cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

B-POEMS

Ecclesiastes 12 (አማ) - መክብብ 1: የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፤ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ብንኖር በዚህ ቻናል ላይ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ ግጥሞች ፣ ወጎች ፣ የተለያዩ ጽሑፎች ይቀርባሉ

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
780
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-47 روز
-1730 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

نمایش همه...

👍 1
"ዮም ፍሰሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም" ዘማሪ ፍቃዱ አማረ @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
نمایش همه...
“ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም፤ በማርያም ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታ ሆነ!” (ቅዱስ ያሬድ)
نمایش همه...
1
ሉቃ 24:5 " ህያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ "ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም ። እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል!
نمایش همه...
🙏 2
Photo unavailableShow in Telegram
እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ስቅለት አደረሳችሁ
نمایش همه...
Repost from ያሬዳውያን
ሐሙስ 1.ጸሎተ ሐሙስ ይባላል፦ ጌታችን ለአይሁድ ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ ሲጸልይ በማደሩ ማቴ ፳፮፥፴፮ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል። 2.ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል። 3. የምስጢር ቀን ይባላል፡- ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምስጢር ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምስጢር ቀን ይባላል። 4. የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል፡- መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድኅነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ ሉቃ ፳፪፥፳ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል። 5. የነጻነት ሐሙስ ይባላል፡- ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነም ዮሐ ፲፭፥ ፲፭ የነጻነት ሐሙስ ይባላል። 🇪🇹👇👇👇👇👇👇🇪🇹 👉@EOTCmahlet👈                  👉@EOTCmahlet👈 👉@EOTCmahlet👈 🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹       @EOTCmahlet     #Join & share
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
+ አንዲት ዘለላ እምባ   + ቅዱሱን መጽሐፍ ለማንበብ ፈልጌ በድንገት ብገልጠው ፣ አየዋት ያቺን ሴት የጌታዬን እግር በእንባዋ ስታጥበው ፣ ምናለ እሷን ብሆን ብዬ ተመኘሁኝ ፣ ለበደሌ ጸጸት እምባንም ላጣሁኝ ፣ ወለል ብሎ ታየኝ ያጠፋሁት ጥፋት ፣ ግልጥልጥ አለልኝ የበደሌም ክፋት ፣ ከዛም በመቀጠል አንድዬ ፈጣሪን እንዲህ ስል ጠየኩት ፣ እባክህን ስጠኝ አንዲት ዘለላ እምባ ፣ ለሰራሁት ስራ ለኀጢአቴ ላምባ ፣ የበደሌን ብዛት የኀጢአቴን ክፋት በማልቀስ ልግለጸው ፣ ፍቀድልኝና ከእግርህ ወድቄ በእምባዬ ልጠበው ፣ በዛውም ይታየኝ የጥፋቴ ብዛት ፣ ደግሜ እንዳልሰራው እንዲያድርብኝ ጸጸት ፣ ከሰጠኸኝ መክሊት አንዱን እምባ አድርገው ፣ ጽድቅን አትርፌበት ነፍሴን አድኜበት ላንተው ልመልሰው ፣ ✍ ብሩክ መለሰ @orthopoems @orthopoems @orthopoems
نمایش همه...
1
Repost from ያሬዳውያን
#ዕረቡ በማቴዎስና በማርቆስ ወንጌል መሠረት በዚህ እለት ሦስት ነገሮች ተደርገዋል። 1. የካህናት አለቆች ጸሀፍትና ፈሪሳውያን በጌታ ላይ ተማክረዋል ሊያስገድሉትም ወስነዋ። 2. ጌታችን በስምኦን ዘለምጽ ቤት ተገኝቶ አንዲት ሴት(ማርያም እንተ ዕፍረት) ዋጋው የከበረ የአልባስጥሮስ ሽቱ ቀብታዋለች። 3. ይሁዳ ጌታን ለመሸጥ ወደ ጸሀፍት ካህናት ጋር በመሄድ ተዋውሏል። በአይሁድ ዘንድ 72 አባላት የነበሩት ሸንጎ ነበር። "ሲናድርየም " ይባላል።አብዛኛዎቹ ሰዱቃውያን ሲሆኑ ጥቂቶቹ ጸሀፎችና ፈሪሳውያን ነበሩ። የተሰበሰቡትና ጌታን እንዴት እንደሚይዙት የተማከሩት በካህናቱ አለቃ በቀያፋ ግቢ ነበር። በዚ ጊዜ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ የነበረው ያስቆሮቱ ይሁዳ ወደ ስብሰባው በመሄድ "ምን ትሰጡኛላችሁ እኔ አሳልፌ እሰጣችኋለሁ" በማለት ጌታን ለመሸጥ ተዋዋለ።ይህን ያደረገው በስምኦን ዘለምጽ ቤት እያሉ አንዲት ሴት ጌታን የከበረ ሽቱ ስትቀባው ለድሀ አዛኝ በመምሰል "ይህ ሽቱ ተሽጦ ለድሆች ቢሰጥ መልካም ነበር "ሲል ጌታ የልቡን መሻት አውቆ ስለተቃወመው አኩርፎ ሄዶ ተዋውሎ በ30 ብር የተስማማ። ከዛም ሊያስገድሉት ወስነዋል። እንዲሁም ሐሙስ በአል ስለነበር በአሉን አክብረው ውለው ማታ ላይ አስይዘው አርብ ጠዋት ሸንጎ ሊያቆሙት ተስማምተው ተለያዩ (ማቴ 26÷3.. ማር 14÷1-11 ሉቃ 22÷1-6) በዚህ እለት በቤተክርስቲያን የሚሰበከው ምስባክ - አንድ ሰአት መዝ 83÷5 - ሦስት ሰአት መዝ 41÷6 - ስድስት ሰአት መዝ 41÷5 - ዘጠኝ ሰአት መዝ 83÷2 - አስራ አንድ ሰአት መዝ 6÷2 © ተግባራዊ ክርስትና
نمایش همه...
👍 2