fa
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

رفتن به کانال در Telegram
1 067
مشترکین
+424 ساعت
-27 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
አዋጁ ለወጣቶች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ ---------------------------- (ዜና ፓርላማ) ሐምሌ 10፣ 2017 ዓ.ም፤ የስታርታፕ አዋጅ ለወጣቶችና ታዳጊዎች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊና የቴክኖሎጂ እድገት ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የኢፌድሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገልጸዋል። ይህ የተገለጸው ምክር ቤቱ ባካሄደው 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ ሲሆን፣ የሃገርን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማጎልበት እና ለወጣቱ ከፍተኛ የስራ ዕድል ከመፍጠር አኳያ አዳዲስ የሀብት ምንጭ የሆኑ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤቶችን ለማበረታታት አዋጁ እንደሚያግዝ አባላቱ ተናግረዋል። የስታርታፕ ፕሮግራም የተለያዩ የአስፈጻሚ ተቋማት፣ የፋይናንስ ድርጅቶችን እንዲሁም ባለሀብቶችን በማጣመርና በማስተሳሰር ምቹ የሆነ የኢኮኖሚ ስነ-ምህዳር መፍጠር የሚያስችል እንደሆነም አባላቱ ተናግረዋል፡፡ በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ረቂቅ አዋጁን ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ የተደገፈ የስታርታፕ ውጤት በሂደት ትላልቅ ኢንዱስትሪዎችንና ኩባንያዎችን በማፍራት ለኢኮኖሚ ዕድገትና ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አብራርተዋል። ሰብሳቢው ስታርታፕ ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የኢኮኖሚ ዕድገትና ልማትን ለማፋጠን ቁልፍ ሚና ያለውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንድትሆን የሚያስችል ነው ብለዋል ። አዋጁ ምቹ የስታርታፕ ምህዳርን በመገንባት ስታርታፖችን ውጤታማና ስኬታማ በማድረግ፤ ስታርታፖች እና የስታርታፕ ምህዳር ገንቢዎችን ዒላማ ያደረገ የተቀናጀ ድጋፍ መስጠት የሚያስችል የተሳለጠ የስያሜ፣ የዕውቅና እና የአቅም ግንባታ አተገባበር ሥርዓት በመዘርጋት ቀጣይነት ያለው የቴክኖሎጂና የኢኮኖሚ እምርታን እንደሚያረጋግጥ ተናግረዋል። ስታርታፖችን እና የስፓርታፕ ምህዳር ገንቢዎች የሚያጋጥማቸውን የፋይናንስ አቅርቦት ተግዳሮቶች እና የፋይናንስ ስጋትን በዘላቂነት ለመቅረፍ የግራንት ፕሮግራም፣ የብድር ዋስትና ማዕቀፍ እና የፈንዶች ፈንድ መዋቅር ማደራጀት የሚያስችል አዋጅ እንደሆነም ሰብሳቢው ገልጸዋል። ምክር ቤቱም አዋጁን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል፡፡ ©️ HPR

#የቴክኒክና_ሙያ_ትምህርትና_ሥልጠና_ዘርፍ_እና_የተከናወኑ_ተግባራት ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ማለት በሀገሪቱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ መሠረት በማንኛውም የሙያ ዘርፍ ደረጃቸው ከከፍተኛ ትምህርት በታች በሆኑ መደበኛ ወይም መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሚሰጥ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና እንዲሁም የሙያ ትምህርትና ብቃት ምዘና ሥርዓት ሲሆን መደበኛ ባልሆነ መልኩ የተገኘ የሙያ ብቃት ሥርዓትን ይጨምራል። (በሚኒስትሮች ም/ቤት ደንብ ቁጥር 515/2014 አንቀጽ2 ንዑስ አንቀጽ 4) #የማንኛው_የቴክኒክና_ሙያ ትምህርትና_ስልጠና_ፕሮግራም_የፈቃድ_ማመልከቻ_መገምገሚያ_መስፈርቶች ፡- -የሙያ ደረጃዎች ፤ -ስርዓተ ትምህርትን፣ -የአሰልጣኞች ብቃትን፤ -የማሰልጠኛ እቃዎችን፤ -የስልጠና መሳሪያዎችን፤ እና -ቁሳቁሶችንና የመረጃ መሳሪያዎችን አስመልክቶ የተቀመጡትን ዝቅተኛ መለኪያዎችን የሚያሟላ መሆን ይኖርበታል፡፡ የኢፊዲሪ የትምህርት እና ስልጠና ባለሥልጣን ይህን አሟልተው ለተገኙት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የስልጠና ኘሮግራሙን መጀመር የሚያስችላቸውን አስፈላጊውን ፈቃድ ይሰጣቸዋል፡፡ #ማንኛውም_ፈቃድ_የሚጠይቅ_የቴክኒክና_ሙያ _ትምህርትና_ስልጠና _ተቋም_በዝቅተኛ_ደረጃ_ማሟላት_ያለበት_ስታንዳርዶች፡- -የተቋሙ አመራር እና አደረጃጀት፤ -አስተዳደራዊ ሰነዶች፣ መመሪያዎችና ተሟልተው መያዝ ያለባቸው ደንቦች እና ደጋፊ ሰነዶች፤ -የማሰልጠኛ ተቋማት ሕንፃዎች ከባቢያዊ ሁኔታና የቦታ ስፋት መለኪያዎች፤ -የስርዓተ ትምህርት መስፈርቶች፤ -የሰው ሀብት፤ -የመማሪያ ክፍሎች ስፋትና ተፈላጊ ቁሳቁሶች፤ -ቢሮዎችና የተቋሙ ፊዚካል ግብዓቶች፤ -የሰርቶ ማሳያ ክፍሎች ስፋት እና ግብአቶች (ላብራቶሪዎች፣ ዴሞንስትሪሽን፣ ወርክ ሾፖች እና ኮምፒውተር ማዕከል)፤ -የቤተ-መጻሕፍት ስፋትና ይዘት፤ -የተማሪ ቅበላና ሬጂስትራር፤ -የጥራት ማረጋገጥ ስርዓት፤ -የጥናት እና ምርምር፤ የፕሮጀክት ኢንዳስትሪያል ኤክስቴንሽን እና የማህበረሰብ አገልግሎት እና -የፈቃድ ዕድሳት መገምገሚያ መስፈርቶች ናቸው፡፡ #እስከአሁን_በቴክኒክ_እና_ሙያ_ስልጠና_ሥራ_ዘርፍ_የተከናወኑ_ተግባራት -በፌደራል መንግስት ለሚቋቋሙ እና ከፌደራል መንግስት በጀት ለሚመደብላቸው የቴክኒክ እና ሙያ ተቋሟት ፈቃድ እና የፈቃድ እድሳት መስጠት፤ -የውጭ ሀገር ዜግነት ባላቸው ለሚከፈቱ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ፈቃድ እና የፈቃድ እድሳት መስጠት፤ -ለበጎ አድራጎት የተቋቋሙ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ፈቃድ እና የፈቃድ እድሳት መስጠት፤ -የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማትን ለመገምግም የሚያስችል ስታንዳርድ ማዘጋጀት፤ -ሁሉንም የሙያ ደረጃዎች ከስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በማምጣት በባለሙያዎች እንዲታዩ ማድረግ፤ -የመውጫ ቅጾችን (Exit formats) ማዘጋጀት እና በየጊዜው ክለሳ ማድረግ፤ -የውጭ ገምጋሚ ባለሙያዎች (አሰሰርስ) የገመገሙትን ተቋማን አጠቃላይ እይታ የሚይሳፍሩበትን ቅጽ ማዘጋጀት፤ -ተቋማት የቴክኒክ እና ሙያን በተመለከት ሙያዊ ምክር ፈልገው ሲመጡ የምክር አገልግሎት መስጠት እና -ለባለስልጣኑ ተጠሪ የሆኑ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ዘግተው ሲወጡ ህጋዊ ሂደቱን ጠብቀው እንዲወጡ ምክር መስጠት ናቸው። የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተከናውነዋል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በራስ ፀጋ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ገለጹ። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግስት እና በፓርቲ ትብብር የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚገመግም መድረክ በድሬደዋ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህን ጨምሮ የብልፅግና ፓርቲ ዋና መስሪያ ቤት እና የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አመራሮች፣ ሚኒስትሮች እና የየክልሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። ከተረጅነት የመውጣት ጥረት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ፣የገበያ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን በመቀነስ ረገድና ሌሎች ጉዳዮችን በመዳሰስ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና የተመዘገቡ ውጤቶችን በተመለከተ በስፋት ውይይት ተደርጓል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፤ ለዜጎች በውጭና ሀገር ውስጥ የስራ እድል በማመቻቸትና በመፍጠር ረገድ የተሳካ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። በኢትዮጵያ ክህሎት መር የስራ ዕድል ፈጠራ እንዲኖር በማድረግ ዜጎች በቀሰሙት ዕውቀትና ክህሎት ለሀገር ከፍታና ብልፅግና መረጋገጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ከስራ እድል ፈጠራም ባለፈ በሌሎች ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተው፥ በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል። በብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)፥ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በፓርቲና በመንግስት ትብብር የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን አንስተዋል። በመሆኑም የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል በተያዘው በጀት ዓመትም የላቀ አፈፃፀም እንዲኖር የተቀናጀ ጥረት ይደረጋል ብለዋል። የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረግ የሀገሪቷን ዘርፈ ብዙ ልማትና እድገት ማሳለጥ መቻሉን አንስተዋል። የኑሮ ውድነትን በማረጋጋት ረገድ በስፋት ጥረት መደረጉንም ተናግረዋል። ©️ ኢዜአ

አረንጓዴ አሻራ ! ለትዉልድ የሚተላለፍ ታሪካዊ አሻራ !

የውጭ ሃገር የሥራ ዕድል... በሥራና ክህሎት ሚንስቴር የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት በሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም አስጠብቆ በማሰማራት ትልቅ ስኬት መመዝገቡ ይታወቃል። አሁንም ህጋዊ የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት በሰለጠነ የሰው ሃይል በተለያዩ የሞያ ዘርፎች በቁጥር ከፍተኛ የሆነ የሰው ሃይል ይፈለጋል። በመሆኑም ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የሞያ ዘርፎች መሰማራት የምትፈልጉ በሙሉ ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ፎርሙን ሞልታችሁ የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ስንል እናሳውቃለን። Driving & Transportation 1. Light Vehicle Driver 2. Heavy Vehicle Driver (e.g., Grader Operator) 3. House Driver 4. Trolley Operator Security & Safety 5. Security Guard 6. CCTV Surveillance Operator 7. Office Security Personnel 8. Plumber 9. Electrician 10. HVAC Technician 11. AC Technician 12. Pumper Domestic & Facility Services 13. Housekeeper 14. House Maid 15. House Cleaner 16. Housekeeping Supervisor 17. Houseman 18. Caretaker 19. Steward 20. Laundry Attendant 21. Bellman Hospitality & Food Services 22. Receptionist 23. Waiter/Waitress 24. Barista 25. Sous Chef 26. Pastry Chef / Dessert Chef 27. Garde Manger Chef 28. Arabica Cuisine Chef 29. Kitchen Assistant 30. Private Cook 31. Room Attendant 32. Hotel Assistant Manager Healthcare & Caregiving 33. Nurse 34. Junior Nurse 35. Home Care Nurse 36. Private Nurse 37. Junior Midwife / Clinical Nurse 38. Elderly Care Assistant 39. Live-in Support Assistant 40. Neonatal Intensive Care Unit (NICU) Nurse 41. Junior Physiotherapist Childcare Services 42. Babysitter 43. Childcare Worker Beauty & Salon Services 44. Hairdresser 45. Hairstylist 46. Beauty Therapist 47. Salon Manager 48. Nail Technician 49. Nail Art Instructor 50. Massage Therapist 51. Makeup Artist Agriculture & Farming 52. Indoor Farmer 53. General Farm Worker Administrative & Marketing 54. Junior Administrative Assistant 55. Junior Marketing Assistant 56. Junior Account Manager 57. Sales Representative 58. Purchaser Skilled Labor 59. Construction Worker 60. Laborer 61. Tailor 62. Storekeeper 63. Supervisor Retail & Customer Services 64. Cashier 65. Promoter https://forms.gle/TF5BcYBtrhwkyjR59 መልካም ዕድል! የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

#የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ የምስጋና መልዕክት የ12 ክፍል የመልቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ እና በተለያዩ የመፈተኛ ጣቢያዎች ከሰኔ 23 2017 ዓ .ም ጀምሮ ሲሰጥ ቆይቷል። የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም ፈተናዎቹን የማስፈተን እና የማስተባበር ተልዕኮ በመውሰድ ሀገራዊ ግዴታውን በአግባቡ በመወጣት ላይ ይገኛል። በዚሁ መሰረት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ 4 ተከታታይ ዙሮች ከ1,150 በላይ ተፈታኞችን ተቀብሎ ሃገር አቀፍ መመሪያን መሰረት አድርጎ ላለፉት ሁለት ሳምንታት ሀገራዊ የመልቀቂያ ፈተናውን ያለምንም ችግር መስጠት ችሏል። ፈተናው ያለምንም ችግር በተለይ የበይነ መረብ online ተፈታኞች የኢንተርኔት መቆራረጥ፣ የኮምፒተር እክል እና መሰል ችግሮች እንዳይኖር ሁሉንም የፈተና ክፍሎች እንዲሁም ሙሉ ተቋሙን በCCTV ካሜራ በታገዘ የቁጥጥር ስርአትን በማዘጋጀት ችግሮች እንዳይከሰቱ በማሰብ ቀደም ተብሎ የተለያዩ ስራዎችን ሰርቷል። ተማሪዎች ፈተናው ከመሰጠቱ ቀደም ብሎ ልምምድ እንዲያደርጉ እንዲሁም የሞዴል ፈተና እንዲፈተኑ በማድረግ በፈተና ወቅት የሚፈጠርን ችግርን ማስቀረት ተችሏል። ይህ ሀገራዊ የመልቀቂያ ፈተናው በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ጉልህ ሚና ለነበራችሁ የICT መምህራን ፣ ለኮሌጁ ሠራተኞችና ማኔጅመንት አባላት፣ለፈተና አስተባባሪዎች ፣ ፈታኞች ፣ በሰላምና ፀጥታ ላይ ለሠራችሁ የፌደራል ፖሊስ አባላት ፣ ለኮሌጁ የጥበቃ ሠራተኞች እንዲሁም ለኢትዮ ቴሌኮምና መብራት ሃይል ከፍተኛ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። በተለይ ተፈታኝ ተማሪዎች ኮሌጁ ለሚከተለው ጥብቅ ዲሲፕሊን ተገዢ በመሆን እንዲሁም መመሪያን በተገቢው ሁኔታ ተግባራዊ በማድረግ ላሳያችሁት ትብብር በራሴ እና በኮሌጁ ስም ምስጋናዬን እያቀረብኩ የፈተና ውጤታችሁ ያማረ እንዲሆን መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ ብለዋል። በመጨረሻም ኮሌጅ በየ አመቱ በሚያዘጋጀው "ክረምትን በክህሎት" በሚል መሪ ቃል የክረምት ልዩ ስልጠና በተለያዩ የስልጠና መስኮች ለ12 ኛ ክፍል ተፈታኞች ያዘጋጀ ስለሆነ በዚህ ልዩ የስልጠና መርሃ ግብር ላይ ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡ የ ኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሀምሌ 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

መጪውን ዘመን የዋጀ አመራር ማፍራት ወሳኝ መሆኑ ተመላከተ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ያዘጋጀው የ2017 ዓመታዊ የእቅድ አፈጻጸም እና የ2018 የእቅድ ውይይት መድረክ ላይ የአመራሩ የማስፈጸም አቅም የሚያጎለብቱ የተለያዩ ስልጠናዎች እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ያለውን ፋይዳ ታሳቢ ያደረገ፣ መጪውን ዘመን የዋጀ አመራር ማፍራት ላይ ያተኮረ ስልጠና በዘርፉ የካበተ ልምድ ባላቸው አሰልጣኞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡ በመድረኩ ወቅቱ የሚፈልገውንና መጪውን ዘመን የዋጀ አመራር ማፍራት ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ በዘርፉ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት በትላንት እና በዛሬ ያልተወሰነ፣ መጪውን ጊዜ ገምቶ፣ ዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታ ተገንዝቦና ስትራቴጂ ነድፎ መጪውን ጊዜ አስቦ የሚሰራ አመራር ለማፍራት በትኩረት መሰራት እንዳለበት በመድረኩ ላይ ተመላክቷል፡፡ በስልጠናው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የተጠሪ ቋማት የሥራ ኃላፊዎች፣ የክልልና የከተማ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊዎችና ምክትል ኃላፊዎች፣ የሙያ ብቃት ማዕከላት ኃላፊዎች፣ የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲኖች እና የባለድርሻና አጋር አካላት ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛል፡፡ ስልጠናውን ተከትሎ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ፣ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ይካሄዳል፡፡ ©️ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር - ኢትዮጵያ

በኮሌጁ ባለፉት ሳምንታት በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ ሲካሄድ የቆየው ምልከታ ተጠናቀቀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ የአፈፃፀም ትግበራን በተመለከተ ሲያካሂድ የቆየውን የግምገማ መድረክ በዛሬው እለት አጠናቋል:: በምልከታ መርሃ-ግብሩ መሰረት የተቀሩ ዲፓርትመንቶችን (ማኑፋክቸሪንግ ፣ኮንስትራክሽን፣ድራፍቲንግና ሰርቬይ እንዲሁም የሆቴልና ቱሪዝም) ዲፓርትመንቶችን የአፈፃፀም ሪፖርት የተመለከተ ሲሆን በዚህም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በ2017 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን ከተቀመጠው ግብ አንፃር ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት መመልከትም ተችሏል:: የኮሌጁ ማኔጅመንት ከትምህርትና ስልጠና ክፍሎች በተጨማሪም የኮሌጁን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደትን አመታዊ ሪፖርት ተገኝቶ የተመለከተ ሲሆን በዚህም በበጀት አመቱ የተሰሩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም በኢንተርፕራይዞችና ኢንዱስትሪዎች ላይ የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትን በዋናነት ተመልክተዋል:: ምልከታ በተካሄደባቸው ክፍሎች የቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግም በማኔጅመንት አባላት ግብረ መልሶች የተሰጡ ሲሆን በተጨማሪም በኮሌጁ ዲን የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ለትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በመስጠት የምልከታ መድረኩ ተጠናቋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሐምሌ 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ