916
مشترکین
+224 ساعت
+37 روز
-530 روز
آرشیو پست ها
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል።
ዘንድሮ የተያዘውን የ8 ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ብሔራዊ የንቅናቄ ስራ ላይ በሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ጥሪ አቅርበዋል።
#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
ሰኔ 08/2018 ዓ/ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከዚህ ቀደም ታርሰው የማያውቁ መሬቶችን የማረስና ወደ ልማት የማስገባት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል!!!
የደነብ ቀበሌ አዲስ እርሻ በምስል በከፊሉ:-
ሰኔ 08/2018 ዓ/ም
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ማዘመን ያስችላል :- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወልቂጤ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )እንደገለጹት ልዩ ልዩ ተቋማትን ያካተተው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመን ያስችላል።
በክልሉ በተለያዩ ከተሞች ግንባታቸው የተጠናቀቁ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ለምረቃ ይበቃሉ ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።
በክልሉ 2018 በጀት ዓመት ከመጠናቀቁ በፊት ከ15 እስከ 17 መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።
በወልቂጤ ከተማ በዛሬው እለት የተመረቀው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ እንዲጀምር ድጋፍ ላደረጉ አካላት ርዕሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል።
የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እንዳሉት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከወረቀት ንክኪ እና ከብልሹ አሰራር የጸዳ አሰራር መዘርጋት ያስችላል።
የከተማዋን ገጽታ በመቀየር ረገድ የሚኖራቸው አበርክቶ ከፍተኛ ስለመሆኑም ዋና አስተዳዳሪው ጠቁመዋል።
ከተማዋን በአጭር ጊዜ ውስጥ መለወጥ የሚያስችል ስርዓት በመዘርጋት ተወዳዳሪነቷን ለማላቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አቶ ላጫ አብራርተዋል።
የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር በበኩላቸው ከተማዋ የአንድነት እና የታታሪ ህዝቦች መገኛ ነች ብለዋል።
የንግድና የኢኮኖሚ ጥንካሬ ማሳያ ከተማ ስለመሆኗም ከንቲባው አስረድተዋል።
ከለውጡ መንግስት ወዲህ የብልጽግና ተምሳሌት ከተማ ነች ያሉት ከንቲባው በከተማዋ የመሰረተ ልማት ስራዎች እየተስፋፋ መሆኑን ጠቁመዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ስኬታማ ያደርገዋል ብለዋል።
ሰኔ 08/ 2018 ዓ.ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በዛሬው ዕለት በይፋ መሰጠት ተጀመሯል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ፈተናው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን በዚህም በ31 ጣብያዎች ወንድ=945 ሴት=989 በድምሩ 1843 ተማሪዎች ፈተናውን የወስዳሉ።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፋታ ሁሴን፣የወረዳው የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አለማየው ኬኔ ፣ የማዕከላዊ ክልል ትምህርት ቢሮ ባለሙያ እንዲሁም የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!!!
በክልል አቀፍ የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች የተወዳደረው
ተማሪ ሙባረክ አ/ጀሊል በተማሪዎች ዘርፍ ከክለሉ 2ኛ
በመውጣት ተሸላሚ መሆን ችሏል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
"ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን የሳይንስ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ" በሚል መሪ ሀሳብ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ፣ የክልሉ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ከቴክኒክና ሙያ ቢሮ ጋር በመቀናጀት በቡታጅራ ከተማ ባካሄዱት 3ኛው ዙር የሳይንስና ፈጠራ ሥራዎች ውድድር
በጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የገደባኖ አንደኛ ደረጃ ት/ት ቤት ተማሪ ሙባረክ አ/ጀሊል በተማሪዎች ዘርፍ ከክልሉ 2ኛ በመውጣት የዋንጫና ሰርተፍኬት ተሸላሚ መሆን ችሏል።
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!!!
ሰኔ 06/2018 ዓ/ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ማጠቃለያ ፈተናን በስኬት እንዲጠናቀቅ ለባለድርሻ አካላት ኦረንቴሽን ሰጠ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ማጠቃለያ ፈተና ፍጹም ሰላማዊ እና ስኬታማ በሆነ መልኩ ለመምራትና ለማጠናቀቅ የሚያስችል ለባለድርሻ አካላት ኦረንቴሽን ተሰጥቷል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን በመድረኩ ተገኝተው እንዳሉት የፈተና ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ እና ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በልዩ ትኩረትና በላቀ ኃላፊነት መንፈስ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አቶ ሚፋታ አክለውም እያንዳንዱ የጣቢያ ኃላፊዎች ፣ ሱፐርቫይዘሮች እና የጸጥታ አካላት የተጣለባቸውን አገራዊና ሙያዊ ኃላፊነት በከፍተኛ ስነ-ምግባር፣ ታማኝነትና ቅንንነት መወጣት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
ተማሪዎችን በፈተና ወቅት ሊገጥማቸው የሚችሉትን ማንኛውንም ስነ-ልቦናዊና አካባቢያዊ ተፅዕኖዎች ለመቀነስ በጋራ መስራት እንደሚገባ በመግለጽ ምቹ፣ ጸጥታው የተጠበቀና የተረጋጋ የፈተና አካባቢ መፍጠር የመድረኩ ዋነኛ ዓላማ መሆኑን አቶ ሚፋታ ገልጸዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ በበኩላቸው ተማሪዎችን በውጤት ለማብቃት በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየቱን የጠቀሱት ኃላፊው ተማሪዎች የተዘጋጁበትን በሚገባ ተረጋግተው እንዲሰሩ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
እንደ ሀገር ኩረጃን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠር የትምህርት ጥራት ለማምጣት የተጀመረው ስራ እውን ለማድረግ ተማሪዎች ከኩረጃ ነጻ በሆነ መልኩ በራሳቸው ተማምነው ፈተናው ለመፈተን እንዲዘጋጁ ኃላፊው መልዕክት አስተላልፏል።
ከሰኔ 8 እስከ 9 የሚሰጠው ክልል አቀፍ የሚንስትሪ ፈተና የሚወስዱ የ6ኛ ክፍል ወ:945 ሴ :898 በድምሩ 1843 ፣ከሰኔ 11/12/2018 ዓ.ም የሚሰጠው የ8ኛ ክፍል ደግሞ ወ:730 ሴ :727 ድ 1458 እንዲሁም የግል ወ:12 ሴ:5 ድ:17 8ኛ በአጠቃላይ 1475 ተማሪዎች ዝግጁ መሆናቸውን አንስተው በ30 የፈተና ማዕከላት ፈተናው እንደሚሰጥ አመላክተዋል።
በሁሉም ትምህርት ቤቶች ለሚገኙ ተማሪዎች የስነ-ልቦና ግንባታ በመስጠት፣በአቀላለም እና በሌሎችም በፈተና አወሳሰድ ሂደት ላይ የሚስተዋሉ ጉድለቶችን በማረም የተሻለ ውጤት እንዲገኝ መስራት እንደሚገባም ተመላክቷል።
በመድረኩ የትምህርት አመራሮች ፣ ባለሙያዎች፣ የፈተና ጣቢያ ሱፐርቫይዘሮች፣ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራንና የጸጥታ አካላት ተገኝተዋል።
ሰኔ 02/2018 ዓ/ም
እንኳን ደስ አላችሁ!!
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በ1ኛ ደረጃ ተማሪዎች የፈጠራ ስራ ከዞኑ ካሉ የከተማና የወረዳ መዋቅሮች 1ኛ በመውጣት የሜዳሊያ ተሸላሚ መሆን ችሏል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያና የጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ በጋራ ባዘጋጁት "ሳይንስ ይመራናል ቴክኖሎጂ ያስቀድመናል" በሚል መሪ ቃል የተከበረው 5ዙር የሳይንስና የፈጠራ ስራ ኤግዚቢሽን ላይ የገ/ጉ/ወ/ወረዳ በ1ኛ ደረጃ ተማሪዎች ዘርፍ ተሸላሚ ሆኗል።
በዚህም በ1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የተማሪዎች ውድድር የወረዳችን የፈጠራ ስራ ፈርጥ የሆነው የገደባኖ አንደኛ ደረጃ ት/ት ቤት ተማሪ ሙባረክ አ/ጀሊል በአጠቃላይ በጉራጌ ዞን ወረዳና ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች በመወዳደር 1ኛ ደረጃ በመውጣት አሸናፊ ሆኗል።
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!!
