1 088
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+227 روز
+1330 روز
آرشیو پست ها
በድሬዳዋ አስተዳደር የሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጁ ጉብኝት አደረጉ።
መጋቢት 10 2016 ዓ.ም
በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ቀደም ሲል ከተለያዩ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጋር በተደረሰው የጋራ መገባባትና በተዘጋጀው የጋራ ዕቅድ መሰረት በዛሬው እለት የሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቴክኖሎጂ ክበብ አባል ተማሪዎችን በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና እና በሂሳብ ማለትም(STEM) ግንዛቤ ለማስጨበጥ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንዲጎብኙ ተደጏል፡፡
በዚህም ተማሪዎቹ በኮሌጁ የተግባር ስልጠና የሚሰጥባችውን ዲፓርትመንቶች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በሰልጠና ክፍሎች የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራንም ለጉብኝት ለመጡት ተማሪዎቹ የተግባር ስልጠና የሚስጥበትን ክፍሎች(workshops) በማስጎብኘት እንዲሁም በየዲፖርትመንቱ ስለሚሰጡ ሙያዎች በቂ ማብራሪያ እንዲያገኙ አስችለዋል::
በተጨማሪም ተማሪዎቹ በኮሌጁ ዲኖች ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ተጨማሪ ግንዛቤ ማስጨበጫ ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን ተማሪዎቹም በኮሌጁ የተፈጠረላቸውን ግንዛቤ እንደ ቴክኖሎጂ ክበብ በሚማሩበት ት/ቤት ለሚገኙ ሌሎች ተማሪዎችም ግንዛቤ እንዲፈጥሩ ሃላፊነት ወስደው ጉብኝታቸውን አጠናቀዋል፡፡
ድሬዳዋ
መጋቢት 10/2016
የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን
በኢፌዴሪ የስራ ክህሎት ሚኒስተር ክብርት ሙፈሪያት ከሚል የተመራ ልኡካን ቡድን ለስራ ጉብኝት ድሬዳዋ ገቡ
በኢፌዴሪ የስራ ክህሎት ሚኒስተር ክብርት ሙፈሪያት ከሚል የተመራ ልኡካን ቡድን በጠዋቱ መንግስታዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ እንዲሁም ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ ልኡክ ቡድኑ ድሬዳዋ ገብተዋል።
ድሬዳዋ አለምአቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱም የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ ቤት ሀላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍን ጨምሮ በካቢኔ አባላትና በፓርቲ ከፍተኛ የስራ አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
በአሁኑ ሰአትም በድሬዳዋ አስተዳደር የተከናወኑ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የልማት፣ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች ላይ ውይይት እያካሄዱ ይገኛል።
ልኡክ ቡድኑ ለ 10 ተከታታይ ቀናትን የሚቆይ እንደሆነም ከወዲሁ ታውቋል።
©️ የድሬዳዋ መንግስት ኮምንኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
2ኛ ዙር ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የወረዳዎች የምዝገባ አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ።
የፕሮግራሙ ተሳታፊ ወጣቶች በኮቦ የመረጃ ስርአት ምዝገባ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን ምዝገባው ከየካቲት 26/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት በ 11 የከተማ ወረዳ አንድ ማዕከላት እየተከናወነ ይገኛል፡፡
በዛሬው ዕለት ያለፉት 8 የምዝገባ ቀናት አፈጻጸም እና በቀሪ ቀናት በምዝገባ ወቅት ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ሂደቶች ላይ 11 የአንድ ማዕከል ማስተባበሪ ባለሙያዎች እና አስተባባሪዎች በተገኙበት ተገግሟል፡፡
በውይይቱ ለምዝገባ ቅድመ ዝግጅት የተከናወኑ ተግባራት፤ የወረዳዎች የምዝገባ አፈጻጸም እና የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ ከድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በኩል ቀርቧል፡፡
በማስከተል ከውይይቱ ተሳታፊዎች ጥያቄዎች ቀርበው ምላሽ የተሰጠ ሲሆን በመጨረሻም በቀጣይ ቀናት ምዝገባውን በጥብቅ ዲሲፕሊን በዕረፍት ቀናትም ጭምር በማከናወን ዕቅዱን ማሳካት ትኩረት ተሰጥቶታል።
በተጨማሪ ዝቀተኛ አፈጻጸም ያላቸውን ወረዳዎች የተጠናከረ ድጋፍ ከቢሮ በማድረግ እንዲሁም በተሰጠው ጊዜ ገደብ ሰልጣኞችን ማቅረብ ባልቻሉ ወረዳዎች ምትክ ከሌሎች ወረዳዎች ወጣቶችን ወደ ፕሮግራሙ ማቀላቀል የሚቻልበት ሁኔታ ከወዲሁ እንዲመቻች የሥራ መመሪያ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በመስጠት የምዝገባ አፈጻጸም የግምገማ ውይይት ተጠናቋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት በቢሮው የሚመለከታቸውን ባለሙያዎችን፤ ሞዴል የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችን እና የቀበሌ አንድ ማዕከል ባለሞያዎችን በመያዝ በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ የሚገኙ የኢንተርፕራይዝ ልማት ሥራዎችን የልምድ ልውውጥ አካሄደ።
በልምድ ልውውጡም በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችን ተሞክሮ መመልከት የተቻለ ሲሆን በተለይም ያላቸውን ሀብት የመጠቀምና የስራ ተነሳሽነታቸው፤ የገበያ ትስስር የተፈጠረበት እና የቦታ ምችችት በማድረግ ረገድ በተለይም ከአስተዳደሩ በተደረገ ድጋፍ የተለያዩ ሼዶችን በክላስተር መዘጋጀቱን መመልከት ተችሏል።
በዚህም በልምድ ልውውጡ የተሳተፉ ሞዴል የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች በተመለከቱት ነገር ጥሩ መነቃቃት የፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸው በቀጣይ የሚሰሩት ስራ ላይ ተጨማሪ እሴት እንዲጨምሩ የሚያስችላቸው እንደሆነ ገልጸዋል በመጨረሻም መልካም አቀባበል ላደረጉልን የአስተዳደሩ የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች ምስጋና አቅርበዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (E-LMIS) ላይ ለአገር ውስጥና ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ግንዛቤ መፍጠር የሚያስችል መድረክ ተካሄደ።
በአገር አቀፍ ደረጃ የሥራ ዕድል ፈጠራውን የተሳለጠ ለማድረግ የሚረዳ ዲጂታል ስርአት ተዘርግቶ ወደ ሥራ መገባቱ የሚታወቅ ሲሆን ለአገር ውስጥ ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ያለውን ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ለማስገንዘብ መድረኩ ተዘጋጅቷል።
በዚህም ሀያ አንድ ለሚሆኑ ኤጀንሲዎች ስለ አዲሱ ሥርዓት (E-LMIS) ምንነትና እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ አቅም መፍጠር መቻሉን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 4/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የሠላም ፥ የፍቅር ፥ የአንድነት ፥ የመተዛዘን ፥ የመደጋገፍ ፥ የይቅርታ ፥ የፈውስ እና የጽድቅ ጾም ይሁንልን!
Sooma nagaa, jaalala, tokkummaa, araara, gargaarsa, dhiifama, fayyina, fi qajeelummaa nuuf haa ta'u!
Waxaan idiin rajaynayaa in bisha barakaysan idiin noqoto mid badhaadhe, farxad, jacayl iyo nabad galyo wadata oo la idin ka aqbalo soonka!
‘’ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ’’ ኘሮጀክት እንደ መጀመሪያው ዙር ሁሉ በ2016 ዓ.ም በተመሳሳይ ወደ አንድ ሺ ለሚጠጉ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራ አጥ የሆኑ ወጣቶች ቋሚ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በምዝገባ ላይ ይገኛል፡፡
በአስተዳደሩ የምትገኙ ዕድሜያችሁ ከ18 እስከ 25፤ የትምህርት ደረጃችሁ 12ኛ ክፍል ያጠናቀቃችሁ እና ከዚያ በታች፤ ምንም አይነት ስራ የሌላችሁ እና በፕሮጀክቱ አሰራር ለመመራት ፍቃደኛ የሆኑ ከየካቲት 26/2016 እስከ መጋቢት 06/2016 በቀበሌ አንድ ማዕከላት በአካል በመገኘት እንዲመዘገቡ ቢሮው ጥሪ እናስተላልፏል።
በዚህም የአስተዳደሩ ወጣቶች ወደ ቀበሌ አንድ ማዕከላት በመሄድ እየተመዘገቡ የሚገኝ ሲሆን መስፈርቱን የምታሟሉ ቀሪ የምዝገባ ቀናት ጥቂቶች በመሆናቸው እንዲሁም ቀድመው ለሚመዘገቡ በሚመርጡት ሙያ የሥራ ላይ ልምምድ የሚያደርጉበትን ዕድል የሚፈጥርላቸው መሆኑን የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 30/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚብሽን(Job fair) ዝግጅት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ምክክር ተደረገ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ይህን የምክክር መድረክ ሲያዘጋጅ የሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚብሽኖች አሰሪውና ስራ ፈላጊው በአንድ ቦታ የሚገናኙበትና ሥራ ፈላጊው አሰሪው ላቀረበው ክፍት የሥራ ቦታ የሚያመለክትበት ቀጣሪው ቃለመጠይቅ የሚያደርግበትን መድረክ ውጤታማነት ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡
በዚህ የምክክር መድረክ ላይ ተሳታፊ የሆኑ ባለድርሻ አካላት በአጠቃላይ ሥራ ፈላጊውና (job seekers) እና ቀጣሪዎች (Employers) በቀላሉ መገናኘት እንዲችሉ መንግሥት ከሚሰጣቸው የስራ ስምሪት አገልግሎቶች መካከል ሥራና ሰራተኛ ማገናኘት ኤግዚብሽን (Job fair) ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በማስተካከልና በመናበብ ሊሰሩ በሚችሉበት አግባብ ላይ በሰፊው ተወያይተዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 29/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ለቴክኖሎጂና የፈጠራ ስራ ተወዳዳሪዎች ስልጠና ሰጠ፡፡
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ በዋነኛነት የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራኖች፣ ሰልጣኝ ተማሪዎች፣ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም የአጠቃላይ ትምህርት መምህራንና ተማሪዎች ክፍተታቸው በመለየት የፈለጉትን ቴክኖሎጂ ለመቅዳት/ኮፒ ለማድረግ እንዲችሉ ያለባቸውን ክፍተት ለመሙላት የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መስጠት ተችሏል፡፡
በዚህም በ2016 ዓ.ም ለሚደረገው የቴክኖሎጂና የፈጠራ ስራ ውድድር ላይ የውድድር ተነሳሽነት በመፍጠር ቴክኖሎጂ የመቅዳት አቅምን ማሳደግ፤ አሰልጣኞች፣ ሰልጣኞች፣ ኢንተርፕራይዞች፣ መምህራንና ተማሪዎች ቴክኖሎጂን በመቅዳት ለአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ዕድገት የተሻለ አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ማስቻልና ቴክኖሎጂ በመቅዳት ሂደት ውስጥ የውድድር መንፈስ መፍጠርና በቴክኖሎጂው ዙሪያ ዓለም አቀፋዊ እውቀትና እውቅና እንዲያገኙና የሚያደርግ ይሆናል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 29/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
The Sustainable Employment through Entrepreneurship and Enterprise Development (SEED) ፕሮግራም ላይ ለድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ለሚመለከታቸው ሰራተኞች ገለጻ ተደረገ፡፡
ፕሮግራሙ በኢንትርፕሪነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት መሪነት በማስተርካርድ ፋውንዴሽን የገንዘብ ድጋፍ ከድርጅቶች ጥምረት (ኦርቢት ኢኖቬሽን ሃብ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ፣ የአሜሪካ የቴክኖሎጂ ኮሌጅ እና ተስፋ ኢንተርፕራይዝ ) ጋር በመተባበር የ5 አመት ፕሮግራም ነው፡፡
ይህም ፕሮግራም በድሬዳዋ አስተዳደር ሁለት ኮሌጆች ማለትም አንድ የመንግስት እና አንድ የግል ኮሌጆች ተመርጠው ወደ ትግበራ መግባት የሚያስችላቸውን የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሚገኙ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡
በዚህም በቢሮው የሚመለከታቸውና አካላት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆችን በማጎልበት ለውጥ አምጭ የንግድ ሞዴሎችን በማስተዋወቅ፣ የንግድ መፈልፈያ ማዕከላትን በማቋቋምና ወደ ስራ በማስገባት እንዲሁም ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ ልማቶችን በማጎልበት የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራን ለመደገፍ የሚያስችለውን ፕሮግራም በሚገባ እንዲረዱት ያስቻለ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
