1 088
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+227 روز
+1330 روز
آرشیو پست ها
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሴት አመራሮችና ሰራተኞች ዘንድሮ በዓለም ለ133ኛ በሃገራችን ለ48 ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው ዓለማቀፉ የሴቶች ቀንን "ሴቶችን እናብቃ፤ ልማትና ሰላምን እናረጋግጥ!" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ-ግብሮች አከበሩ፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን በዓሉን ስናከብር የሴቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በመስራት ሊሆን ይገባል ብላዋል፡፡
የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው የሴቶችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነትና ተሳታፊነት ለማሳደግ በርካታ ስራዎች በመሰራት ላይ መሆኑን ጠቅሰው የሴቶችን ቀን በዓመት 1 ቀን ከማክበር ባሻገር የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነታቸውን በማረጋገጥ መሆን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በበዓሉ አከባበር ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን፣ ም/አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ከሪማ አሊ እንዲሁም የአስተዳደሩ የፉይናስና ኢኮኖሚ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሙሉካ መሀመድ የተገኙ ሲሆን ልምድና ተሞክሯቸውን በሰፊው ለታዳሚዎች አካፍለዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ለንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር ተወዳዳሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፤
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በ2016 ዓ.ም ለሚደረገው ብሩህ የንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር መወዳደር የሚፈልጉ እንዲመዘገቡ በማስታወቂያ አሳውቆ መመዝገቡ ይታወሳል በዚህም ከተለያዩ ዘርፎች የተመረጡ ዳኞችን በመያዝ ለውድድሩ የሚያስፈልጉ መመሪያዎችን እና አሰራሮችን በማዘጋጀት በቀጣይም የተወዳዳሪዎችን ሰነድ በመመርመር ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያልፉትን በመለየት ስልጠና ሰጥቷል፤
ውድድሩ የሀሳብ ስለሆነ ተወዳዳሪዎች ከሀሳብ ደረጃ ወጥተው ዕውን የሚያደርጉበትን ብቃት እንዲያገኙ ድጋፍ የሚደረግላቸው ሲሆን ድጋፉም ማሰልጠን፣ መሸለምና ማብቃት በሚል ሶስት ደረጃዎችን ያልፋል፤ በመሆኑም በዋናነት በየዘርፉ የሚታዩ ዋና ዋና ተግዳሮቶችን መቅረፍ ላይ ያተኮሩ አዳዲስ የንግድ ፈጠራ ሀሳቦችን ማመንጨት የሚችሉበትን እና የአካባቢያቸውን ጸጋዎች ለይተው በፈጠራ ሀሳብ በመደገፍ ጥቅም ላይ ማዋልን እንዲያዳብሩ ስልጠናው መሰጠቱን የስራ ዕድል ፈጠራ ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ ቤተልሔም ድንበሩ ተናግረዋል፡፡
በዚህም የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እንደተናገሩት ድሬዳዋ የኢንደስትሪ እና የንግድ ኮሪደር እንደመሆኗ መጠን ይህንን ታሳቢ ያደረጉ ሃሳቦች እንደሚበረታቱ ጠቅሰው ውድድሩ ተወዳዳሪዎች ከሀሳብ ደረጃ ወጥተው ዕውን የሚያደርጉበትን ብቃት እንዲያገኙ ድጋፍ የሚያገኙበትን ሁኔታ የሚያመቻች በመሆኑ አሸናፊ የሚሆኑ በቀጣይ ከአስተዳደሩ ጀምሮ እስከ ፌደራል ድረስ በመሸለምና በማብቃት ሂደት ውስጥ የሚበረታቱ እንደሚሆን ገልጸዋል፤
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ለንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር ተወዳዳሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፤
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በ2016 ዓ.ም ለሚደረገው ብሩህ የንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር መወዳደር የሚፈልጉ እንዲመዘገቡ በማስታወቂያ አሳውቆ መመዝገቡ ይታወሳል በዚህም ከተለያዩ ዘርፎች የተመረጡ ዳኞችን በመያዝ ለውድድሩ የሚያስፈልጉ መመሪያዎችን እና አሰራሮችን በማዘጋጀት በቀጣይም የተወዳዳሪዎችን ሰነድ በመመርመር ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያልፉትን በመለየት ስልጠና ሰጥቷል፤
በዚህም ውድድሩ የሀሳብ ስለሆነ ተወዳዳሪዎች ከሀሳብ ደረጃ ወጥተው ዕውን የሚያደርጉበትን ብቃት እንዲያገኙ ድጋፍ የሚደረግላቸው ሲሆን ድጋፉም ማሰልጠን፣ መሸለምና ማብቃት በሚል ሶስት ደረጃዎችን ያልፋል፤ በመሆኑም በዋናነት በየዘርፉ የሚታዩ ዋና ዋና ተግዳሮቶችን መቅረፍ ላይ ያተኮሩ አዳዲስ የንግድ ፈጠራ ሀሳቦችን ማመንጨት የሚችሉበትን እና የአካባቢያቸውን ጸጋዎች ለይተው በፈጠራ ሀሳብ በመደገፍ ጥቅም ላይ ማዋልን እንዲያዳብሩ ስልጠናው መሰጠቱን የስራ ዕድል ፈጠራ ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ ቤተልሔም ድንበሩ ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from N/a
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባለፋት ቀናት በስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎች ላይ ሲያካሂደው የቆየውን የ2016 ዓ.ም የመጀመርያ 6ወር አፈፃፀም ድጋፍና ክትትል ግብረ መልስና ማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ አካሄደ::
በግብረ መልስ አሰጣጥ መድረኩ ላይ ድጋፍና ክትትል ሲደረግባቸው የነበሩ ዋና ስራ ሂደቶች እና ስራ ክፍሎች የተገኙ ሲሆን በዲን ፅ/ቤት የሚመራው የድግፍና ክትትል ቡድንም ትግበራውን በማጠናቀቅና ግብረ መልሶችን በማዘጋጀት የተቋሙ ፑል አመራር አባላት በተገኙበት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለተሳታፊዎች ቀርቧል::
በመድረኩ በቀረበው ማጠቃለያ ግብረ መልስም ዋና ስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎች በድጋፍና ክትትል ወቅት ከተሰጣቸው ተልዕኮ አንፃር የታዩባቸውን ክፍተቶችና ጥሩ ተመኩሮዎች በዝርዝር በማስቀመጥ ግብረ መልስ መስጠት ተችሏል::
በተጨማሪም በሪፖርት መልክ ከተሰጠው ግብረ መልስ በተጨመማሪ ለሁሉም ስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎች በተደረገው ድጋፍና ክትትል መሰረት የፅሁፍ ግብረ መልስ የተሰጣቸው ሲሆን በዚህም የታዩ ክፍተቶችን በቀጣይ አፅኖት ሰተው ለመተግበር እንደ መነሻ ይሆናልም ተብሏል::
በመጨረሻም በተቋሙ ካሉት የስራ ሂደቶችና ክፍሎች በክትትልና ድጋፍ ወቅት በአንፃራዊነት ልቆ የተገኘው የ አይ.ሲ.ቲ ትምህርትና ስልጠና ክፍል በመድረኩ ለሌሎች የስራ ሂደቶችና ክፍሎች ተሞክሮውን እንዲያክፍል የተደረገ ሲሆን ይህም የስራ ክፍሎቹ በቀጣይ የነበሩ ውስንነቶችን በመቅረፍ እንደ ተቋም ለሚመዘገው ውጤት ጉልህ አስተዋፇ እንዲያበረክቱ እንደሚያግዝም ታምኖበታል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
የካቲት 27/2016 ዓ.ም
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በAUDA NEPAD እና EU የገንዘብ ድጋፍ እየተተገበረ የሚገኘው የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የግማሽ ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ከየካቲት 25-26/2016 በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ሚዛን አማን ተከናወነ፡፡
የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ፣ከድሬዳዋ እና ከሚዛን አማን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች እንዲሁም ከSIFA ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የተውጣጡ የSIFA ተወካዮችና የስራ ሀላፊዎች ከየካቲት 25-26/2016 በሚዛን አማን፣ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የተከናወነ ሲሆን በእለቱም የመስክ የስራ ጉብኝት ተደርጓል ፡፡
የካቲት 26/2016 ዓ.ም
ሚዛን አማን
ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያ ሴቶች ማህበር ለድሬዳዋ ቅርንጫፍ አባላት በህይወት ክህሎት ዙሪያ ያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬው እለት መሰጠት ተጀመረ፡፡
በስልጠናው ላይ በመገኘት ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲንም/ አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንደ ገለጹት እንደሚታወቀው ሃገራችን ኢትዮጵያ አሁን ላለችብት እድገት እንዲሁም ቀጣይ ለምትደርስበት የእድገት ደረጃ ለመድረስ የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነዉ። ስለዚህ ሴቶችን በማብቃትና አካታች እቅዶችን ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡
ለዚህም ደግሞ ኮሌጃችን ጠንከሮ እየሳራ ይገኛል በዚህም መሰረት ደግሞ በከተማችን እንዲሁም በምስራቁ የሃገራችን ክፍል የሚገኙ ሴት የመገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎችን በህይወት ክህሎት ዙሪያ የተዘጋጁ ስልጠናዎችን በማዘጋጀትና በመስጠት ሴቶችን ወደ አመራር ለማምጣት እድል ልንሰጥ ይገባል ብለዋል፡፡
በስልጠናው ላይ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያ ሴቶች ማህበር ከድሬዳዋ ቅርንጫፍ አባላት የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሞያዎች የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናው ለ3ቀን የሚቆይ ይሆናል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
የካቲት 26/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት በተለያየ ዘርፍ ስር ለሚገኙ አሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት አሰሪና ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156/2011 እና በሙያ ደህንነትና ጤንነት ላይ ስልጠና ተሰጠ።
በቢሮው የውጭ አገር ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት በዋናነት የሰራተኛውን ደህንነትና ጤንነት የማስጠበቅ ስራዎች ትኩረት የተሰጣቸው ሲሆኑ ይህም የኢንዱስትሪውን ምርታማነት በማሳደግ የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የሚጫወተው ሚና ቀላል አይደለም።
በተጨማሪም በተለይ በአሰሪና ሰራተኞች መካከል የሚፈጠረውን አለመግባባት በመቀነስ እንዲሁም የኢንደስትሪውን ሰላም እንዲሁም ደህንነትና ጤንነት ለማስጠበቅ መሰል ስልጠናዎች ያላቸው ፋይዳ ከፍ ያለ መሆኑንና በተጨባጭም ውጤት እሚያስገኙ እንደሆነ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 25/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
”ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት” በሁለተኛው ዙር ሥራ ፈላጊ ወጣቶችን ወደ ትግበራ ለማስገባትእንዲያስችል ለመልማይ እና ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተዘጋጀ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በዚህ ዓመት ቀበሌዎች ለሚተገበረው ”ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት” ውስጥ መሳተፍ ያለባቸውን ወጣት የሆኑ ነዋሪዎችን በመምረጥ በኩል የተጣለባቸውን ሃላፊነት በአግባበቡ መወጣት እንደሚገባቸው ከየቀበሌው ለተመረጡ መልማይና ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች ገለጻ ተደርጓል፡፡
በመጀመሪያው ዙር ”ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት” ተግባራዊ ተደርጎ እንደ አስተዳደር የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል ከተጠቃሚዎች ምልመላ ጀምሮ የታዩ የአሰራር ክትተቶችን በማሻሻል ወደ ምዝገባ መገባቱ ይታወቃል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 25/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ላይ የሚሰሩ የውጭ አገር ዜግነት ያላቸው ሰራተኞች ህጋዊነት የሚያረጋግጥ የቁጥጥር ስራ መሰራቱ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት በአዋጅ በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት በአስተዳደሩ በሚገኙ ኢንደስትሪዎችና የግል ድርጅቶች ውስጥ በተለያዩ የሥራ መደብ ላይ ተቀጥረው የሚሠሩ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ቁጥጥር አደረገ።
የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፉን የሚመሩት አቶ መሀመድ ኢብራሂም ዜጎች ወደ ውጭ አገራት በመሄድ የመስራት መብት እንዳላቸው ሁሉ የውጭ አገራት ዜጎችም ወደ አገራችን በመምጣት በተለያዩ የሥራ መስኮች ላይ የመሥራት መብት እንዳላቸውና ሲሰሩ ሀገሪቱ ባጸደቀቻቸው የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 መሠረት ተገቢውን ፎርማሊቲ እንዲያሟሉ የሚጠበቅ(የሚገደዱ) መሆኑን ገልጸዋል፤
በዚህም መሰረት በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ህጉን ተከትለው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ማረጋገጥ ዋና አላማው ያደረገው ይህ ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1156/2011 በአግባቡ ተፈጻሚነት፤ ወቅቱን ጠብቆ የታደሰ የመኖሪያ ፈቃድ መኖሩን፤ የፓስፖርት እና የስራ ፈቃድ እንዳላቸው፤ ለአገራችን ዜጎች በተገቢ መልኩ የእውቀት ሽግግር እያደረጉ መሆኑን እንዲሁም በሚሰሩበት ክልል/አስተዳደር ላይ የሥራ ግብር እየከፈሉ መሆኑን የማረጋገጥ ስራ ተሰርቷል፡፡
የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ መሀመድ ኢብራሂም አክለው በቁጥጥር ሂደቱ ህጉን መሰረት ያላደረጉ አተገባበሮችና የታዩ ክፍተቶችን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የመፍትሔ አቅጣጫ በማስቀመጥ እልባት እንዲያገኙ ማስቻል እና አስተዳደራችን ለውጭ አገር ዜጎች ምቹና ተመራጭ የሥራ ቦታ እንዲሆን መደላድል የሚፈጥር እንደሚሆን ተናግረዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 22/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
