fa
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

رفتن به کانال در Telegram
916
مشترکین
+224 ساعت
+37 روز
-530 روز
آرشیو پست ها
ሰኔ 13/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በ20 ቀናት እንዲፈፀሙ ታቅደው የሚሰሩት ተግባራት አፈፃፀም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተገመገመ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በወረዳው የ20 ቀናት ዕቅድ መነሻ ያደረገ የእስካሁን የተከናወኑ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ ተካሄዷል። በመድረኩ ወቅታዊ የንቅናቄ ተግባራት የሚመሩ ተቋማት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በተለይም የፋይዳ መታወቂያ ስርጭት፣ የኢቲዮ ኮደርስ ስልጠና፣ የገጠርና የከተማ ኮሪደር ልማት ስራዎች፣ የገቢ፣ የግብርና፣ የንግድ፣ የስራ እድል ፈጠራ የእስካሁን አፈጻጸም በጥልቀት ተገምግሞ አቅጣጫዎች ተቀምጧል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን በመድረኩ እንደገለጹት በሁሉም መስክ የታቀዱ እቅዶች በቀሪ ቀናት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። በልዩነትም በግብርና ልማት፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና፣ በብሄራዊ መታወቂያ ምዝገባ፣ በአረንጓዴ ልማትና በቀሪ ስራዎች በከፍተኛ ቁርጠኝነት መፈፀም እንዳለበት አቶ ሚፈታ አክለው አመላክተዋል።    የገደባኔ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አ/ረሂም ርዳ በበኩላቸው ጠንካራ የልማት እና የለውጥ ስራዎችን በተጠናከረ መልኩ በማስቀጠል በቀጣይ ጊዜያት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ አንስተዋል። የንቅናቄ ተግባራት የሚመሩ ተቋማት የተመዘገቡ ስኬቶችን ይበልጥ በማስቀጠልና የታዩ ጉድለቶችን ፈጥኖ በማረም መሄድ እንዳለባቸው አሳስበዋል። በመድረኩ በወረዳው በ20 ቀናት ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ተግባራት ያሉበት ደረጃ፣የተመዘገቡ ውጤቶች እና የታዩ ክፍተቶች በስፋት በመገምገም በቀሪ ቀናት የተሰጡ አቅጣጫዎችን በአግባቡ በመተግበር የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ሁሉም በትኩረት እንደሚሰራ ተመላክቷል።

ሰኔ 11/ 2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በዛሬው ዕለት በይፋ መሰጠት ተጀመረ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፥ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለተከታታይ ለሁለት ቀናት የሚሰጠው የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በዛሬው ዕለት በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መልኩ መጀመሩን የወረዳው ትምህርት ጽሕፈት ቤት አክሎ አስታውቋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ ፈተናውን ባሰጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የሚሰጠው ፈተና ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ተረጋግተው ፈተናው መፈተን እንዳለባቸው ገልጸዋል። አቶ አለማየው አክለውም በዘንድሮ የ8ኛ ክፍል ፈተና ወ:730 ሴ :727 ድ 1458 እንዲሁም የግል ወ:12 ሴ:5 ድ:17 8ኛ በአጠቃላይ 1475  በ30 የፈተና ማዕከላት ፈተናው እንደሚወስዱ አስታውቀዋል። ተማሪዎች ከኩረጃ ነጻ በሆነ መልኩ በራሳቸው ተማምነው ፈተናው መፈተን እንዳለባቸው ጠቅሰው መልካም ዕድል ይሁንላችሁ ሲሉ ምኞታቸውን ተናግረዋል። በፈተናው ማስጀመሪያ መረሃ ግብር ላይ የወረዳው ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ፣የክልሉ ትምህት ቢሮ ሱፐርቫይዘር አስፋው አላቦ፣ የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ አቶ ወንድሙ ገብሬ እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት በአካል ተገኝተዋል።

ሰኔ 10/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ወረዳዊ የአመራር መድረክ እየተካሄደ ነው። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ "ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የዕለቱ የመወያያ ሰነድ እያቀረቡ ይገኛሉ። የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ የመድረኩ ዋና ዓላማ ከምርጫው በኋላ የተገኙ ውጤቶችን መገምገም፣ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን ማጠናከር፣ ያጋጠሙ ችግሮችን ለይቶ ለቀጣይ ስራችን መማሪያ ማድረግ እና በተለይም የህዝብን አገልግሎት በተሻለ ሁኔታ ለማሳካት የጋራ አቅጣጫ ማስቀመጥ መሆኑን ገልጸዋል በመድረኩ ላይ የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህጻናት ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ነጅቢያ ማህሙድ ፣የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን፣የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ ጨምሮ አጠቃላይ የወረዳው አመራሮች ተገኝተዋል።

ሰኔ 09/2018 ዓ.ም ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነጻ ቀበሌዎች በማስፋፋት ለጤና ተስማሚ አካባቢ መፍጠር እንደሚገባ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ቀቻ ቀበሌ ከአይነ-ምድር ነፃ የሆነ መንደር በመፍጠር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የምረቃ ፕሮግራም ተካሄዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አብራር እንደገለጹት በሃገር ዓቀፍ እና በወረዳ ደረጃ ጽዱ መንደር እና ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ግብ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በጤናው ዘርፍ የመንግስት ፖሊሲ በዋናነት በሽታን ቀድሞ መከላከል እና አክሞ ማዳን በመሆኑ መከላከል ማለት ከግል ጀምሮ እስከ አካባቢ ንፅህና በመሆኑ ሜዳ ላይ ከመጸዳዳት ነጻ የሆነ ቀበሌ በመፍጠር ከግል እስከ አካባቢያቸው ንጽህና መጠበቅ እንደሚገባ ገልጸዋል። በዛሬው እለት በቀቻ ቀበሌ ከአይነምድር የፀዳ መንደር መፈጠሩን መንደሩን ተዛዙረው በማየት ማረጋገጥ መቻላቸው አንስተው ይህ የተጀመረው የጽዱ መንደር ተግባር የበለጠ በማጠናከር ማስቀጠል እንደሚያስፈልግ ጠቁመው ዛሬ በቀበሌ የታየው ከአይነ ምድር የጸዳ መንደር በማረጋገጥ በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችል ስራ በመሆኑ የቀበሌው ማህበረሰብ የተጀመረው የተሻሻሉ መጸዳጃ ቤቶች ተጠቃሚነት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ለቀበሌው የእውቅና የምስክር ወረቀት በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

ሰኔ 09/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከዚህ ቀደም ታርሰው የማያውቁ መሬቶችን የማረስና ወደ ልማት የማስገባት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል!!! የደሳ ቀበሌ የመኸር እርሻ በምስል በከፊሉ:-

ቀን 08/2018 ዓም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መጎራጎር ቀበሌ በገጠር ስራ እድል ፈጠራ በተደራጁ ወጣቶች በበልግ የለማ ድንች አሁናዊ ሁኔታ በምስል:-