fa
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

رفتن به کانال در Telegram
1 071
مشترکین
+224 ساعت
+37 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
🌍ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት፣ ለሁለንተናዊ ተጠቃሚነት🌍 የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት የዜጎችን መብትደህንነትና ተጠቃሚነት ባረጋገጠ መልኩ ተግባረዊ እየተደረገነው፡፡ በዚህም ባለፉት ሦስት ዓመታት በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ በሥራ ስምሪቱ ዙሪያ ተጨማሪ ግልጽነት ለመፍጠር፣ ዜጎች ህጋዊ ባልሆኑ አማራጮች ላልተፈለገ ወጪና እንግልት እንዳይዳረጉ ከዛሬ ጀምሮ በማህበራዊ ትስስር ገጾቻችን ተከታታይ መረጃዎችን እናጋራለን፡፡ 📌ምን ምን ጉዳዮች ተካተዋል? ✅ ቁልፍ መስፈርቶ፦ በሥራ ስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን ማሟላት ስላለብዎ ጉዳዮች፣ ✅ ዋና ዋና ሂደቶች፦ ህጋዊ የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ለመሆን መከተል      ያለብዎት ሂደት፣ ✅ ስለስልጠና ማዕከላትና ክፍያ ስርዓት፦ የትኛው ስልጠናና የሥልጠና     ማዕከል ክፍያ ይጠይቃል? ✅ የኤጀንሲዎች ዝርዝርና ህጋዊ ሥራ ስምሪት የሚካሄድባቸው፦ ህጋዊ ስራ ስምሪት ላይ ፍቃድ ያላቸው ኤጀንሲዎችና መዳረሻ ሀገራት፣ ✅ለሰለጠኑና በከፊል ለሰለጠኑ ባለሙያዎች ያሉ ዕድሎች፦ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ ባለሙያዎች በሥምሪቱ ያላቸው እድልና መከተል ያለባቸው ቅደም          ተከተል፣ ✅ስኬታማ ታሪኮች፦ የህጋዊ ስራ ስምሪት ፋይዳዎች እና ስኬታማ ታሪኮች፣ ✅የርቀት የሥራ ዕድል፦ ካሉበት ሆነው ተጨማሪ ገቢ ማግኘት ስለሚችሉበት የርቀት ሥራዎች፣ ✅ጥያቄና መልስ፦ በሥምሪቱ ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል፣ 📢 የእርስዎ ሚና የማይተካ ነው!📢 ✅ ይህንን መረጃ በማጋራት ዜጎቻችን በህገወጦች አማላይ ማስታወቂያ ተታለው ላልተፈለገ ወጪና እንግልት ብቻ ሳይሆን ለከፋ አደጋ እንዳይጋለጡ የበኩልዎን ይወጡ!🚨 ✅ በሥራ ስምሪቱ ላይ ማንኛውንም ጥያቄ ካልዎት ያድርሱን፣ 📟ይከታተሉን! 🎯 ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ! ለወዳጅ ለጓገኛዎ ያጋሩ! ስለ ውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ማንኛውም ጥያቄ ካለዎት ይላኩልን! 🎯 በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ለመሆን ፍላጎት ካልዎት ህጋዊና  ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን ብቻ ይጠቀሙ፣ ሌሎችም     እንዲጠቀሙ ያበረታቱ፣ እራሰዎንና ሌሎችንም ከአደጋ ይጠብቁ!  

#በመካከላችን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ከሚመራበት መርሆች መካከል አካታችነት አንዱ ሲሆን በዚህም አካል ጉዳተኞች በመሰልጠንም ሆነ በማሰልጠን ሂደት ውስጥ እንዲሳተፉና ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ ያደርጋል። የማነ ግርማ ይባላል በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 13 አመታትን ያስቆጠረ የስራ ላይ ቆይታ አለው ወደ ስራ አለም ከመቀላቀሉ አስቀድሞ በፈርኒቸር ሜኪንግ በደረጃ 1 እና 2 እዚያው በኮሌጁ የሰለጠነ ሲሆን ስልጠናውን እንዳጠናቀቀም ኮሌጁ በወርክሾፕ ቴክኒሺያንነት የስራ ዕድል አመቻችቶለታል በተጨማሪም በደረጃ 3 እና 4 በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ስልጠናውን ተከታትሎ አጠናቋል። የዚህ ሳምንት የሥራና ክህሎት ቤተሰብ እንግዳችን ብርቱና በኮሌጁ ውስጥ የሚሰሩ ልዩ ልዩ ቴክኖሎጂዎችና የእንጨት ስራዎች ላይ በግንባር ቀደምነት የምናገኘው በስራውም ታታሪና ታዛዥ እንደሆነ የኮሌጁ ዲኖችና አብረውት የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራን ይመሰክራሉ፤ የማነ መስማት የተሳነው ሲሆን ከሰዎች ጋር ለመግባባት የማይቸግረው ጥሩ ተግባቢና በኮሌጁ ውስጥ ለአዲስ ገቢ ሰልጣኞች የምልክት ቋንቋ ስልጠና ድጋፍ እንደሚያደርግ ማወቅ ችለናል። ክህሎትና ሥራ ለሁሉም ከሁሉም በሁሉም!

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት የተቋሙን የ6ወር አፈፃፀም እና የEASE ፕሮጀክትን እስካሁን ተደረሰበትን አፈፃፀም ሪፖርት ለኮሌጁ ማህበረሰብ ቀርቦ ውይይት ተካሄደ:: መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸውም እንደ ተቋም ከዚህ አመት ጀምሮ በርካታ ዘርፈብዙ ስራዎችን ለማከናወን የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅዶችን በመንደፍ ወደተግበራ መገባቱን አስታውሰው ይህ ውጤታማ እንዲሆንም የኮሌጁን ማህበረሰብ የነቃ ተሳትፎን ከመቼው ጊዜ በላይ የሚጠይቅ ወቅት በመሆኑ ሁሉም አካል በዚህ አግባብ ተነሳሽነት በማሳይት ተልኮን መፈፅም እንደሚገባም ገልፀዋል:: በእለቱ በተካሄደው መድረክ የኮሌጁን የ2017 በጀት አመት የ6ወር አፈፃፀም ያቀረቡት የኮሌጁ የእቅድና በጀት ስራ ክፍል ሀላፊ አቶ አለማየሁ ብርሃኑ ሲሆኑ በቀረበው ሪፖርትም ኮሌጁ የበጀት አመቱን ትግበራን ከጀመረበት የዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት አንስቶ በ6ወር ውስጥ የነበረውን አጠቃላይ ንቅስቃሴ በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን አክለውም ኮሌጁ እስከ በጀት አመቱ መጠናቀቂያ ድረስ ለትግበራ በእቅድ የያዛቸውን ተግባራት ለመድረኩ ተሳታፊዎች አመላክተዋል:: በመቀጠል የEASE ፕሮጀክት ወደ ትግበራ ከገባበት ጊዜ አንስቶ የተከናወኑ ስራዎችን አፈፃፀም ሪፖርት በEASE ፕሮጀክት የሞኒተሪንግና ኢቫሉዌሽን አስተባባሪ ኢንጂነር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በቀረበው አፈፃፀምም የፕሮጀክቱን ባለሙያዎች ከማዋቀርና የኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርድ ከማቋቋም አንስቶ የፕሮጀክቱ አመራሮችንና ባለሙያዎችን በልምድ ልውውጥና ስልጠናዎች የማብቃት እንዲሁም 65 ለሚሆኑ የተቋሙ አገልግሎት ሰጪ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ መቻሉም ተገልፇል:: በተጨማሪም በቀረበው ሪፖርት በአስተዳደሩ ለሚገኙ የሚዲያ ባለሙያዎች እና የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አመራሮችና ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ያለውን የተዛባ አመለካከት መቀየር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መካሄዱም በሪፖርቱ ከቀረቡት ነጥቦች የሚጠቀሱ ናቸው:: በመጨረሻም የEASE ፕሮጀክት የቀጣይ ስድስት ወራት እቅድ በፕሮጀክቱ አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በዚህም በቀጣይ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ለመፈፀም በእቅዱ ላይ የተመላከት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በተቋሙ የሪኢኖቬሽን ስራዎች ፣ የአሰልጥኞች ስልጠና፣ የኢንተርፕሩነርሺፕ ስልጠናዎች፣ የሴቶችን መደገፍና ማብቃት እንዲሁ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠዎችን ተግባራዊ ለማድረግ መያዙ ከብዙ ጥቂቱ መሆኑን በቀረበው እቅድ ተመላክቷል:: የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረበው የአፈፃፀም ሪፖርትና የቀጣይ እቅድን መነሻ በማድረግ ለቀጣይ ትግባራት ውጤታማነት የሚረዱ ገንቢ እስተያየቶችና ምክረ ሃሳቦች በስፋት አንስተው ውይይት ተደርጎበት መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን የካቲት 1/2017 ዓ.ም

ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት መደበኛ ስራ 6ወር አፈፃፀምና የEASE ፕሮጀክት የሩብ አመት አፈጻጸምን ለኮሌጁ የቦርድ አባላት ቀረበ፡፡ የተቋሙን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የEASE ፕሮጀክት አፈጻጸም በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለቦርዱ የቀረበ ሲሆኑ በዚህም ኮሌጁ ከዝግጅት ምእራፍ ጀምሮ በ6ወሩ ውስጥ የነበረውን የእቅድ አፈፃፀምና የተሰሩ ስራዎችን እንዲሁም የተገኙ ውጤቶችን የገለፁ ሲሆን አያይዘውም በቀጣይ በተቋሙ ሊሰሩ በእቅድ የተያዙ ስራዎችን ለቦርድ አባላት አቅርበዋል፡: በመድረኩ የቀረበውን ሪፖርት መነሻ በማድረግም የቦርድ አባላቱ ሀሳብ አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በቀጣይ በሚኖረው እንቅስቃሴ ላይ ምክረ-ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል:: በመጨረሻም የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ በኮሌጁ እቅድ አፈፃፀም እንዲሁም በፕሮጀክቱ ትግበራ አፈጻጸም ላይ ማጠቃለያ እና የቀጣይ ስራ አቅጣጫና መመሪያም ሰጥተዋል፡፡ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥር 30/2017 ዓ.ም

ከአመታት በኋላ ህዳሴ የሆነለት ፕሮጀክት… “ፕሮጀክቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ የቅድመ ዝግጅት ስራውን በማጠናቀቅ ተመርቆ ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ የሚገባ ይሆናል” አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ መንግስት ኢንዱስትሪዎችን ለመደገፍና ሊያግዙ የሚችሉ የተርን ኪ ፕሮጀክቶች በአገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች ማቋቋሙ የሚታስ ነው፤ ከነዚህም ውስጥ በድሬዳዋ የሚገኘው ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን ምርቶችን እያመረተ ለፋብሪካዎች ግብአት እንዲያቀርብ ታልሞ የተመሰረተ ቢሆንም ባለፉት ዘጠኝ አመታት ግንባታው ተጠናቆና ማሽኖቹ ተሟልተው ወደ ስራ መግባት ሳይችል ለታለመለት አላማም ሳይውል በተለያዩ ምክንያቶች ያለምንም ስራ አስተዳደሩንና ነዋሪውን እንደታሰበው ሳይጠቅም ቆይቷል፡፡ ይሁንና የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሃር በሰጡት አቅጣጫ ማሽኖቹ ወደ ስራ ገብተው የስራ እድል ሚፈጥሩበት፣ የፋብሪካ ግብዓቶችን የሚያቀርቡበት እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች የተግባር ስልጠና የሚያገኙበት ለማድረግ ፕሮጀክቱ ወደ ድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር መጥቶ በስሩ ወደ ሚገኘው የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተላልፎ ውጤት አምጪ ስራዎችን ለመስራት እንቅስቃሴዎች የተደረጉ መሆኑንና ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ ለማስገባት የተከናወኑ ስራዎችን በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የመስክ ምልከታ መደረጉን የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል፡፡ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳላህዲን አብዱልሃሚድ በበኩላቸው የተርን ኪ ፕሮጀክት ለአስተዳደሩ ነዋሪ ከስልጠና በላይ የሚታሰበውን የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እሳቤን ተጨባጭ ለማድረግ አጋዥ ሆኖ ተገኝቷል፤ በዚህም ሰልጣኞች በተግባር ልምምድ የሚያደርጉበትና የስራ እድል እንዲፈጠርላቸው የሚያመቻች ሲሆን በአጠቃላይ ትምህርትና ስልጠናውን፣ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎችን በተሻለ አቅም ለመምራት የሚያስችል ይሆናል ብለዋል፡፡ በኮሌጁ የማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት ኃላፊና አሰልጣኝ መምህር የሆነው ዮሐንስ ተካ እንደገለጹት በኮሌጅ ለሚሰጠው ትምህርትና ስልጠና ፕሮጀክቱ አጋዥነት በቀጥታ የትምህርትና ስልጠና ጥራትን ከመጨመር አኳያ ሰልጣኞች ተግባራዊ የሆነ ልምድ እንዲያካብቱ የሚያግዝ መሆኑ ከኮሌጅ አጠናቀው ሲወጡ በራሳቸውም ሆነ በኢንዱስትሪዎች ላይ ተሰማርተው ሲሰሩ በክህሎት የበቁ እንደሚያደርጋቸው ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 30/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ከአመታት በኋላ ህዳሴ የሆነለት ፕሮጀክት… “ፕሮጀክቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ የቅድመ ዝግጅት ስራውን በማጠናቀቅ ተመርቆ ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ የሚገባ ይሆናል” አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ መንግስት ኢንዱስትሪዎችን ለመደገፍና ሊያግዙ የሚችሉ የተርን ኪ ፕሮጀክቶች በአገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች ማቋቋሙ የሚታስ ነው፤ ከነዚህም ውስጥ በድሬዳዋ የሚገኘው ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን ምርቶችን እያመረተ ለፋብሪካዎች ግብአት እንዲያቀርብ ታልሞ የተመሰረተ ቢሆንም ባለፉት ዘጠኝ አመታት ግንባታው ተጠናቆና ማሽኖቹ ተሟልተው ወደ ስራ መግባት ሳይችል ለታለመለት አላማም ሳይውል በተለያዩ ምክንያቶች ያለምንም ስራ አስተዳደሩንና ነዋሪውን እንደታሰበው ሳይጠቅም ቆይቷል፡፡ ይሁንና የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሃር በሰጡት አቅጣጫ ማሽኖቹ ወደ ስራ ገብተው የስራ እድል ሚፈጥሩበት፣ የፋብሪካ ግብዓቶችን የሚያቀርቡበት እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች የተግባር ስልጠና የሚያገኙበት ለማድረግ ፕሮጀክቱ ወደ ድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር መጥቶ በስሩ ወደ ሚገኘው የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተላልፎ ውጤት አምጪ ስራዎችን ለመስራት እንቅስቃሴዎች የተደረጉ መሆኑንና ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ ለማስገባት የተከናወኑ ስራዎችን በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የመስክ ምልከታ መደረጉን የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል፡፡ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳላህዲን በበኩላቸው የተርን ኪ ፕሮጀክት ለአስተዳደሩ ነዋሪ ከስልጠና በላይ የሚታሰበውን የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እሳቤን ተጨባጭ ለማድረግ አጋዥ ሆኖ ተገኝቷል፤ በዚህም ሰልጣኞች በተግባር ልምምድ የሚያደርጉበትና የስራ እድል እንዲፈጠርላቸው የሚያመቻች ሲሆን በአጠቃላይ ትምህርትና ስልጠናውን፣ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎችን በተሻለ አቅም ለመምራት የሚያስችል ይሆናል ብለዋል፡፡ በኮሌጁ የማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት ኃላፊና አሰልጣኝ መምህር የሆነው ዮሐንስ ተካ እንደገለጹት በኮሌጅ ለሚሰጠው ትምህርትና ስልጠና ፕሮጀክቱ አጋዥነት በቀጥታ የትምህርትና ስልጠና ጥራትን ከመጨመር አኳያ ሰልጣኞች ተግባራዊ የሆነ ልምድ እንዲያካብቱ የሚያግዝ መሆኑ ከኮሌጅ አጠናቀው ሲወጡ በራሳቸውም ሆነ በኢንዱስትሪዎች ላይ ተሰማርተው ሲሰሩ በክህሎት የበቁ እንደሚያደርጋቸው ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 30/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ዜና የቢሾፍቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅምንት አባላት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት እና ኮሌጁ
+5
#ዜና የቢሾፍቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅምንት አባላት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት እና ኮሌጁን እንቅስቃሴ ያስጎበኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ፡፡ ኮሌጁ በቀጣይ በተለያዩ የሞያ መስኮች የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ለድሬዳዋ ብሎም ለምስራቁ የሃገራችን ክፍል ከዛም አልፎ ለሃገራችን ብቁ የሆኑ በሙያ እንዲሁም በክህሎት የበለጸጉ ስራ ፈጣሪ የሆኑ ወጣቶችን እያፈራ ይገኛል ያሉ ሲሆን አያይዘውም በኮሌጁ እየተተገበሩ ያሉ ፕሮጀክቶች እንዲሁም መደበኛው ስራ ከ12ቱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤዎች አንጻር የተቃኙ ናቸው ብለዋል፡፡ የመስክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም የልኡካን ቡድኑ ጋር በነበረው የጋራ ውይይት ወቅት ልኡክ ቡድኑን የመሩት የቢሾፍቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ደበላ ተስፋ እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየወሰደ ያለው ቁርጠኝነት ለሌሎች ከተሞች አራያ መሆን የሚችል ነው ብለዋል፡፡በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለመላው ሃገራችን የሚበቃ ነው ብለዋል፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የፕሮጀክቶ አፈጸጸም እንዲሁም የግንባታ ሂደቱን እስካሁን የደረሰበት ደረጃ በአቶ መሃመድአወል ጠሃ ገለጻ ተደርጓል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥር 29/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ በ2017 በጀት ዓመት በመጀመሪያው ስድስት ወራት የስራ አጥነት ምጣኔን ከ18 ከመቶ በታች  ለማድረስ የተያዘውን ዕቅድ ማሳካት መቻሉን ተገለጸ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የማዘጋጃቤታዊ  አገልግሎት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤቱ ባቀረቡበት ወቅት በስራ እድል ፈጠራ በከተማ እና በገጠር ለ10,588 ቋሚ እና ጊዜያዊ የስራ እድሎች ለመፍጠር ታቅዶ ለ9,995 ዜጎች የስራ እድል የተፈጠረ ሲሆን የእቅዱን 94% ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል። በአስተዳደሩ የዋጋ ግሽበትን በመቆጣጠር እና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ በ2016 የነበረውን የ28 በመቶ የዋጋ ንረት እና የ27 በመቶ የምግብና ምግብ ነክ ሸቀጦች የዋጋ ግሸበት ለመቀነስ  በስድስት ወሩ 17.3 በመቶ በማዉረድ በበጀት ዓመቱ ለታቀደዉ ከ10 በመቶ በታች ለማድረግ የተያዘውን እቅድ ማሳካት መቻሉ ተመላክቷል። የአስተዳደሩን ገቢ በተመለከተ በ2017 በጀት ዓመት በመጀመሪያው 6 ወራት 3.3 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ማለትም 2.8 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ የተቻለ ሲሆን  የእቅዱ 85% ማሳካት ተችሏል። የካፒታል ፕሮጀክት አፈጻጸምን በተመለከተ በበጀት አመቱ 123 አዲስ እና 35 ነባር በጥቅሉ 158 ፕሮጀክቶች በካፒታል በጀት ተደግፈው እንዲሰሩ የታቀዱ ሲሆን  የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ሲታይ 14 ፕሮጀክቶች የተጠናቀቁ፤ 4 ፕሮጀክቶች በመጠናቀቅ ሂደት ላይ ያሉ 60 ፕሮጀክቶች በጥሩ አፈጻጸም የተጠናቀቁ መሆናቸው በሪፖርቱ ተገልጿል። በግብርና ዘርፍ የግብርና ምርትና ምርታማነትን የማሳደግና የአምራቹን ህብረተሰብ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ  እንዲሁም ለኢኮኖሚ ዘርፍ አጋዥ ሚና ለመጫወት በአነስተኛ አርሶ አደሮች እርሻ በሚከናወኑ የሰብል፤ የእንስሳት እርባታና የከተማ ግብርናን ልማት እንቅስቃሴ እየተከናወኑ ተግባራት በተሻለ አፈጻጸም የነበራቸው መሆኑ በሪፖርቱ ተመላክቷል። ©️DGC ጥር 28/2017

በአስተዳደሩ በ2017 በጀት ዓመት በመጀመሪያው ስድስት ወራት የስራ አጥነት ምጣኔን ከ18 ከመቶ በታች  ለማድረስ የተያዘውን ዕቅድ ማሳካት መቻሉን ተገለጸ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የማዘጋጃቤታዊ  አገልግሎት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤቱ ባቀረቡበት ወቅት በስራ እድል ፈጠራ በከተማ እና በገጠር ለ10,588 ቋሚ እና ጊዜያዊ የስራ እድሎች ለመፍጠር ታቅዶ ለ9,995 ዜጎች የስራ እድል የተፈጠረ ሲሆን የእቅዱን 94% ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል። በአስተዳደሩ የዋጋ ግሽበትን በመቆጣጠር እና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ በ2016 የነበረውን የ28 በመቶ የዋጋ ንረት እና የ27 በመቶ የምግብና ምግብ ነክ ሸቀጦች የዋጋ ግሸበት ለመቀነስ  በስድስት ወሩ 17.3 በመቶ በማዉረድ በበጀት ዓመቱ ለታቀደዉ ከ10 በመቶ በታች ለማድረግ የተያዘውን እቅድ ማሳካት መቻሉ ተመላክቷል። የአስተዳደሩን ገቢ በተመለከተ በ2017 በጀት ዓመት በመጀመሪያው 6 ወራት 3.3 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ማለትም 2.8 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ የተቻለ ሲሆን  የእቅዱ 85% ማሳካት ተችሏል። የካፒታል ፕሮጀክት አፈጻጸምን በተመለከተ በበጀት አመቱ 123 አዲስ እና 35 ነባር በጥቅሉ 158 ፕሮጀክቶች በካፒታል በጀት ተደግፈው እንዲሰሩ የታቀዱ ሲሆን  የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ሲታይ 14 ፕሮጀክቶች የተጠናቀቁ፤ 4 ፕሮጀክቶች በመጠናቀቅ ሂደት ላይ ያሉ 60 ፕሮጀክቶች በጥሩ አፈጻጸም የተጠናቀቁ መሆናቸው በሪፖርቱ ተገልጿል። በግብርና ዘርፍ የግብርና ምርትና ምርታማነትን የማሳደግና የአምራቹን ህብረተሰብ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ  እንዲሁም ለኢኮኖሚ ዘርፍ አጋዥ ሚና ለመጫወት በአነስተኛ አርሶ አደሮች እርሻ በሚከናወኑ የሰብል፤ የእንስሳት እርባታና የከተማ ግብርናን ልማት እንቅስቃሴ እየተከናወኑ ተግባራት በተሻለ አፈጻጸም የነበራቸው መሆኑ በሪፖርቱ ተመላክቷል። ©️DGC ጥር 28/2017

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከኔዘርላንድ የልማት ድርጅት (SNV) ጋር በመተባበር በወጣት፣ ሴቶች እና አካል ጉዳተኞች ለሚመሩ በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር ለሚገኙ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በበግና ፍየል ማድለብ ለተሰማሩ በአጠቃላይ አስር ማህበራት ለእያንዳንዱ ኢንተርፕራይዝ 100,000 ብር የሚገመት ስራ ማስጀመሪያ ድጋፍ ተደረገ፤ የድጋፍ ርክክብ ስነ ስርዓቱ የቢሮው ተወካይ እና የልማት ድርጅቱ ተወካይ እንዲሁም የእንስሳት ጤና እና ሀብት ልማት ተወካይ በተገኙበት የተደረገ ሲሆን የተደራጁት ወጣቶች፣ ሴቶችና አካል ጉዳተኛ ዜጎች የሥራ እድል ለራሳቸውና ለሌሎች እንደሚፈጥሩ እንዲሁም ለሌሎች ምሳሌ በመሆን በበግና ፍየል ማድለብ ላይ በአነስተኛ አቅምና እውቀት አሁን በመጀመር በቀጣይ አስፍተውና አጠናክረው እንዲቀጥሉ ከባለሙያዎች ጋር ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን ይህም ድጋፍ ከዚህ በፊት ሲደረግ የነበረው ተከታታይ ድጋፍ አካል ነው፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 27/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ