cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

ትክክለኛ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ! #Ethiopia #Ethiopianews #Addismereja

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
3 244
مشترکین
-124 ساعت
+207 روز
+4630 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

#👇 የሶፊያ ሽባባው መልዕክት ነው👇 አባካችሁ እኔን ደካማዋን መነጋገሪያ ማድረግ ትታችሁ ብርቱ ስለሆነው ስለክርስቶስ ፍቅር ተነጋገሩ!!! ስለንጉሱ መነጋገር ትታችሁ ስለኔ ስለማልጠቅም ባሪው እንደትልቅ ነገር አታውሩ!!!ስለሱ ማውራት ብዙ ላይክና ኮሜንት ባያስገኝ ብዙ ሽልማትና አክሊል ያስገኛለል!! በዲያቆን ዘማሪያም የሰርግ ስነስርአት ተጋብዤ በቦሌ መድሀኒአለም ቤተክርስቲያን ስገኝ አገልጋዮች ሁሉ በደስታ ተቀብለውኛል። ብዙ ስትቆሚ እንዳይደክምሽ ብለው መቋሚያ ሰጥተውኛል። አቤት ጨዋነታቸው ፣አቤት አክብሮታቸው፣አቤት ፍቅራቸው። ሁሉን በተራ እያቀፍኩ ፍቅሬን ብገልጽላቸው  ደስ ባለኝ። ይህቺን ፎቶ ነጥላችሁ ወስዳችሁ ወደኦርቶዶክስ ተመለሰች እያላይሁ በመሄዴ መቋሚያ በመያዜ የምሳቀቅ መስሏችሁ  አቧራ የምታስነሱ ፕሮቴስታንት ወንድሞቼ ኦርቶዶክስ ሆነች ብትሉኝ የሚያሳፍረኝ አይደለም።የሚያሳፍረኝ ክርስቶስን አለማመንና አለማምለክ ብቻ እንጅ ሌላ አይደለም። ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤቴ ናት።ባሳደገችኝ ቤተክርስቲያኔ መገኘቴ ርዕስ ሊሆን አይገባም።የዘወትር ርዕሳችሁ ከመታወቅ የሚያልፈው የክርስቶስ ፍቅር ይሁን።ምክንያት እየፈለጋችሁ የሚከፋፍልና የሚያራርቅ ነገር ከምትሰሩ የክርስቶስን ፍቅር ስበኩ ወንጌል ይሄ ብቻ ነው።በሄድኩበት በመድሀኒአለም ቤተክርስቲያን ወንጌል ነው የተሰበከው እናንተም ስለአንዲት ደካማ ግለሰብ ወሬ ማናፈስ ትታችሁ ብርቱ ስለሆነው ክርስቶስ ፍቅር ስበኩ።ካልቻላችሁም ዝም በሉና ወደ ንግድ ወይም ሌላ ስራ ተሰማሩ። ከንቱ ድካም አትድከሙ ይልቅ ወሬና አሉባልታ ተውና ስራ እንስራ።ከአሮጊቶች ተረት ወጥተን ድህነትን እንዋጋ። ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇👇 https://t.me/Satenawmedia1
نمایش همه...
👍 3👏 2🥰 1
#በጂንካ የ8 ዓመት ታዳጊን  አስገድዶ ግብረ ሶዶም  ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ  ጽኑ እስራት ተቀጣ በጂንካ ከተማ በ8 ዓመት ታዳጊ ልጅ ላይ የአስገድዶ ግብረ ሶዶም   መድፈር ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በጽኑ እስራት እንደተቀጣ የጂንካ ከተማ ፍትህ ጽ/ቤት አስታዉቋል፡፡ የጂንካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ግንቦት 2 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት ውሳኔዉን በተከሳሹ ላይ አስላልፎበታል፡፡ተከሳሽ ወጣት ማንያዘዋል አዳሙ  የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 2:00 ሰዓት አከባቢ ድርጊቱን መፈፀሙን በማመኑ ባመነው መሰረት ማስረጃ መስማት ሳያስፈልግ  ውሳኔ እንደተሰጠ የጂንካ ከተማ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት  አቶ በቃሃኝ ጥላሁን  በተለይም  ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል  ። ተከሳሽ የግል ተበዳይን እኔ ጋር  አሳድራለው በማለት ከቤተሰቦቹ  በመውሰድ ህፃኑን አስገድዶ  ግብረ ሶዶም ወንጀል  መፈፀሙ አረጋግጧል ። አሰገድዶ የመድፈር ወንጀል የደረሰበትን ህፃን ለጤናም ሆነ ለስነ-ልቦና ጉዳት የሚዳርግ ተግባር ከመሆኑ አንጻር በጂንካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሰጠው  ውሳኔ ተከሳሽንና ሌሎችንም  መሠል ወንጀል አድራጊዎችን የሚያስተምር ውሳኔ አስተላልፎበታል፡ በመሆኑም  ግንቦት 2 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት አስገድዶ ግብረ ሶዶም መፈፀሙን ሙሉ በሙሉ በችሎት ቀርቦ በማመኑ የጂንካ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤት  በ15 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ  መወሰኑን አቶ በቃኀኝ ጥላሁን ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል  ፡፡ Via:በኤደን ሽመልስ https://t.me/Satenawmedia1
نمایش همه...
1
#ማይክ ሀመር ከኦሮሞ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ከፕሮፌሰር መረራ ጉዲና እና ዳውድ ኢብሳ ጋር መምከራቸው መከሩ የአሜሪካን መንግስት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሀመር #ከኦሮምያ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር ተወያዩ። ሀመር የመከሩት ከኦፌኮ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና እና ከኦነጉ ሊቀመንበር ዳውድ ኢብሳ ጋር መሆኑም ታውቋል። የኦፌኮ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ከማይክ ሀመር ጋር በሀገራዊ እንዲሁም በኦሮምያ ክልል ወቅታዊ ጉዳዮች መምከራቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ አረጋግጠዋል። በሀገራዊ እና በኦሮምያ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለማይክ ሀመር ሙሉ ገለጻ እንዳደረጉላቸው ፕሮፌሰር መራራ ለአዲስ ስታንዳርድ አስታውቀዋል። ከማይክ ሀመር ጋር በነበረን ቆይታ ዋነኛ አጀንዳ የነበረው ሀገራዊ ምክክሩ ነበር ሲሉ የገለጹልን ፕሮፌሰር መረራ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ "ኢትዮጵያን የትም አያደርሳትም፣ ምክንያቱም ደግሞ ሁሉን ያሳተፈ አይደለም፣ በሁሉም ዘንድ ደግሞ እምነት የሚጣልበት አይደለም" ሲሉ እንደገለጹላቸው ለአዲስ ስታንዳርድ አስታውቀዋል። ሌላኛው ከማይክ ሀመር ጋር በነበረን ውይይት የተነሳው ነጥብ የበቴ ኡርጌሳ ግድያ ነበር ያሉት መረራ ጉዲና የፈጠረባቸውን ድንጋጤ እና የቤተሰቦቹ እስር እንዳሳዘናቸው በመግለጽ ስሜቴን ለልዩ ልዑኩ አጋርቻለሁ ብለውናል። በተያያዘ ዜና የአሜሪካ መንግስት ልዩ ልዑኩ ማይክ ሀመር በአዲስ አበባ በሚገኘው የአሜሪካን ኤምባሲ ከኦነጉ ሊቀመንበር ዳውድ ኢብሳ ጋር መምከራቸውም ከፓርቲያቸው ቃል አቀባይ ለሚ ገመቹ የኤክስ ማህበራዊ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። ዳውድ ኢብሳ እና ማይክ ሀመር በምን ጉዳዮች ላይ እንደመከሩ ቃል አቀባዩ ያሉት ነገር የለም። https://t.me/Satenawmedia1
نمایش همه...
#ወደር-የለሽ አበርክቶት ከዓመታት በፊት ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንድ የሆነ ዶኩመንት ለማዘጋጀት ከተለያዩ ካምፓሶች የተውጣጣን የሥራ ኃላፊዎች በአቃቂ ካምፓስ (አሁን ለቀድሞ ባለቤቱ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተመለሰ) ተገናኝተን ነበር። በወቅቱ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን የነበሩት ታዋቂ የአእምሮ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ተማሪ የነበሩ (ስላላስፈቀድኩ ስማቸውን አልጠቅስም) በአጋጣሚ ስለ መምህራቸው ብዙ ነገር አጫወቱኝ። አንድ የማልረሳው ፕሮፌሰር አሥራት በአንዱ ቀን ከፍተኛ ትኩረት የሚፈልገውን የቀዶ ሕክምና ትምህርት (ትምህርቱ ቀዶ ሕክምና በሕመምተኛ ላይ እየተከናወነ ነው የሚሰጠው) ክላስ ተደራርቦባቸው በከፍተኛ መጠን እግራቸው ተንቀጥቅጦ ሊወድቁ ሲሉ እያጫወተኝ ያለው ፕሮፌሰር እና ሌሎች ተማሪዎች አፈፍ አድርገው ያዟቸው። ''ያን ቀን ምን ያህል ቢያስተምሩ ነው?'' አልኩት። ለተከታታይ 18 ሰዓት'' አላለኝም??? ለፕሮፌሰር አሥራት እና ለአጋር የሕክምና መምሕራን ተከፍሎ የማያልቅ ውለታ አለብን። ምሥጋና በጣም ያንሳል! ልክ የዛሬ 25 ዓመት በዛሬው ዕለት ሕይወታቸው ያለፈው ፕሮፌሰር አሥራት እጅግ የተከበሩ እና የተወደሱ (Most Distinguished) የቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት፣ የሕክምና ፕሮፌሰር፣ የአፄ ኃ/ሥላሴ የግል ሐኪም፣ ፖለቲከኛ እና በሁለት መንግሥታት የግፍ እስር የደረሰባቸው ኋላም ለሞት ተላልፈው የተሰጡ ምርጥ ዜጋችን ነበሩ። ፕ/ር አሥራት ወ/የስ በሕክምናው በኩል ላደረጉት ወደር-የለሽ አበርክቶ፤ የኢትዮጵያ አንድነት ተጠብቆ እንዲቆይ ላደረጉት ተጋድሎ እንዲሁም የመጣ የሔደው አጀንዳውን ለማስፈጸም እንደ ጆከር ለሚመዘው አሳዛኙ የአማራ ሕዝብ ለከፈሉት የበዛ መስዋዕትነት በእኔ በ Ordinary ዜጋዋ ልብ ውስጥ ዘላለም ተከብረው ይኖራሉ። 🙏
نمایش همه...
#inside_soccer ‼️ ማንችስተር ሲቲ የሊጉን መሪነት ተረከበ ! ማንችስተር ሲቲ ከቶተንሀም ጋር ያደረገውን የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ሰላሳ አራተኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሐ ግብር 2ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን መሪነት መረከብ ችለዋል። የማንችስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ኤርሊንግ ሀላንድ 2x ከመረብ ማሳረፍ ችሏል። ኬቨን ዴብሮይን አንድ መቶ አስራ ሁለተኛ ለግብ የሆነ ኳሱን አመቻችቶ በማቀበል በሊጉ ታሪክ ብዙ አመቻችቶ ያቀበለ #ሁለተኛው ተጨዋች ሆኗል። ኖርዊያዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኤርሊንግ ሀላንድ በውድድር ዘመኑ ሀያ ሰባተኛ የሊግ ግቡን ማስቆጠር ችሏል። ማንችስተር ሲቲ በአዲሱ የቶተንሀም ስታዲየም የመጀመሪያ የፕርሚየር ሊግ ጎል ማስቆጠር ችሏል። በሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ስንተኛ ናቸው ? 1️⃣ ማንችስተር ሲቲ :- 88 ነጥብ 5️⃣ ቶተንሀም :- 63 ነጥብ ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ? እሁድ - ማንችስተር ሲቲ ከ ዌስትሀም ዩናይትድ እሁድ - ሼፍልድ ከ ቶተንሀም Via:tikvahethsport   https://t.me/Satenawmedia1
نمایش همه...
#Mother'sDay‼️😍😍😍
የዓለማችን ጀግና እናቶች እነማን ናቸው...?
የእናቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ መከበር ከጀመረ 120 ዓመት ሊሞላው ጥቂት ዓመት ብቻ ቀርቶታል የመንግስታቱ ድርጅት በየዓመቱ በፈረንጆች ግንቦት ወር ከገባ ሁለተኛው እሁድ የእናቶች ቀን ሆኖ እንዲውል በወሰነው መሰረት እለቱ ይከበራል። እናቶች ለዓለማችን የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ለማስታወስ በሚል ከፈረንጆቹ ከ1907 ጀምሮ በየዓመቱ በመከበር ላይ ነው። እናትነት በራሱ ጀግንነት ቢሆንም በዓለም አቀፍ ደረጃ ፈተናዎችን ተቋቁመው ለየት ያሉ ስራ የሰሩ እናቶች ደግሞ ይኖራሉ። በዓለማችን በየቦታው ለልጆቻቸው እና ለዓለማችን እልፍ መልካም ስራዎችን ያበረከቱ እልፍ እናቶች ቢኖሩም በዚህ ዘገባችን ግን ጥቂቶቹን ብቻ እናነሳለን። ✅አበበች ጎበና ከ1928-2013 ዓ.ም! ኢትዮጵያዊቷ ክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ ለ41 ዓመታት በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ህፃናትን ተንከባከበው ለቁም ነገር በማብቃት ከጀግና እናቶች መካከል ይጠቀሳሉ። በ1972 ዓ.ም በኢትዮጵያ ተከስቶ በነበረው የተፈጥሮ ድርቅ ሳቢያ ወላጆቻቸውን በሞት ያጡ ሁለት ህፃናትን በመያዝ አበበች ጐበና ህፃናት ክብካቤና ልማት ማህበርን መመስረታቸውን የህይወት ታሪካቸው ያመለክታል። አፍሪካዊቷ ማዘር ቴሬዛ በመባል የሚታወቁት ክብርትዶ/ር አበበች በ41 ዓመታት በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ህፃናትን ተንከባከበው ለቁነገር ያበቁ ሲሆን፤ በተለይዩ ድህነት ቅነሳ ፐሮግራሞች ከአንድ ነጥብ አምስት ሚልዮን በላይ ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ሰጥተዋል። ✅ዶክተር ካትሪን ሃምሊን 1924-2020! አውስትራሊያቷ ዶክተር ኤሊኖር ካትሪን ሐምሊን ወደ ኢትዮያ መጥተው የፌስቱላ ሆስፒታልን ከኒውዚላንዳዊው ባለቤታቸው ዶክተር ሬጂናልድ ሐምሊን ጋር መስርተው ከ60 ዓመት በላይ አገልግለዋል። በጽንስና ማህጸን ሙያቸው በፌስቱላ ችግር የሚሰቃዩ በርካታ ሴቶች ፈውስ አግኝተው ጤናማ ኑሮ እንዲገፉ አስችለዋል። የማህጸን ሀኪም የሆኑት ዶ/ር ካትሪን ሀምሊን በኢትዮጵያ ከ60 ሺህ በላይ በፌስቱላ የተጠቁ ሴቶችን ከስነልቦናዊ እና አካላዊ ቁስለት ለማዳን ችለዋል። ✅ሜሪ ኩሪ (1867-1934)  የሁለት ልጆች እናት የሆነችው ሜሪ ኩሪ በአደጋ ምክንያት ባሏን ብታጣም ሁለት ልጆቿን ከማሳደግ ጎን ለጎን በኬሚስትሪ ዘርፍ በሰራችው ምርምር የኖቤል ሽልማትን ማግኘት ችላለች። ✅ሳጁርነር ትሩዝ! የዓለማችን ጀግና እናት በመባል የምትታወቀው ሳጁርነር ትሩዝ ስትሆን በባርነት የተሸጠው የአምስት ዓመት ወንድ ልጇን ከባርነት ለማስለቀቅ ባደረገችው ተጋድሎ ጀግና ተብላለች። ✅ካቲ ሂድብ!  የዓለማችን ጀግና እናት በመባል የምትታወቀው ካቲ ሂድብ ስትሆን ወላጅ አልባ ህጻናትን ለመርዳት ባደረጉት ጥረት ይታወሳሉ። ይህች እናት በተለይም በዚምባብዌ፣ ህንድ፣ ቦስኒያ፣ ሜክሲኮ፣ ቦሊቪያ እና ዩጋንዳ ወላጅ የሌላቸውን ህጻናት በማሳደግ የዓለማችን ባለውለታ እንደሆኑ ተገልጿል። ✅ዋሪስ ድሬ! ሶማሊያዊቷ ዋሪስ ድሬ ሌላኛዋ የዓለማችን ጀግና እናት የተባለች ሲሆን በተለይም በ13 ዓመቷ የህጻንነት እድሜዋ የቀረበላትን ጋብቻ በመሸሽ ያሳለፈቻቸው ውጣ ውረዶች ከባድ ነበሩ ተብሏል። ብዙ አስቸጋሪ የህይወት ምዕራፎችን በማለፍም ስኬታማ ሞዴል ለመሆን የበቃች ሲሆን በዓለም ላይ ያለእድሜ ጋብቻን እና የሴት ልጅ ግርዛትን የሚያስቀሩ ስራዎችን ማከናወኗ ተገልጿል። ✅ሳራህ ብሪድላቭ! የዓለማችን የመጀመሪያዋ በጥረቷ ሚሊየነር የሆነችው ጥቁር ሴት ሳራህ ብሪድላቭ ሌላኛዋ የምድራችን ጀግና እናት ተብላለች። ይህች እናት የባሪያ ንግድ ሰለባ የነበረች ሲሆን የወደፊት ህይወቴ የባሰ አስቀያሚ ሳይሆን ከድህነት መውጣት አለብኝ፣ ለልጆቼም የተሻለ ሁኔታ መፍጠርም አለብኝ በሚል ወደ ንግድ ገብታ በጥረቷ እና በላቧ ስኬታማ በመባል የብዙ እናቶች አርዓያ መሆኗ ተገልጿል። ✅ኢሬና ሴንድለር! በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ከ2 ሺህ 500 በላይ አይሁዳዊያንን ከእልቂት የታደጉት ፖላንዳዊቷ ኢሬና ሴንድለር ደግሞ ተጨማሪ የዓለማችን ጀግና እናት ተብለዋል። አይሁዳዊያንን ከናዚ እልቂት የታደጉት እኝህ እናት ድርጊታቸው መታወቁን ተከትሎ ብዙ መከራን የተቀበሉ እና እንዲገደሉ ቢፈረድባቸው በተዓምር ከሞት ተርፈው በፖላንድ መንግሥት የጀግና ሜዳሊያ ለመሸለም በቅተዋል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለማችን ብዙ ጀግና እናቶችን መጥቀስ ቢቻልም ለእርስዎ ጀግና እናት ማን ናት? ጀግና እናት ማለትስ ለእርስዎ ምን ማለት ነው? አስተያየትዎን ያካፍሉን። ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ💕 https://t.me/Satenawmedia1
نمایش همه...
ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

ትክክለኛ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ! #Ethiopia #Ethiopianews #Addismereja

👍 3 1
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አመራረጥ አዲስ መመሪያ በመዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡ ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሃብት ብክነት እና ብልሹ አሰራር ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ለፋና ቴሌቪዥን የሰጡት ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንደገለፁት፤ በትግራይ ክልል ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የሱፐርቪዥን ቡድን በመላክ ዩኒቨርሲቲዎቹ ያሉባቸውን ችግሮች መጠናቱን ገልፀዋል፡፡ "ዩኒቨርሲቲዎች የብዙ ደሃ ሕዝብ ሃብት የሚፈስባቸው ቦታዎች ናቸው" ያሉት ሚኒስትሩ፤ ስለዚህ ተቋማቱ በሙስናና ብልሹ አሰራር የተጨመላለቀ አስተዳደር ሊኖራቸው አይገባም ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲዎች በዋናነት የተማረ የሰው ኃይል ከማምረት ይልቅ፣ ህንጻ ማምረት ላይ የተሰማሩ ተቋማት እንደነበሩ ያስታወሱት ሚኒስትሩ፤ "ዩኒቨርሲቲዎች የሚታለቡ የጥገት ላሞች ናቸው" የሚለው የአንዳንድ ግለሰቦች አባባል አሁን ላይ አይሠራም ብለዋል፡፡ ሦስት ጊዜ መጥፎ የኦዲት ግኝት ያለበት ዩኒቨርሲቲን የሚመሩ ከፍተኛ አመራሮች በሙሉ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ የሚያዝ የገንዘብ ሚኒስቴር መመሪያ መኖሩን ጠቁመዋል፡፡ ኃላፊዎቹም በህግ የሚጠየቁበት አግባብ መኖሩንም አክለዋል፡፡ ይህንን አሰራር በመከተል "ሦስት ጊዜ መጥፎ የኦዲት ግኝት ያለበት ዩኒቨርሲቲን የሚመሩ አመራሮችን በሙሉ እንቀይራለን" ሲሉ ተናግረዋል፡፡ https://t.me/Satenawmedia1
نمایش همه...
👍 1
#MinisterOfEducation ‼️ " በሚቀጠለው ዓመት ምንም አይነት አዳዲስ ፕሮጀክቶች አይኖሩም " - ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ የትምህርት ሚኒስቴር እና የ22 ዩኒቨርሲቲዎች የ2017 በጀት ዕቅዳቸው መገምገሙን ገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል። የትምህርት ሚኒስቴር፣ የሚኒስቴሩ ሁለት ተጠሪ ተቀማት፣ የ8 የምርምር እና የ14 የአፕላይድ አጠቃላይ 22 ዩኒቨርስቲዎች የ2017 በጀት እቅድ በገንዘብ ሚኒስቴር በተካሄደ የበጀት ስሚ መርሀ ግብር መገምገሙ ተነግሯል። በግምገማው ወቅት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ፤ የመንግስትን በጀት በእቅድ ለተያዘለት አላማ ብቻ በአግባቡና በቁጠባ መጠቀም ይገባል ብለዋል። አስፈጻሚ መ/ቤቶች እና የስራ ሀላፊዎች በጀትን በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ በበኩላቸው ፤ " በሚቀጠለው ዓመት ምንም አይነት አዳዲስ ፕሮጀክቶች አይኖሩም " ብለዋል። ሚኒስቴር መሰሪያ ቤቱ እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ የበጀት እቅዳቸውን በተቀመጠላቸው የበጀት ጣሪያ መሰረት አስተካክለው በጠቂት ቀናት ውስጥ ለገንዘብ ሚኒስቴር እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡ https://t.me/Satenawmedia1
نمایش همه...
#CentralEthiopia‼️ የፖሊስ ጣቢያው ዝርፊያ… በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወልቂጤ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ዝርፊያ እንደተፈጸመበት ተነግሯል፡፡ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 እንደዘገበው በፖሊስ ጣቢያው ዝረፊያ የተፈፀመው ትናንት ሰኞ ግንቦት 5/2016 ዓ.ም  ከምሽቱ 7፡40 ገደማ ነው ብሏል፡፡ በዝርፊያው ለጊዜው ተለይተው ያልታወቁ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች ከፖሊስ ጣቢያው እንደተወሰዱ የወልቂጤ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ትዕግስቱ ፉጅየ ነግረውናል ያለው ዘገባው በተጨማሪም ከጣቢያው ተዘርፎ የነበረ ፓትሮል መኪና መንገድ ላይ መገኘቱን ኃላፊዋ ነግረውናል ብሏል፡፡ በአሁን ሰዓት ፖሊስ ጣቢያው ታሽጎ የማጣራት ሂደት እየተከናወነ እንደሆነም ነው የተሰማው፡፡ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ https://t.me/Satenawmedia1
نمایش همه...
👍 3
#Sudan ‼️ በሱዳን ጥገኝነት ለጠየቁ የቀድሞ ሰላም አስከባሪዎች ጥበቃ እንደሚያደርግ የስደተኞች ተቋሙ ገለጸ! በሱዳን በጥገኝነት እየኖሩ ያሉ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ አባላት፣ ተፋላሚው የሱዳን "ፈጥኖ ደራሽ ኀይሎች"፣ በሰሞኑ መግለጫው ካቀረበው የጣልቃ ገብነት ክስ ጋራ ተያይዞ የደኅንነት ስጋት እንዳደረባቸው ገለጹ፡፡ ለደኅንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁን የትግራይ ተወላጅ የሰላም አስከባሪ አባላት፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ የሱዳን "ፈጥኖ ደራሽ ኀይሎች" ባወጣው መግለጫ፣ የህወሓት ታጣቂዎች በሱዳኑ ጦርነት እየተሳተፉ እንደኾነ ያቀረበው ክስ፣ “በመጠለያ ጣቢያዎች ያለነውን ስደተኞች ለጥቃት እንዳይዳርገን ስጋት ፈጥሮብናል፤” ብለዋል፡፡ ስለ ጉዳዩ ለአሜሪካ ድምፅ በኢሜይል አስተያየት የሰጠው የተባበሩት መግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር በበኩሉ፣ “የስደተኞቹን የደኅንነት ስጋት እረዳለኹ፤ ኹኔታውን የተመለከተ መፍትሔም እያፈላለግኹ ነው፤” ብሏል፡፡ Via:VoA https://t.me/Satenawmedia1
نمایش همه...
ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

ትክክለኛ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ! #Ethiopia #Ethiopianews #Addismereja