1 088
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+227 روز
+1330 روز
آرشیو پست ها
በድሬዳዋ አስተዳደር በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ለኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን፣ ሰልጣኞችና ኢንተርፕራይዞች በተከለሰው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ፖሊሲ ትግበራ ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በዚህም የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆችና ኢንተርፕራይዞች ለፖሊሲው ተግባራዊነትና ለአጠቃላይ ሃገራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር ተግባብተው ይሰሩ ዘንድ ለማስቻል ሃገራዊ የሳይንስ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅ ፖሊሲ፣ ሃገራዊ የኢኖቬሽን ስርዓት ምንነትና የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የ10 ዓመት እቅድ፣ የቴክኖሎጅ ልማትና ሽግግር ሂደት፣ የአእምሮ ንብረት ምንነትና አጠባበቅ እንዲሁም ቴክኖሎጅ መር ስራ ፈጠራ የሚሉ አንኳር ጉዳዮች ላይ መስጠት ተችሏል፡፡
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩን አስመልክቶ በዳይሬክቶሬቱ የቴክኖሎጂ ሽግግር ባለሙያ የሆኑት አቶ ሽመልስ ፍሰሃ እንደተናገሩት የዚህ ስልጠና ዓላማም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት እና ኢንተርፕራይዞች መንግስት ለኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ እድገት የሰጠውን ትኩረት ተገንዝበውና አፈጻጸሙን ተረድተው በዛው ልክ ለሃገራዊ የኢኮኖሚ ሽግግሩ ጉልህ ድርሻቸውን ይወጡ ዘንድ መነቃቃትን መፍጠርና የመፈጸም አቅምን ለማጎልበት መሆኑን ገልጸዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 3/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለሚገኙ ዋና ስራ ሂደቶችና ክፍሎች የ2016 ዓ.ም ሁለተኛ ሩብ ዓመት የድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብር በማካሄድ ላይ ይገኛል::
የድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብሩን እያደረገ የሚገኘው በኮሌጁ ዲን የሚመራ የድጋፍና ክትትል ቡድን ሲሆን በድጋፍና ክትትሉ ወቅትም ስራ ሂደቶችና ክፍሎች በበጀት አመቱ የእቅድ አፈፃፀም ግምገማና ሪፖርት፣ በመረጃ እደረጃት፣ በQMS አተገባበር ያሉበት ደረጃ፣ በስራ አካባቢ ያላቸው የካይዘን አተገባበር እንዲሁም በግብአት አጠቃቀም ያሉበትን ቁመና የሚገመግም ሲሆን በተጨማሪም ስራ ሂደቶችና ክፍሎች እንደየስራ ባህርያቸው መፈፀም ከሚገባቸው ተግባራት ምን ያህሉን ተግባራዊ አድርገዋል ሚለው ላይም ያተኮረ የድጋፍና ክትትል መሆኑ ተገልጿል::
የድጋፍና ክትትል ቡድኑ በድጋፍና ክትትሉ ወቅት ለስራ ሂደቶችና ክፍሎች በቃል ግብረ መልስ የሚሰጥ ሲሆን የድጋፍና ክትትሉ ማብቂያ ላይም ለሁሉም በፅሁፍ ግበረ መልስ የሚሰጥም ይሆናል::
የዚህ ድጋፍና ክትትል ዋና አላማ በተቋሙ የሚገኙ ስራ ሂደቶችና ክፍሎች በአፈፃፀም ጉድለት የሚታይባቸውን ተግባራቶች ለይቶ ትኩረት እንዲሰጣቸው የማድረግና የተሻለ አፈፃፀም ለታየባቸው ስራ ሂደቶችና ክፍሎች ደግሞ ለሌሎች ተሞክሮ እንዲሆኑ በማለም ሲሆን በቀጣይም ድጋፍና ክትትሉ በቀሩት ስራ ሂደቶችና ክፍሎችም የሚቀጥል ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
የካቲት 2/2016 ዓ.ም
የከተማ እና የገጠር የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎችን ወደ አንድ በማምጣት አቅምን በተደራጀና ወጥነት ባለው መልኩ ለመምራት የሚያስችል አቅጣጫ ተቀምጦ ወደ ተግባር መገባቱ ተገለጸ፤
በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ የከተማና የገጠር ነዋሪዎችን ሁሉአቀፍ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል ከዚሁ ጋር በተያያዘ በሥራ እድል ፈጠራው ዘርፍ ያለውን ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው የክላስተር አመራሮች ጋር በቀጣይ ወደ አንድ በማምጣት የሚመራበት ሁኔታና አቅጣጫ ላይ ውይይት ተደረገ ሲሆን የሥራ ዕድል ፈጠራ እድሎችን ለሁሉም እኩል ተደራሽ የማድረግ ሥራ ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል።
በአስተዳደሩ የአራቱም ገጠር ክላስተሮች ምክትል ሥራ አስፈፃሚዎችና የገጠርና ከተማ የሥራ እድል ፈጠራ ቡድን መሪዎች እንዲሁም የቢሮው አመራሮች በተገኙበት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በመወያየትና በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር በአንድ ላይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብና ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር ለማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ ተችለዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 30/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from N/a
Witness of Christ Church ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ::
የስልጠና ድጋፉ የተሰጠው ለኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፖርትመንት አሰልጣኝ መምህራን ሲሆን የስልጠናው ይዘትም በResidential and Commercial Electrical Systems in USA Standard ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልፅጿል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥር 30/2016 ዓ.ም
Repost from N/a
አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በአጫጭር ስልጠና እያሰለጠናቸው ለሚገኙ ሰልጣኞች በተግባር የተደግፈ የስራ ላይ ልምምድ ስልጠና ሰጠ::
አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በSolar PV Instalation ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ለሚገኙትን 47 ሰልጣኞች
በ > Apply Principles of renewable energy Operation.
> Read and Interpret Plans and Specifications.
> Install DC/AC Wiring Systems
in conduit and Conneet Equipment.
> Determine and sizing of PV system.
> Perform Site Assessment.
Unit of Competency ላይ ሰልጣኞቹን በኦሲስ ኦርፋን ቻሪቲ ለ 2 ቀን የቆይ በተግባር የተደግፈ የስራ ላይ ልምምድ ስልጠና ተሰጥቷል::
ሰልጣኞቹ በንድፈ ሀሳብ ሲከተታተሉ የቆዩትን ስልጠና ስራ ቦታው ላይ በአካል ተገኝተው በተግባር የሰለጠኑ ሲሆን ይህም ሰልጣኞቹ በቀጣይ ወደስራ አለም ሲገቡ በእጅጉ እንደሚያግዛቸው ተገልጿል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥር 30/2016 ዓ.ም
The Sustainable Employment through Entrepreneurship and Enterprise Development (SEED) ፕሮግራም በኢንትርፕሪነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት መሪነት ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን እና ከድርጅቶች ጥምረት ( ኦርቢት ኢኖቬሽን ሃብ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ፣ የአሜሪካ የቴክኖሎጂ ኮሌጅ እና ተስፋ ኢንተርፕራይዝ ) ጋር በመተባበር የሚሰራ የ5 አመት ፕሮግራም በድሬዳዋ አስተዳደር ወደ ስራ ለመግባት ቅድመ ዝግጅቱን ጀመረ፤
ይህም ፕሮግራም እንደ ኢትዮጵያ ለአንድ ሚሊዮን ወጣቶች እና ሴቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ይፈልጋል፡፡ አንድ መቶ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆችን በማጎልበት ለውጥ አምጭ የንግድ ሞዴሎችን በማስተዋወቅ፣ የንግድ መፈልፈያ ማዕከላትን በማቋቋምና ወደ ስራ በማስገባት እንዲሁም ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ ልማቶችን በማጎልበት የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራን ለመደገፍ በማለም የሚተገበር እንደሆነ በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ በተካሄደው የማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ገልጸዋል።
የፕሮግራሙ የኮምንኬሽንና የማህበረሰብ ልማት ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ ሳሚናስ በላይነህ እንደተናገሩት ፕሮግራሙ አራት ዋና ዋና ትኩረቶች የሚኖሩት ሲሆን እነዚህም፡-
i) አንድ መቶ የቴ/ሙ/ት/ስ ኮሌጆችን በማጎልበት ወደ አንድ ሚሊዮን ወጣቶችን መጥቀም፤
ii) በሙያ እና በኢንተርፕራይዝ ልማት የወጣቶችን የስራ እድል ማሳደግ፤
iii) የፋይናንስ እና የገበያ ትስስር ፈጠራን ማመቻቸት፤
iv) ለሥራ ፈጠራ እና ለኢንተርፕራይዝ ልማት አመቺ አካባቢን መፍጠር ላይ በትኩረት አቅጣጫ ተይዘው ወደ ተግባር የሚገባ ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማረፊያና ማረሚያ ቤት ጋር ለታራሚዎች በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዙሪያ ከስልጠና እስከ ስልጠና ማዕከል አቅም ግንባታ መፍጠር የሚያስችል የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረመ።
የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ከማረሚያ ቤቱ ጋር የተደረገው ስምምነት ኮሌጁ ያለበትን ያለበትን ማህበራዊ ኃላፊነት ከመወጣት ያለፈ በማረሚያ ቤቱ የሚገኙ ታራሚዎች የበቁ ሞያተኞችን ለማፍራት የሚደረገውን ጥረት ሁሉአቀፍ በሆነ ድጋፍና በጥምረት የመስራት የሁለትዮሽ መግባባት የፈጠረው ነው ብለዋል።
በስምምነት ፊርማው ላይ የማረሚያ ቤቱ ሀላፊ ረ/ኮሚሽነር ወንድሙ ደበላ እንደተናገሩት ስምምነቱ ማረሚያ ቤቱ ለታራሚዎች የሚሠጠዉን ስልጠና ከማጠናከር ባለፈ ታራሚዎች ታንፀዉ እንዲወጡ የአንድ አካል ሚና ብቻውን ውጤት ስለማያመጣ ኮከሌጁ ጋር የተደረገው ስምምነትና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በመጨረሻም በማረሚያ ቤቱ እየተሰጠ የሚገኘውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ያግዝ ዘንድ አጠቃላይ የገንዘብ ግምታቸው ስድስት መቶ ዘጠና አምስት ሺህ ሶስት መቶ ብር የሚያወጡ ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለአውቶሞቲቭ እና ለፈርኒቸር ስልጠናዎች የሚያገለግሉ የተለያዩ የስልጠና ማቴሪያሎችና ማሽኖችን ድጋፍ ማድረግ ተችሏል፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥር 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማረፊያና ማረሚያ ቤት ጋር ለታራሚዎች በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዙሪያ ከስልጠና እስከ ስልጠና ማዕከል አቅም ግንባታ መፍጠር የሚያስችል የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረመ።
የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ከማረሚያ ቤቱ ጋር የተደረገው ስምምነት ኮሌጁ ያለበትን ያለበትን ማህበራዊ ኃላፊነት ከመወጣት ያለፈ በማረሚያ ቤቱ የሚገኙ ታራሚዎች የበቁ ሞያተኞችን ለማፍራት የሚደረገውን ጥረት ሁሉአቀፍ በሆነ ድጋፍና በጥምረት የመስራት የሁለትዮሽ መግባባት የፈጠረው ነው ብለዋል።
በስምምነት ፊርማው ላይ የማረሚያ ቤቱ ሀላፊ ረ/ኮሚሽነር ወንድሙ ደበላ እንደተናገሩት ስምምነቱ ማረሚያ ቤቱ ለታራሚዎች የሚሠጠዉን ስልጠና ከማጠናከር ባለፈ ታራሚዎች ታንፀዉ እንዲወጡ የአንድ አካል ሚና ብቻውን ውጤት ስለማያመጣ ኮከሌጁ ጋር የተደረገው ስምምነትና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በመጨረሻም በማረሚያ ቤቱ እየተሰጠ የሚገኘውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ያግዝ ዘንድ አጠቃላይ የገንዘብ ግምታቸው ስድስት መቶ ዘጠና አምስት ሺህ ሶስት መቶ ብር የሚያወጡ ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለአውቶሞቲቭ እና ለፈርኒቸር ስልጠናዎች የሚያገለግሉ የተለያዩ የስልጠና ማቴሪያሎችና ማሽኖችን ድጋፍ ማድረግ ተችሏል፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥር 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
‹‹የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ ተማሪዎችን በመቀበል እና አሰልጥኖ በማብቃትና በማስመረቅ ለቀጠናው ትስስር ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።››
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
****
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሶማሊ ላንድ የመጡ ከ10 በላይ ሰልጣኞችን በኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽንና በፍሪጅ ጥገና እንዲሁም በICT ዘርፍ የሰለጠኑ ሰልጣኞችን በዛሬው እለት አስመረቀ፡፡
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት እና ለሰልጣኞች ሰርተፊኬት የሰጡት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲሆኑ በንግግራቸውም በቅድሚያ ለዛሬ የምርቃት ቀን የደረሳችሁ ሰልጣኖች ለድሬዳዋ ከተማችን አባሳደር ናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ አያይዘውም ትምህርት እና ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ እድገት ቁልፍ መሳሪያ ነው። ይህን መሳርያ ደግሞ ለከተማችን ወጣቶች ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካ ወጣቶችም ማድረስ ይኖርብናል፡፡
ለዚህም በዛሬው እለት በኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽንና በፍሪጅ ጥገና እንዲሁም በICT ዘርፍ ለተከታታይ 20 ቀናት ያክ ስልጠናቸውን የተከታተሉ የሶማሊ ላንድ ዜግነት ያላቸው ወጣቶች አንዱ ማሳያው ናቸው ብለዋል፡፡ ኃላፊው በማስቀጠል የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ ተማሪዎችን በመቀበል እና አሰልጥኖ በማብቃት ለቀጠናው ትስስር ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። በቀጣይም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች የተለያዩ ሰልጣኞችን በመቀበል የምስራቅ አፍሪካን በትምህርትና ስልጠናው የማዋሃድ ስራን የሚሰራ ይሆናል፡፡ በመጨረሻም አንድላይ ከሆንን ብዙ ነገሮችን ማሳካት ስለምንችል በህብረት መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጎረቤት ሀገራት ሶማሌላንድ፣ ጅቡቲ፣ከኬንያ፣ከታንዛንያ እንዲሁም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ጋር በትምህርትና ስልጠና ለማዋሃድ በንቃት ሲሰራ መቆየቱ የሚታወስ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በዛሬው እለት ስልጠናችሁን አጠናቃችሁ ለምርቃት የበቃችሁ የሶማሊ ላንድ ሰልጣኝ ተማሪዎች ለዚህ ውህደት ማሳያ ናችሁ ብለዋል፡፡ከዚህ ኮሌጅ ስልጠናችሁን ጨርሳችሁ ወደ ሀገራችሁ ስትሄዱ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያገኛችሁትን ስልጠና ሌሎች ወጣቶች እንዲያገኙ የአባሳደርነት ሚናችሁን እንድትወጡ አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከዚህ ቀደም ከ18 በላይ የምስራቅ አፍሪካ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ማሰልጠኑና ለምርቃት ማብቃቱ የሚታወስ ሲሆን የአሁኑ ስልጠና ለሁለተኛ ጊዜ የሚደረግና አብዛኛው ስራ ማለትም የምግብ፣የመኝታ ወጪን ኮሌጁ ሸፍኖ ማሰልጠኑ ይታወሳል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 28/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
