fa
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

رفتن به کانال در Telegram
1 067
مشترکین
-224 ساعت
-67 روز
+430 روز
آرشیو پست ها
በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት አምራች ተቋማት ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር በቅርበት ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡ የHope Enterprise -Seed Project ከድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በጋራ በመሆን የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ከኢንዱስትሪዎች ጋር ለማስተሳሰር ያለመ የውይይት መድረክ በዛሬው እለት ተከናወነ፡፡ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪዎችና ተቋማት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማስጠበቅ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ እየሰራ እንዳለ ይታወቃል፡፡ይህም ተግባሩ በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚስተዋለውን ችግር ለመፍታትና የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችሮችን ለመቅረፍ አስችሏል፡፡ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እና በኢንዱስትሪዎች መካካል ያለውን ክፍተት ለመሙላት ታስቦ በዛሬው እለት የተከናወነው ይህ የውይይት መድረክ የምናሰለጥናቸውን ሰልጣኞች በኢኮኖሚው ላይ ተጠቃሚ መሆን እንዲችሉ ኢንዱስትሪዎች ከድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በተሸለ መልኩ ተቀራርበው ሊሰሩ ይገባል ያሉት የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ አያይዘውም የPublic privet Partnershipን ለማሳደግ እና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ እንዲያድግና በኮሌጆች ውስጥ የሚሰለጥኑ ሰልጣኞች የስራ ፈጣሪነትን የተላበሱ እንዲሆኑ በኮሌጆች ውስጥ ከሚሰራው ስራ በተጨማሪ ኢንዱስትሪዎችና ደጋፊ ድርጅቶች ተቀራርበው እየሰሩ ይገኛሉ ያሉት የHope Enterprise- Seed Project አስተባባሪ አቶ መላኩ ሲሆኑ አያይዘውም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ጥቂት አንጋፋ ኮሌጆች ውስጥ የሚመደብ እንደመሆኑ መጠን እንደ ከHope Enterprise- Seed Project ጋር በቅርበት እየሰራና ሌሎች ኮሌጆችን የማብቃት ስራ እየሰራ ነው ለዚህም ከፍተኛ ምስጋና እናቀርባለን ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት የተደረገው የውይይት መድረክ ላይ ኮሌጁ ከSEED Project እና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እስካሁን የሰራቸውን ስራዎች የመነሻ ጽሁፍ በአቶ ዘየደ ተክሌ የቀረበ ሲሆን፣ በSEED በኩል ደግሞ በአቶ መላኩ በኩል ቀርቦ በመጨረሻም በቀረቡት ጽሁፎች ላይ ውይይት በማድረግ የመድረኩ ፍጻሜ ሆኗል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ግንቦት 20/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

E-LMIS ሥራ ፈላጊዎችን ለመመዝገብ ብቻ ሳይሆን ከምዝገባ ባለፈ የበርካታ ተጨባጭ ዕድሎች ተጠቃሚ ለማድረግ ታልሞ የተነደፈ ሰፊ መድረክ ነው ። በE-LMIS ከሚያገኟቸው ዕድሎች መካከል ፦ 📍 የሀ
E-LMIS ሥራ ፈላጊዎችን ለመመዝገብ ብቻ ሳይሆን ከምዝገባ ባለፈ የበርካታ ተጨባጭ ዕድሎች ተጠቃሚ ለማድረግ ታልሞ የተነደፈ ሰፊ መድረክ ነው ። በE-LMIS ከሚያገኟቸው ዕድሎች መካከል ፦ 📍 የሀገር ውስጥ ሥራዎችን ፦ በሀገር ውስጥ ያሉ ክፍት የስራ ቦታዎችን በቀላሉ ለማግኘት ✈️ የውጭ ሀገር የሥራ ዕድሎች፦ ህጋዊና ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ለማመልከት 🏠 የርቀት (Remote) ሥራዎች፦ ከቤት ወይም ካሉበት ሆነው የሚሰሩባቸውን የስራ ዕድሎች ለማግኘት 🆔 የሰራተኛ መለያ (Labor ID)፦ የራስዎን ይፋዊ የዲጂታል የሥራ መለያ ለመያዝ 🤝 ታማኝ አሰሪዎች፦ በመንግስት ከተረጋገጡ ድርጅቶች ጋር በቀጥታ ለመገናኘት 🔔 የሥራ ጥቆማዎች፦ አዲስ የሥራ ማስታወቂያ ሲወጣ ወዲያውኑ በስልክዎ መልዕክት ለመቀበል የእነዚህን እና የሌሎች በርካታ ዕድሎች ተጠቃሚ ለመሆን ዛሬውኑ ይመዝገቡ ሁሉንም በአንድ ቦታ ያግኙ ! We can/ይቻላል !

ካናዳ፤ ምዝገባም ሆነ ስምሪት አልተጀመረም! 🛑 የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎች ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ በውጭ ሀገራት በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ላይ በህጋዊ መንገድ እንዲሰማሩ ለማስቻል በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት ዜጎች በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (lmis.gov.et) ላይ በመመዝገብና ህጋዊ ሂደቶችን በመከተል፣ ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ስምምነት ወደተፈራረመችባቸው የሚከተሉት ሀገራት በህጋዊ መንገድ በመሰማራት ላይ ይገኛሉ፦ 👉ሳውዲ አረቢያ 👉የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ 👉ጆርዳን 👉ኳታር 👉ሊባኖስ 📍ወደ ካናዳ የሚደረግ የሥራ ስምሪት አለ? የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መቀመጫውን ካናዳ ካደረገው "ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል" (FUTURE FIT INTERNATIONAL INC.) ጋር ስምምነት የፈጸመው በዋነኛነት ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ነው። ስምምነቱ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ብቻ ያተኩራል፦ • ከካናዳ ኮሌጆች ጋር በመተባበር ተማሪዎችን በዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ በሚፈለጉ ክህሎቶች ማሰልጠን፤ • ብቁ የሆኑ ተማሪዎች በካናዳ በሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የነፃ ትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማመቻቸት። ⚠️ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ! ከዚህ ስምምነት ውጪ፦ ✅"ሚኒስቴሩ ወደ ካናዳ ህጋዊ የሥራ ስምሪት ጀምሯል" በማለት የተሳሳተ መረጃ ከሚሰጡ፤ ✅"ወደ ካናዳ እንልክዎታለን" በማለት ከፍተኛ ገንዘብ ከሚጠይቁ፤ ✅"ከሚኒስቴሩ ህጋዊ ውክልና ተሰጥቶናል" ከሚሉ አጭበርባሪዎች ራሳችሁን ጠብቁ! 📍ምን ማወቅ ይኖርብዎታል? ✍️ከፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል ጋር የተደረገው ስምምነት ወደ ተግባር ሲገባ፣ ዝርዝር መረጃው በሚኒስቴሩ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና በብሔራዊ ሚዲያዎች ብቻ ይፋ ይደረጋል። ✍️ለዚህ ፕሮግራም ተጠቃሚ ለመሆን ምንም ዓይነት ክፍያ መፈጸም አይጠበቅብዎትም! ክፍያ የሚጠይቁ አካላት ሁሉ አጭበርባሪዎች መሆናቸውን ይወቁ። ✍️አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎችን ሲመለከቱ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ (  9138 በነፃ የስልክ መስመር ወይም info@mols.gov.et ) እና በአቅራቢያዎ ለሚገኙ የህግ አስከባሪ አካላት ይጠቁሙ። 🚨ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት ይፋዊ አድራሻዎቻችንን ብቻ ይጠቀሙ፦ ግንቦት 19/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYI

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447ኛ ዓመተ ሂጂራ የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተ
+1
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447ኛ ዓመተ ሂጂራ የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በዓሉ የፍቅር፣ የደስታ እና የመተሳሰብ እንዲሆንም ተመኝተዋል! በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ! ኢድ ሙባረክ!!

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የአምራች ኢንዱስትሪውን ፍላጎት ለመለየት የተዘጋጀ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ:: አምራች ኢንዱስትሪው የሚጠይቀውን ብቁና የሰለጠን የሰው ሀይል በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ አሰልጥኖ ለማቅረብ ታሳቢ ያደረገ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በተቋም ደረጃ የተጠና ሲሆን ወጣቶች ጊዜው የሚጠይቀውን የአጫጭር ስልጠና ምርጫቸው ከማድረጋቸው ጋር ተያይዞ የአምራች ኢንዱስትሪውን የሙያ ፍላጎት መሰረት ያደረገ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም ለመቅረፅ የጥናት ቡድኑ ከኢንዱስትሪ አድቫይዘሪግ ቦርድ አባላት ጋር በቅንጅት መስራቱም ተገልፇል:: በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ትኩረት ተደርጎባቸው ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ለኢንዱስትሪው ግብዓት የሚሆኑ ብቁ ባለሙያዎችን የማፍራቱን ሂደትን መደገፍ ዋነኛው መሆኑ የተገለፅ ሲሆን የፕሮጀክቱ ባለሙያዎች ከትምህርትና ስልጠና ዘርፉ ጋር በመቀናጀት ባዘጋጁት የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት ያደርገ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም ላይ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ሲያደርግም ቆይቷል:: በፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ መሰረት ውጤታማነታቸው ታምኖበት የተለዩ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራሞችን የጥናት ቡድኑ በዝርዝር ያቀረበ ሲሆን በተጨማሪም ለስልጠና ፕሮግራሞቹ እየተዘጋጁ ሚገኙት ማሰልጠኛ ሞጁሎች ላይም ለባለድርሻ አካላት ገለፃ አድርገዋል:: በመድረኩ በቀረቡት አጠቃላይ ሰነዶች መነሻነት ውይይት የተካሄደ ሲሆን ተሳታፊዎች በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የበቃ የሰው ሀይል ከማሟላት አኳያ በጥናቱ ያልተዳሰሱና ሊካተቱ ይገባል ያሏቸውን ጉዳዮች ለጥናት ቡድኑ አመላክተዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ ለሚገኙ አምስት የግል እና ሶስት የመንግስት ኮሌጆች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የድጋፍና ክትትል እና ጥራት ቁጥጥር አደረጃጀቶችን የሚያጠናክር የአቅም ግንባታ መድረክ ተዘጋጀ፡፡ ይህም የአቅም ግንባታ መድረክ ኮሌጆች በድጋፍና ክትትል እና በጥራት ቁጥጥር ቡድን ተዋቅረው እያካሄዱ የሚገኝ ሲሆን በይበልጥ በቀጣይነትም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራትን ለማስጠበቅና ለማረጋገጥ ውስጣዊ አቅም የሚያጎለብት መሆኑም ታውቋል፡፡ በዚህም በየተቋማቱ የሚካሄደው የስልጠና ፕሮግራም ሁሉም አሰልጣኝ መምህራን የሚሰጡት ስልጠና በዕቅድ ላይ ተመስርተው ስለመስጠታቸው፤ እያንዳንዱ የስልጠና ፕሮግራም በተቀመጠው መመሪያና አላማ መሰረት እየተሰጠ ስለመሆኑ በተያያዘም ለስልጠና አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች መሟላታቸውንና የስልጠና ቦታዎች አመቺነት ማረጋገጥ ላይ ትኩረት የሚደረግ ይሆናል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 17/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ ለሚገኙ አምስት የግል እና ሶስት የመንግስት ኮሌጆች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የድጋፍና ክትትል እና ጥራት ቁጥጥር አደረጃጀቶችን የሚያጠናክር የአቅም ግንባታ መድረክ ተዘጋጀ፡፡ ይህም የአቅም ግንባታ መድረክ ኮሌጆች በድጋፍና ክትትል እና በጥራት ቁጥጥር ቡድን ተዋቅረው እያካሄዱ የሚገኝ ሲሆን በይበልጥ በቀጣይነትም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራትን ለማስጠበቅና ለማረጋገጥ ውስጣዊ አቅም የሚያጎለብት መሆኑም ታውቋል፡፡ በዚህም በየተቋማቱ የሚካሄደው የስልጠና ፕሮግራም ሁሉም አሰልጣኝ መምህራን የሚሰጡት ስልጠና በዕቅድ ላይ ተመስርተው ስለመስጠታቸው፤ እያንዳንዱ የስልጠና ፕሮግራም በተቀመጠው መመሪያና አላማ መሰረት እየተሰጠ ስለመሆኑ በተያያዘም ለስልጠና አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች መሟላታቸውንና የስልጠና ቦታዎች አመቺነት ማረጋገጥ ላይ ትኩረት የሚደረግ ይሆናል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 17/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

‘ፈልጉልኝ’፤ ብቁ ባለሙያዎችን ለአሠሪዎች፣ ፍትሃዊ የሥራ ዕድል ለሁሉም ዜጎች! የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት አካል የሆነና አሠሪና ሠራተኞችን በቀላሉ ማገናኘት የሚያስችል ‘ፈልጉልኝ’ የተሰኘ ሀገራዊ ዲጂታል መተግበሪያ ዛሬ በይፋ አስመርቀን ወደ ሥራ አስገብተናል። በመርሃ ግብሩ ‘ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030’ ስትራቴጂን መሠረት በማድረግ የመጪውን ዘመን የሥራ ገበያ መልክ እና የሰው ሠራሽ አስተውሎትን መሰረት ያደረጉ ዲጂታል መተግበሪያዎች በሀገራዊ ልማት ውስጥ ያለውን ሚና በጥልቀት ያየንበት ውጤታማ የፓናል ውይይትም አካሂደናል። ወደ ሥራ የገባው ይህ ዲጂታል መተግበሪያ፤ በሀገራችን ምጣኔ-ሀብት ውስጥ በሥራ ገበያው ውስጥ ያለውን የመረጃ ክፍተት በመቅረፍ ሥራ ፈላጊ ዜጎችንና አሠሪዎችን ካሉበት ሆነው በቀጥታ የሚያገናኝ ዘመናዊ የሥራ ሥነ-ምህዳር ነው። መተግበሪያው መደበኛ ያልሆነውን የሥራ ዘርፍ ወደ መደበኛ የኢኮኖሚ ሥርዓት ከማሸጋገሩም በላይ፣ በማስረጃ ላይ የተመሠረተ የፖሊሲ ቀረጻን በማገዝ እና አስተማማኝ የመረጃ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ አኳያም ሚናው የላቀ ነው። ከሁሉ በላይ በቴክኖሎጂ አማካኝነት የሥራ ገበያውን ትክክለኛ ፍላጎት በማሳየት፣ የትምህርትና ሥልጠና ተቋማት የሥራ ገበያው የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል እንዲያፈሩ ስልታዊ አስተዋጽኦም ያበረክታል። ይህንን ዘመናዊ መተግበሪያ እውን በማድረግ ሂደት ሚና ለነበራችሁ አካላት በሙሉ ያለኝ ልባዊ ምስጋና የላቀ ነው። የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ ያለውን ልምድ እንዲሁም ፕሮጀክቶችን የማስፈጸም አቅምን ሌሎች ተቋማት ሊጋሩት ይገባል ተባለ፡፡ በGermeny Development Bank/KFW እና AUDA-NEPAD
+1
ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ ያለውን ልምድ እንዲሁም ፕሮጀክቶችን የማስፈጸም አቅምን ሌሎች ተቋማት ሊጋሩት ይገባል ተባለ፡፡ በGermeny Development Bank/KFW እና AUDA-NEPAD አማካኝነት ተግባራዊ የሚደረገው የSIFA ፕሮጀክትን ክትትልና ግምገማ እንዲሁም ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ ያለመ የከፍተኛ ባለሙያዎች የመስክ የስራ ጉብኝት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዛሬው እለት ተከናወነ፡፡ የከፍተኛ ልኡክ ቡድኑን የተቀበሉትና የኮሌጁን አጠቃላይ ስራ ያስጎበኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት የSIFA ፕሮጀክት በኮሌጃችን ተግባራዊ መሆኑ የአካባቢውን ብሎም የቀጠናውን ወጣቶች በICT የዳበረና እውቀት ያለው ትውልድ ለመገንባት ያስችለናል፡፡በተጨማሪም ኮሌጁ በICT እና በRailway ምህንድስና ዘርፍ እንዲሁም በተለያዩ ሙያዎች የልህቀት ማእከል ለመሆን እየሰራ እንደ መሆኑ መጠን ይህ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ኮሌጁን በICT ዘርፍ ቀዳሚ የልህቀት ማእከል የሚያደርግ ይሆናል ብለዋል፡፡ ከፍተኛ ልኡክ ቡድኑን የመሩት በAUDA-NEPAD የSIFA ፕሮጀክት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ገመቹ እንዳሉት ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ ያለውን ልምድ እንዲሁም ፕሮጀክቶችን የማስፈጸም አቅምን ሌሎች ተቋማት ሊጋሩት ይገባል ያሉ ሲሆን በተለየ መልኩ ከአስተዳደሩ ጋር ያለው ስራን ተናቦ የመስራት ልምዱ ፕሮጀክቱ በታለመለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ይረዳዋል ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት በኮሌጁ የተገኘው ይህ ከፍተኛ የባለሙያዎች ቡድን በኮሌጁ የሚገኘውንና ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘውን የICT ልህቀት ማእከልን እንዲሁም የተለያዩ የስራ ክፍሎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታ እጅግ ደስተኛ እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ግንቦት 17/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ ያለውን ልምድ እንዲሁም ፕሮጀክቶችን የማስፈጸም አቅምን ሌሎች ተቋማት ሊጋሩት ይገባል ተባለ፡፡ በGermeny Development Bank/KFW እና AUDA-NEPAD
+1
ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ ያለውን ልምድ እንዲሁም ፕሮጀክቶችን የማስፈጸም አቅምን ሌሎች ተቋማት ሊጋሩት ይገባል ተባለ፡፡ በGermeny Development Bank/KFW እና AUDA-NEPAD አማካኝነት ተግባራዊ የሚደረገው የSIFA ፕሮጀክትን ክትትልና ግምገማ እንዲሁም ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ ያለመ የከፍተኛ ባለሙያዎች የመስክ የስራ ጉብኝት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዛሬው እለት ተከናወነ፡፡ የከፍተኛ ልኡክ ቡድኑን የተቀበሉትና የኮሌጁን አጠቃላይ ስራ ያስጎበኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት የSIFA ፕሮጀክት በኮሌጃችን ተግባራዊ መሆኑ የአካባቢውን ብሎም የቀጠናውን ወጣቶች በICT የዳበረና እውቀት ያለው ትውልድ ለመገንባት ያስችለናል፡፡በተጨማሪም ኮሌጁ በICT እና በRailway ምህንድስና ዘርፍ እንዲሁም በተለያዩ ሙያዎች የልህቀት ማእከል ለመሆን እየሰራ እንደ መሆኑ መጠን ይህ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ኮሌጁን በICT ዘርፍ ቀዳሚ የልህቀት ማእከል የሚያደርግ ይሆናል ብለዋል፡፡ ከፍተኛ ልኡክ ቡድኑን የመሩት በAUDA-NEPAD የSIFA ፕሮጀክት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ገመቹ እንዳሉት ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ ያለውን ልምድ እንዲሁም ፕሮጀክቶችን የማስፈጸም አቅምን ሌሎች ተቋማት ሊጋሩት ይገባል ያሉ ሲሆን በተለየ መልኩ ከአስተዳደሩ ጋር ያለው ስራን ተናቦ የመስራት ልምዱ ፕሮጀክቱ በታለመለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ይረዳዋል ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት በኮሌጁ የተገኘው ይህ ከፍተኛ የባለሙያዎች ቡድን በኮሌጁ የሚገኘውንና ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘውን የICT ልህቀት ማእከልን እንዲሁም የተለያዩ የስራ ክፍሎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታ እጅግ ደስተኛ እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ግንቦት 17/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር ከተለያዩ  የመንግስት ሴክተር መስሪያቤት የተወጣጡ ተወካዮች እና የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት በከተማ እና በገጠር የተሰሩ የስራ ዕድል ፈጠራና ሌሎች የልማት ስራዎች ጉብኝት አካሄዱ፡፡ የፕሮግራሙ ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት በያዝነው በጀት ዓመት ባለፉት 9 ወራት የተከናወኑ አበይት ተግባራት ምልከታ ተደረጉ ሲሆን ወጣቶች እና ሴቶችን ተጠቃሚ በማድረግ በኩል ሰፊ ስራዎች የተሰሩባቸው በዶሮ እርባታ ዘርፍ እና ንብ ማነብ የተሰማሩ አራት ኢንተርፕራይዞች እና የህብረት ስራ የማህበራት ያሉበት ደረጃ ታይቷል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የገጠር ስራ ዕድል ፈጠራ ከግብርና ዉሃ ማዕድንና ኢነርጂ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ማስተባበርያ ጋር በመተባበር በአዳዳ፣ በኢጀአነኒ፤ ቢሻንቤሄ እና ቢዮአዋሌ ቀበሌዎች የተከናወኑ አመርቂ ክንውኖች ምልከታም ተደርጓል፡፡ ሁለት ኢንተርፕራይዞች በዶሮ እርባታ ዘርፍ እና  ሁለት ኢንተርፕራይዞች በንብ ማነብ የተሰማሩ እና አንድ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ህብረት ስራ ማህበር በአጠቃላይ አራት ኢንተርፕራይዞችና አንድ የህብረት ስራ ማህበር ያሉበት ደረጃ ታይቷል፡፡ በቢሻንቤሄ 42 ሄክታር ማልማት የሚችል የመስኖ ተቋም ግንባታ 90 በመቶ ግንባታው መጠናቀቁ ታይቷል፡፡ ይህ ግንባታ 267 አባ/እማወራ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ታውቋል፡፡ ሰፊ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ያለው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ዙሪያ ዋነኛው 11 ሄክታር የሸፈነ የፓፓያ ክላስተር ማሳ ጉብኝት በዛሬው ዕለት ተደርጓል፡፡ አቶ ሲሻው አያሌው የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ስራ መስተባበሪያ ዩኒት ሰብሳቢ በሰጡት ገለጻ የምርትና ምርታማነት ዕድገትን ለማስገኘት እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ FSRP በነቂስ ከተለያዩ ሴክተር መ/ቤቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ ቴክኒካል ኮሚቴው በጉብኝቱ ማጠቃለያ ወቅት እንደተናገሩት የህብረተቡን የኑሮ ደረጃ ለመቀየር አመርቂ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ ተናግረው ለውጡ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ ወጣቶችን እና ሴቶችን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ በፕሮግራሙ የሚሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ለውጦችን ማሳየት በመቻላቸው ሌሎችም ልምድ ሊቀምሩበት እንደሚገባ ሃሳብ ሰጥተዋል፡፡

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa - آمار و تحلیل کانال تلگرام @bolsdd