fa
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

رفتن به کانال در Telegram
1 064
مشترکین
-224 ساعت
-77 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
ባለብዙ ተሰጥኦው የድሬው ወጣት ክፍል 1 https://youtube.com/watch?v=qhHKBVvgjYE&feature=shared

በኮሌጁ ሰልጥነው ስልጠናቸውን የሚያጠናቅቁ ሰልጣኞች ኢንዱስትሪውን እንዲያንቀሳቅሱ ብቻ ሳይሆን የራሳቸውን ስራ ፈጥረው ኢኮኖሚው ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ የሚያደርጉ ሰልጣኞችን እያፈራ እንዳለ ገለጸ፡፡ #ዜና|የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከEDI ጋር በመተባበር ስልጠና ለሚያጠናቅቁ ሰልጣኞች የስራ ፈጣሪነት ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ጀመረ፡፡ ቴክኒክና ሙያ ማለት ለመቀጠር ዝግጁ የሚሆኑ ሰልጣኞችን ብቻ የሚያፈራ ሳይሆን የራሳቸውን ስራ ፈጥረው ለሌሎችም የስራ እድል መፍጠር የሚችሉ ወጣቶች የሚፈሩበት ትልቅ ተቋም ነው ያሉት በስልጠናው ማስጀመሪያ እለት በመገኘት ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ ም/ዲኗ አያይዘውም በኮሌጁ ሰልጥነው ስልጠናቸውን የሚያጠናቅቁ ሰልጣኞች ኢንዱስትሪውን እንዲያንቀሳቅሱ ብቻ ሳይሆን የራሳቸውን ስራ ፈጥረው ኢኮኖሚው ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ የሚያደርጉ ሰልጣኞችን እያፈራ ያለ ትልቅ ኮሌጅ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም ይህን ስልጠና የወሰዳችሁ ሰልጣኞች በቀጣይ ጊዜያችሁ የራሳችሁን ስራ እንዴት እንደምትፈጥሩ ግንዛቤ የሚፈጥርላችሁ ስልጠና ነው፡፡ስልዚህ ስልጠናውን በአግባቡ እንድትከታተሉ አሳስባለሁ ብለዋል፡፡ በመጨረሻም በተለያዩ ሙያ እየሰለጠናችሁ እንደመሆኑ መጠን ኮሌጁ በሚያዘጋጃቸው እንዲሁም የተለያዩ አለማቀፍ ተቋማት በሚያዘጋጁት የተለያዩ የስራ ፈጠራ ውድድሮች ላይ እየተሳተፋችሁ በማሸነፍ የራሳችሁን ስራ የምትፈጥሩበትን የገንዘብ ድጋፍ እንድታገኙ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል፡፡ ይህ በዛሬው እለት የተጀመረው ስልጠና ከEntrepreneurship Development Institute(EDI) በመጡ አሰልጣኞች እንዲሁም በኮሌጁ በሚገኙ ብቁ አሰልጣኞች አማካኝነት እየተሰጠ ያለ ሲሆን በቀጣይም መሰል ስልጠናዎች ለኮሌጁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በየጊዜው እንደሚዘጋጅም ለማወቅ ተችሏል:: የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 4/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ ለወቅታዊ ትኩስ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃ You tube: Dire Dawa Polytechnic College(DDPTC) Facebook: https://web.facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/Dire Dawa Polytechnic College TikTok: tiktok.com/@diredawapolytechnicollege Facebook (https://web.facebook.com/Dire)

የፅሁፍ ፈተና ጥሪ!! ከዚህ ቀደም የኢትዮዽያ አየር መንገድ ባወጣው የስራ ማስታወቂያ የተወዳደራችሁ በሙሉ ለፅሁፍ ፈተና ያለፋችሁ ስም ዝርዝር ከዚህ በታች በተቀመጠው መሰረት ቅዳሜ ህዳር 6/2018
+2
የፅሁፍ ፈተና ጥሪ!! ከዚህ ቀደም የኢትዮዽያ አየር መንገድ ባወጣው የስራ ማስታወቂያ የተወዳደራችሁ በሙሉ ለፅሁፍ ፈተና ያለፋችሁ ስም ዝርዝር ከዚህ በታች በተቀመጠው መሰረት ቅዳሜ ህዳር 6/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ላይ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እንድትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን። መረጃውን ሼር በማድረግ ይተባበሩ

በአስተዳደሩ የተጀመረው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ቀጥሎ እየተካሄደ መሆኑ ተገለጸ፤ በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ በሁለቱ የመንግስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች አዲስ በተከለሰው የሙያ ደረጃና የሆልስቲክ ምዘና አሰጣጥ ስርዓት የሙያ ምዘና በመውሰድ ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል። በዚህም ከኮሌጆቹ የተወጣጡ የኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና Practical እና Knowledge Test በመውሰድ ላይ የሚገኙ ሲሆን በቀጣይም በሌሎች ዲፓርትመንቶች ያልተመዘኑ አሰልጣኝ መምህራን በተመሳሳይ የሚመዘኑ መሆኑን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኃላፊ እና የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 3/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በገጠር የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተደራሽነትን ለማሳደግ ከዋሂል ወረዳ እና ቀበሌ ወጣቶች ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት አካሄደ። የውይይት መድረኩ ዋሂል ገጠር ወረዳ የተውጣጡ ሴቶችና ወጣቶችን ተሳታፊዎች ያደረገ ሲሆን በዋናነት የአስተዳደሩ የገጠር ወረዳዎች በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተደራሽነታቸውን በማሳደግ ፍትሃዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የታለመ ነው። በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ እና የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ስልጠና ም/ዲን አቶ አብዱልፈታህ አፈንዲ በሰፊው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጠቀሜታን ለወጣቶቹ ያብራሩ ሲሆን በመደበኛ እና በአጫጭር የስልጠና አማራጭ ያሉ እድሎችን በዝርዝር አስረድተዋል፡፡ ቢሮው ባለፉት አመታት በአስተዳደሩ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን አከናውኖ ብዙ ውጤት መገኘቱን ጠቅሰው፤ በ2018 የአስተዳደሩን ገጠር አካባቢ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በክህሎት ልማት ዘርፍ ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ጋር ማለትም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ጋር አቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ የገጠር ወጣቶች በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጆች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ ፍትሃዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚደረገውን እንቅስቃሴን ለማነቃቃት በክህሎት ልማት ዙሪያ በዋሂል ወረዳ ያካሄደው የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት በተቀሩት ሶስቱ ወረዳዎች ላይ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 3/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በብልጽግና ፓርቲ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት የወጣቶች ክንፍ በፓርቲው የወጣቶች ክንፍ የወጣቶች ክንፍ ምስረታ፣ የዕቅድ ኦረንቴሽንና ፕሮግራም ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄዱ፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 3/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በብልጽግና ፓርቲ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት የወጣቶች ክንፍ በፓርቲው የወጣቶች ክንፍ የወጣቶች ክንፍ ምስረታ፣ የዕቅድ ኦረንቴሽንና ፕሮግራም ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄዱ፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 3/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

Save The Children የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር ስራ ፈላጊ የሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረጉ ተገለጸ። በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እንደገለጹት ከግብረሰናይ ድርጅቱ ጋር በመሆን  ከአስተዳደሩ አራት ወረዳዎች የተወጣጡ ስራ ፈላጊዎችን በልዩ ልዩ ሙያዎች በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እንዲሰለጥኑ መደረጉን ተናግረዋል። አቶ ሰኢድ አክለው ግብረሰናይ ድርጅቱ ለስራ ፈላጊዎቹ ተደራጅተውም ይሁን በግል ለሚሰሯቸው ስራዎች የመነሻ ካፒታል ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸው ቢሮውም የገበያ ትስስር እንዲኖራቸው  ሁኔታዎችን ያመቻቻል ብለዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 30/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ሶስተኛ ዙር ትግበራ ስድስተኛ ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ተካሄደ። በዚህም የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ወጣቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና ወስደው በስራ ላይ ልምምድ የገጠሟቸው ገጠመኞች ላይ በመወያየት እርስ በእርስ አቅም የሚገነባቡበት የመጨረሻ መድረክ ተፈጥሮላቸዋል። በአቻ ለአቻ ውይይቱ ላይ ወጣቶቹ በተለያዩ ተቋማት ከወዲሁ ቅጥር ተፈጽሞላቸው ተጠቃሚነታቸው ከጠበቁት በላይ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን የመጨረሻ ዙር በመሆኑም ለቢሮ እና ለአንድ ማዕከል አመራሮችና ባለሙያዎች የስራ አቅጣጫ ተሰጥቷል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የ2018 ዓ.ም በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የአዲስ ሰልጣኝ ቅበላና ምደባን በሚመለከት ከወረዳ ም/ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር ውይይት ተካሂዷል ፡፡ በአመራር እርከን የወረዳ አስፈጻሚዎች ለህብረተሰቡ ቅርብ በመሆናቸው ስለቴክኒክና ሙያ ስልጠና በማህበረሰቡ ውስጥ የቆየውን ሰፊ የተባዛ የግንዘቤ ችግር በመቅረፍ ወጣቱ ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት በመምጣት ሰልጥኖ ራሱንና ማህበረሰቡን የሚጠቅም ዜጋ እንዲሆን ትልቅ ሥራ መስራት እንደሚገባ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ በውይይቱ ላይ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደተናገሩት ቢሮው የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ተደራሽነቱን ለማስፋት ከተለያዩ አደረጃጀቶች ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ገልጸው አንድ ማዕከላትም በየወረዳው ዘርፉን ከማስተዋወቅ አንጻር ጉልህ ሚና ይጫወታሉ ብለዋል።  የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ገጽታ ግንባታ በተናጠል ውጤት ሊያስገኝ ስለማይችል በተለይም ከሰፊው የማህበረሰብ ክፍል ጋር በአገልግሎት መስጠት የሚገናኘው ይህ አካል የቴክኒክና ሙያ አምባሳደር ሆነው በአጫጭር ስልጠናው በቅንጅት በመስራት የተገኘው ውጤት በመደበኛውም ለመድገም መግባባት መፈጠሩን በቢሮው የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን ገልጸዋል፡፡ በውይይቱም የ2018 ዓ.ም የስልጠና ዘመን የመደበኛና አጫጭር ገበያ ተኮር ስልጠና ዕቅድ ቀርቦ ገለጻ የተደረገ ሲሆን የነበሩ የተዛቡ የግንዛቤ ችግሮችን ደረጃ በደረጃ በመቅረፍ ሰፊውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተብራርቷል፡፡ በተለይም የአስተዳደሩ ወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚ በሚሆኑበት አግባብ አመራሩ በስፋት ሊሰራበት እንደሚገባ መግባባት የተደረሰ ሲሆን በዘርፉ የሚገጥሙ ችግሮችን በየጊዜው በጥናት በመለየት የሥራውን ዓለም የሰው ሃይል ፍላጎትና አቅርቦት ለማጣጣም የተሰራ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ የሰው ሃይል የገበያ ፍላጎት የዳሰሳ ጥናት ውጤት ቀርቧል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በብልጽግና ፓርቲ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት የሴቶች ክንፍ በፓርቲው የሴቶች ክንፍ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ውይይት አካሄዱ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ