ዓባይ ዘውዱ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ሲታገል ስለደረሰበት እስር፦ (1) በህወሀት ኢህአዴግ ዘመን ከጥቅምት 25/2007 ጀምሮ እስከ ህዳር 2010 ድረስ በፈጠራ የሽብር ክስ 4 ዓመት ከ2 ወር ተፈርዶበት ታስሯል። በአብርሃጅራ፣ በጎንደር 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣በባህር ዳር 9ነኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ በአዲስ አበባ ማዕከላዊ፣ በቂሊንጦ፣ በሸዋሮቢትና በዝዋይ በእስር ተሰቃይቷል። (2) በኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ ደግሞ ስለ ሰፊው የአማራ ህዝብ እና ስለተገፉ ወገኖች ድምፅ በመሆኑ 4 ጊዜ ታስሯል። ይኸውም፦ 1) ሀምሌ 10/2013 ዓ/ም በአዲስ አበባ አውቶብስ ተራ እና በመርካቶ አራተኛ ፖሊስ ጣቢያ ስለምን ለአማራ ተፈናቃዮች ድምጽ ሆንክ በሚል ታስሯል።
نمایش همه...
3
2) ጳጉሜ 3/2014 ዓ/ም በአዲስ አበባ ሜክሲኮ እና በአባ ሳሙኤል ታስሯል። 3) መጋቢት 28/2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ሜክሲኮ እና በአዲስ አበባ ፖሊስ (ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ) ታስሯል። 4) ነሃሴ 4/2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ሜክሲኮ፣ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ እና በቂሊንጦ ታስሯል፤ በአማራዊ ማንነቱ እና በጋዜጠኝነት ሙያው ለህዝብ ድምፅ በመሆኑ እና ስር ነቀል ስርዓታዊ ለውጥ እንዲመጣ በመታገሉ አሁንም በግፍ እስር ላይ ይገኛል። ዓባይ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ-ደቡብ እዝ መከላከያ ካምፕ ለ6 ወራት ያህል በኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ ታግቷል፤ በሜክሲኮ የፌደራል ወንጀል ምርመራ ቢሮም ከ2 ወራት በላይ ከሌሎች የአማራዊ ማንነት ታጋቾች ጋር በሩ እንዲዘጋ ተደርጎ ታስሯል፤ ከሜክሲኮ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ተዛውሮም ታስሯል። ዓባይ አሁን ላይ የፈጠራ የሽብር ክስ ተመስርቶበት በቂሊንጦ እስር ቤት ይገኛል። 4 ዓመት ከ6 ወራት በላይ በታች አርማጭሆ እና በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳዎች በባህል እና ቱሪዝም የፕሮሞሽን ባለሙያነት እንዲሁም በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገለው ዓባይ ዘውዱ ህዳር 1/2010 ዓ/ም ከዝዋይ ማ/ቤት ተፈታበት ጊዜ ጀምሮም በጋዜጠኝነት ሙያው በሽብር ተግባር የተሰማራውንና የህወሀት ኢህአዴግ ተቀጥላ የሆነውን የኦህዴድ ብልጽግን አገዛዝና የስሪቱን ገመና በማጋለጥ ጭምር እየታገለ ይገኛል። ዓባይ ዘውዱ እና ቤተሰቦቹ ስለ እውነተኛ ለውጥ በሚል ኢሰብአዊነትን በመቃወም የከፈሉት መስዋዕትነት ከባድ ነው። በማንኛውም ስርዓታዊ ፈተና ሁሉ ከጎኑ የቆሙ ወገኖችን በሙሉ በእጅጉ ያመሰገነው ዓባይ ህዝባዊ ትግል ማሸነፉ አይቀርም ይሏል። ፍትሃዊ የሆነው የአማራው የህልውና፣ የነፃነት፣ የክብር፣ የእኩልነት እና የአብሮነት ትግል ያሸንፋል! ክብር ለጀግኖች ሰማዕታት ይሁን! ፍትህ ለሁሉም! #ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ! https://t.me/Moamediamoresh
نمایش همه...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

2
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.