ትኩስ መረጃ
📈 تحلیل کانال تلگرام ትኩስ መረጃ
کانال ትኩስ መረጃ (@tekus_info) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 70 368 مشترک است و جایگاه 3 642 را در دسته فیلمها و رتبه 435 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 70 368 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 10 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -1 340 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 229 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 1.61% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 1.21% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 1 131 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 847 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 4 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
توضیحی برای کانال ارائه نشده است.
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 11 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فیلمها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 11 ژوئن | +260 | |||
| 10 ژوئن | +268 | |||
| 09 ژوئن | +282 | |||
| 08 ژوئن | 0 | |||
| 07 ژوئن | 0 | |||
| 06 ژوئن | 0 | |||
| 05 ژوئن | 0 | |||
| 04 ژوئن | 0 | |||
| 03 ژوئن | +82 | |||
| 02 ژوئن | +125 | |||
| 01 ژوئن | 0 |
💙ጂም እና ስፓ 💙 ሬስቶራንት 💙የልጆች መጫወቻ 💙ጌም ዞን 💙ሲኒማ 💙አዳራሽ 💙በቂ የሆነ ሊፍት ያለው (10) 💙የገበያ ማእከል 💙 የደህንነት ካሜራዎች 💙4 ቤዝመንት በቂ የመኪና ማቆሚያ 💙የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ ስቴሽን 💙 ዘመናዊ የቆሻሻ ማስወገጃ 💙ተጠባባቂ ጀነሬተር 💙 የከርሰ ምድር ውሃ⭐️የምንገበያየዉ በኢትዮጵያ ብር ሲሆን በጊዜያት መቀያየር የሚኖር ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ አለመኖሩ ጀንቦሮን እጅጉኑ ተመራጭ ያደርገዋል! ግድየሎትም ያውሩን በእጥፍ ያተርፋሉ ለበለጠ መረጃና ለሳይት ጉብኝት አሁኑኑ ይደውሉ ወይም በዋትስአፕ ያውሩን ☎️ +251-911-97-09-01 ☎️ +251-975-19-93-11 ❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️
| 2 | ኦባሳንጆ መቀሌ ገቡ‼️
የፕሪቶሪያ ስምምነት አደራዳሪ ከነበሩት ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ የአውስትራሊያና የኢንግሊዝ ተወካዮች ያካተቱ የልኡካን ቡድን ከትግራይ ክልላዊ መንግስት ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ለመወያየት መቐለ ከተማ ገብተዋል። ህወሓት በትግራይ ክልል እያደረገ ያለውን ወታደራዊ አፈሳ አጠናክሮ ቀጥሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 345 |
| 3 | እውነታ_ማጣራት፡ ሀሰት: ምስጢረሥላሴ ታምራትን በተመለከተ የተሰራጩት እነዚህ ሁለት ተንቀሳቃሽ ምስሎችና ፎቶግራፍ ትክክለኛ አይደሉም
ግንቦት 24 ቀን በተካሄደው የ2018 የኢትዮጵያ ምርጫ ዕጩ የሆነችውን ፖለቲከኛ ምስጢረሥላሴ ታምራት ያሳያል በሚል በፌስቡክ ማኅበራዊ ገጽ ላይ የተጋሩት እነዚህ ሁለት ተንቀሳቃሽ ምስሎች እንዲሁም አንድ ፎቶግራፍ ሀሰት ናቸው።
ይህ ተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጨው፣ ፖለቲከኞቹ በሰላማዊ መንገድ በምርጫ ውድድር ላይ በንቃት እየተሳተፉ ባሉበት ወሳኝ ወቅት ላይ ነው። በተጨማሪም ተንቀሳቃሽ ምስሉ በማኅበራዊ ገጾች ላይ የተጋራው፥ ዕጩዎቹ የሚወክሉት ፓርቲ በተደጋጋሚ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪዎችን በማቅረብ ላይ በሚገኝበት ወቅት ነው።
በዘንድሮ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ ዕጩ ምስጢረሥላሴ ታምራት ላይ ያነጣጠሩና በፌስቡክ ማኅበራዊ ገጽ ላይ የተጋሩ ሁለት ተንቀሳቃሽ ምስሎችንና አንድ ፎቶግራፍ በጥልቀት የመረመረ ሲሆን፥ የተሰራጩት መረጃዎች በሙሉ ሀሰተኛ መሆናቸውን ተረጋግጧል።
በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ በተደረጉ የፓርቲዎች ክርክር መድረክ ላይ በምታሳየው ድፍረት የተሞላበት የሃሳብ ፍልሚያ ከፍተኛ ድጋፍን እንዲሁም ጠንካራ ትችቶችን እያስተናገደች የምትገኘው ፖለቲከኛዋ ሚስጥርስላሴ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የስም ማጥፋት ዘመቻ (Character Assassination) ኢላማ ሆናለች። በተለይም….
Via_Addis standard
@Addis_News
@Addis_News | 377 |
| 4 | ዛሬ የሚጀምረው ተናፋቂው የዓለም ዋንጫ‼
በመላው ዓለም በጉጉት የሚጠበቀውና ከምድር ታላላቅ የስፖርት ሁነቶች አንዱ የሆነው የዓለም ዋንጫ ዛሬ በይፋ ይጀምራል።
ይህ ታላቅ መድረክ ልዩ ልዩ ሀገራትን፣ ባህሎችንና በቢሊዮን የሚቆጠሩ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን በአንድነት የሚያስተሳስር ልዩ የደስታ በዓል ነው።
በውድድሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሦስት ሀገራት — አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በጋራ ይህንን ውድድር ያስተናግዳሉ።
ይህ ታሪካዊ እትም፣ የእግር ኳስን ዓለም አቀፋዊ ዕድገትና ሰዎችን የማስተሳሰር አስደናቂ ኃይል የሚያሳይ፣ በታሪክ እጅግ ግዙፍ እና ታላቅ ዓላማ ያነገበ የዓለም ዋንጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ከቦነስ አይረስ ጎዳናዎች እስከ አዲስ አበባ መንደሮች፣ ከአውሮፓ ከተሞች እስከ አፍሪካና እስያ ገጠራማ አካባቢዎች፣ የመላው ዓለም እግር ኳስ አፍቃሪያን ዓይኖች አሁን ወደ አንዱ ታላቅ መድረክ አቅንተዋል።
ለሚቀጥሉት ሳምንታት፣ ሀገራት ለላቀው የእግር ኳስ ክብር በሚያደርጉት ፍልሚያ፣ መላው ዓለም በጋራ ይደሰታል፣ አብሮ ይጨነቃል፣ እንዲሁም አብሮ ያልማል።
የዓለም ዋንጫ ከእግር ኳስ ውድድር በላይ ነው፤ ጀግኖች የሚወለዱበት፣ ክብረ ወሰኖች የሚሰበሩበት እና ታሪክ የሚጻፍበት መድረክ ነው።
ውድድሩ ሲጀመር በቢሊዮን የሚቆጠሩ አድናቂዎች የሚጠይቁት አንድ ጥያቄ አለ፦
🏆 የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ማን ያነሳ ይሆን?
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 429 |
| 5 | በመዲናዋ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለአዳዲስ ተሽከርካሪዎች መሰጠት ጀመረ
የአዲስ አበባ ከተማ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲሱን የተሽከርካሪ ሰሌዳ መስጠት መጀመሩን አስታወቀ።
የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘገየ በላይነህ በሰጡት መግለጫ፤ ሰሌዳው የሚሰጠው ለአዳዲስ ተሽከርካሪዎች ብቻ ሲሆን፣ ተመዝግበው ሲጠባበቁ የነበሩ ባለቤቶች በተመዘገቡበት ቅርንጫፍ በኩል በስልክ ጥሪ ተደውሎላቸው መውሰድ እንደሚችሉ ገልጸዋል።
ነባር ሰሌዳ የሚጠቀሙትን በተመለከተ ወደፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በኩል አቅጣጫ እንደሚቀመጥ አመልክተዋል።
@Addis_News
@Addis_News | 438 |
| 6 | MEXC በድንገት የኢትዮጵያን ብር (ETB) ከP2P ላይ አስወገደ።
ዓለም አቀፉ የክሪፕቶ ምንዛሬ መድረክ የሆነው MEXC የኢትዮጵያ ብርን (ETB) ከP2P ሥርዓቱ ላይ ሙሉ በሙሉ በድንገት ማስወገዱ ተረጋገጠ።
ኩባንያው ቀደም ሲል ይህን አገልግሎት የሚያቆመው እ.ኤ.አ. ሰኔ 30 ቀን 2026 መሆኑን ገልጾ የነበረ ቢሆንም ከተቀመጠው ቀነ-ገደብ ሃያ ቀናት ቀድሞ ውሳኔውን በተግባር አውሏል። በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ብር ምርጫ ከፕላትፎርሙ ላይ ሙሉ በሙሉ ጠፍቷል።
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያን የፋይናንስ ህግ መሰረት አድርገው ፦
- ቴሌግራም ዋሌት
- ቢትጌት
- ባይናንስ
- ኦኬኤክስ
- ባይቢት ... የመሳሳሉ መድረኮች በኢትዮጵያን ብር የሚደረጉ የክሪፕቶ ግብይቶች (P2P) ማቆማቸው ይታወሳል።
ብሔራዊ ባንክ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ሥርዓት ያለው የዲጂታል ፋይናንስ ተሳትፎ እንዲኖር የሚያስችል አጠቃላይ የቁጥጥር ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ከዓለም አቀፍ አቻ ተቆጣጣሪዎችና ከአገር ውስጥ ባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ መሆኑን መግለጹም ይታወሳል።
@Addis_News
@Addis_News | 495 |
| 7 | ትራምፕ ለኢራን የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጡ‼️
👉ሆርሙዝ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቷል-ኢራን‼️
#አሜሪካ በኢራን ላይ አዳሯን ከባድ ጥቃት አደረሠች።
# ዋሽንግተን በቶማሃውክ ሚሳኤል ጭምር እስከ #ቴህራን አቅራቢያ ጥቃት ማድረሷን በፕሬዚዳንቷ በኩል ገልፃለች።
#ኢራንም በምላሹ በጆርዳን እና ኩዬት በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ቤዞች ላይ ከ12 በላይ ሚሳይል እና ድሮን በመጠቀም ጥቃት ሰንዝራለች።
በሆርሙዝ ሰርጥም ሁለት መርከቦችን መትቻለሁ” ብላለች።
የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ ኢራን #በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፍ የትኛውም ዓይነት መርከብ አይኖርም ያለችው ሰርጡ ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል ስትል በጦር ቃል አቀባያዋ በኩል ይፋ አድርጋለች።
ኢራን ሆርሙዝ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቧል ካለች በኋላ አለምአቀፍ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ የ 2 ዶላር ጭማሪ አሳይቷል።
የአሜሪካ የቀጠናው ዕዝ ግን የንግድ መርከቦች አሁንም በሆርሙዝ እያለፉ ነው ሲል መግለጫ ሰጥቷል።
አሜሪካ በምሽቱ ጥቃት 49 አቶማሃውክ ሚሳዔሎችን በመጠቀም 18 ኢላማዎችን መምታታቸውን ትራምፕ አሳውቀዋል።
ዛሬ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም ኢራን ወደ ስምምነት ካልመጣች ከምድረ ገፅ ይጠፋሉ ሲሉ ትራምፕ ማስጠንቀቂያ ልከዋል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 554 |
| 8 | የበረራ ፈቃድ ሳይኖረው ለ17 ዓመታት «ኤር ካናዳን» ሲያበር የነበረው ካፒቴን ተያዘ
ረቡዕ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የካናዳ ፖሊስ የ59 ዓመቱ የ«ኤር ካናዳ» ካፒቴን ጄፍሪ ዎል አስፈላጊው የበረራ ፈቃድ ሳይኖረው ለ17 ዓመታት በማጭበርበር በመስራቱ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቋል።
ግለሰቡ ከ2009 እስከ 2025 ባሉት ዓመታት ውስጥ የሀሰት ሰነዶችን በመጠቀም ቦይንግ 767፣ 777 እና 787 አውሮፕላኖችን በመያዝ ከ900 በላይ በረራዎችን የመራ ሲሆን፣ ወደ 3 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ገቢ አግኝቷል።
ኤር ካናዳ ጉዳዩን በጥብቅ እየመረመረው መሆኑን ገልጾ፣ አብራሪዎች በየስድስት ወሩ የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ስለሚያልፉ የመንገደኞች ደህንነት አደጋ ላይ እንዳልወደቀ አስታውቋል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 569 |
| 9 | ብልፅግና ፓርቲ የተወዳደረባቸውን ወንበሮች በሙሉ አሸነፈ
👉 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ወይም የግል ዕጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ምንም መቀመጫ አላሸነፉም።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ከፊል ውጤት እወጃ በስካይ ላይት ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የሌሎች 22 የምርጫ ክልሎችን ውጤት አፅድቆ ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሠረት፣ ከተገለጹት ጠቅላላ 48 የምክር ቤት መቀመጫዎች መካከል ከአንዱ በስተቀር የገዢው ብልፅግና ፓርቲ ዕጩዎች ያሸነፉ ሲሆን፣ የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) ዕጩ ደግሞ በሶማሌ የክልል ምክር ቤት አንድ ወንበር ማሸነፉ ታውቋል። በደገ ሀቡር አንዱን ወንበር የኦጋዴን ግንባር ዕጩ የነበሩት አቶ መሀሙድ ሀሰን ሁሴን አሸንፈዋል።
ለክልል ምክር ቤቶች በጠቅላላው የ12 የክልል ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ውጤቶች ተነግረዋል። የክልል ምክር ቤት ምርጫዎች በየምርጫ ክልሉ ብዙ መቀመጫዎች ያሏቸው በመሆኑ፣ በድምሩ የ38 መቀመጫዎች ውጤት የታወጀ ሲሆን፣ ከነዚህም ውስጥ ብልፅግና ፓርቲ 37ቱን አሸንፏል።
ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠቅላላው የ10 የምርጫ ክልሎች/ወንበሮች ውጤት የተገለጸ ሲሆን (1 ከአማራ፣ 3 ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና 6 ከኦሮሚያ)፣ 10ሩንም መቀመጫዎች በሙሉ የብልፅግና ፓርቲ ዕጩዎች አሸንፈዋል። ውጤታቸው የተገለጹት የምርጫ ክልሎችም በአማራ ክልል ጎዛምን፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ቀዲዳ ጋሜላ 2፣ ጉመር 1 እና እዣ 2 ሲሆኑ፣ በኦሮሚያ ክልል ደግሞ ሀብሮ 1፣ ቅንበቢት፣ ጥቁር እንጭኒ፣ ጀልዱ፣ ወሊሶ 2 እና ወሊሶ 1 የምርጫ ክልሎች ናቸው።
በውጤት እወጃው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ወይም የግል ዕጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ምንም መቀመጫ አላሸነፉም።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 639 |
| 10 | የደቡብ አፍሪካው ስታንቢክ ባንክ በኢትዮጵያ በብቸኝነት በባለቤትነት የሚያስተዳድረውን ራሱን የቻለ ባንክ ለማቋቋም እያሰበ መኾኑ ተሠማ።
ባንኩ ራሱን የቻለ ባንክ ለማቋቋም ያሰበው፣ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ የኢንቨስትመንት ወጪ እየቀነሠና ገቢው እየጨመረ መሄዱን እንደ ጥሩ ምሳሌ በመውሠድ እንደኾነ የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ስታንቢክ ባንክ የግዙፉ የደቡብ አፍሪካ ስታንዳርድ ባንክ አንድ ካል ነው።
ብሄራዊ ባንክ ያወጣው ሕግ፣ በአገር ውስጥ ባንክ የአክሲዮን ድርሻ መግዛት የሚፈልጉ የውጭ ባንኮች ድርሻቸው ከ49 በመቶ እንዳይበልጥ ገደብ ይጥላል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 649 |
| 11 | 'በአዲስ አበባ በጥበቃ ተሰማርተው የነበሩ ሁለት ደረሶች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ታወቀ‼️
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ መጅሊስ በሁለት ደረሶች አሰቃቂ ግድያ ዙሪያ ህብረተሰቡ መግለጫ እስኪሰጥ በትዕግስት እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፏል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 (ሰሚት ጨርቆስ ኮንዶሚኒየም መግቢያ) በጥበቃ ሥራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ ሁለት ደረሶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለው መገኘታቸውን ተከትሎ፣ የክፍለ ከተማው እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት መረጃዎችን አጠናቅሮ መግለጫ እስኪሰጥ ድረስ ህብረተሰቡ በትዕግሥት እንዲጠብቅ አሳሰበ።
ሟቾቹ ሙሐመድ አደም እና ሙሐመድ ዓሊ የተባሉ የጥበቃ ሰራተኞች ሲሆኑ፣ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ በመልካም ስነ-ምግባራቸው የሚታወቁ የዲን ተማሪዎች (ደረሶች) እንደነበሩ ተገልጿል። ከሟቾቹ መካከል ሙሐመድ ዓሊ የልጆች አባት መሆኑም ታውቋል።
ግድያው የተፈፀመው ቅዳሜ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ል ሌሊት እንደሆነ የተገመተ ሲሆን፣ አስክሬናቸው ከሁለት ቀናት በኋላ ሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ል መገኘቱ ተጠቁሟል። ሟቾች የጥበቃ ስራ በሚሰሩበት ስፍራ ምንም ዓይነት የንብረት ስርቆት ወይም የዘረፋ ምልክት አለመገኘቱ የግድያውን አሰቃቂነት አጉልቶታል።
የሟቾች የቀብር ስነ-ስርዓት ትላንት ማክሰኞ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ል በኮልፌ የሙስሊሞች መቃብር ስፍራ ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት ተፈጽሟል። የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በጉዳዩ ዙሪያ ከመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ጠቁሞ፣ መረጃዎችን አጠናቅሮ ዝርዝር መግለጫ እንደሚሰጥ በማስታወቅ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በትዕግሥት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቧል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 865 |
| 12 | የጭቃ ቤት ግንባታ ተከለከለ‼
አሁን ላይ ተፈፃሚ የሆነው በአንድ ክልል ነው በቀጣይ ግን በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንደሚተገበር ተነግሯል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ከተሞችን ለማዘመን እና ከአካባቢ ጥበቃ ጋር የተጣጣመ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት አዲስ ጥብቅ መመሪያ አስተላልፏል።
ደብዳቤው ከደረሰበት ቀን ጀምሮ በማንኛውም ማዘጋጃ ቤት በኩል የጭቃ ቤት ግንባታ ፈቃድ ማጽደቅ ሙሉ በሙሉ ታግዷል።
በእንጨትና ጭቃ ግንባታ ሳቢያ የሚመጣውን የደን መመናመን ለመግታት እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን የድርቅና የጎርፍ አደጋ ለመከላከል ነው።
ማንኛውም ግንባታ ከተማን በሚያዘምኑና ደረጃቸውን በጠበቁ ግብዓቶች ማለትም በብሎኬት፣ በጡብ እና በተሻሻሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ብቻ መከናወን እንዳለበት ታዟል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 863 |
| 13 | ኩዬት ለኢትዮጵያውያን ፈቀደች‼️
ኩዌት ከኢትዮጵያ ጨምሮ ከ10 ሀገራት የቤት ሰራተኞችን ለመቅጠር ፈቀደች።
የኩዌት የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር የቤት ሰራተኞች ቅጥርን የሚቆጣጠር አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ዘገባ አመላከተ።
በአዲሱ መመሪያ መሰረት ኩዌት ከኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጨምሮ ከ10 ሀገራት የቤት ሰራተኞችን (ወንድም ሴትም) ለመቅጠር ፈቅዳለች።
የተፈቀደላቸው ቀሪዎቹ ሀገራት ደቡብ አፍሪካ፣ ቤኒን፣ ፊሊፒንስ፣ ስሪላንካ፣ ሕንድ፣ ቪየትናም፣ ኔፓል እና ሴኔጋል (ለወንዶች ብቻ) ናቸው።
የቅጥር ሂደቱን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግም ማመልከቻዎች በየግዛቱ በሚገኙ የአገልግሎት ማዕከላት በኩል እንደሚስተናገዱ የሀገሪቱ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
@Tekus_Info
@Tekus_Info | 892 |
| 14 | በኦሮሚያ ክልል ፤ አርሲ ውስጥ በጥቃት አድራሾች የተቃጠለው ቤተክርስቲያን ሊሠራ ነው ተባለ!
«በአርሲ የተቃጠለውን ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን መልሰን እንሠራለን።» -የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከአንድ ሳምንት በፊት ስለተፈጸመው የኦርቶዶክሳውያን ግድያና የቤተ ክርስቲያን መቃጠል ኃዘናቸውን በመግለጥ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ፈቃደኛ መሆናቸውን ማሳወቃቸው ተዘግቧል ።
በኦሮሚያ ክልል፤ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በኢትዮጵያ አገር አቀፍ ምርጫ ቀን እና በዋዜማው ግንቦት 23 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በተፈጸመው ጥቃት ንጹሐን ምእመናን መገደላቸው ተዘግቧል ። ከተፈጸመው ግድያ በተጨማሪ ከመቶ ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እንደተቃጠለ ይታወሳል።
@Addis_News
@Addis_News | 1 033 |
| 15 | "የሰራኸው ታሪክ በምንም አይቀየርም"- ዶ/ር ቴድሮስ
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖም፣ በዓለም ዋንጫው ታሪክ የመጀመሪያው ሶማሊያዊ ዳኛ በመሆን ታሪክ ለሰራው ኦማር አርታን ያላቸውን ጥልቅ አጋርነት እና ድጋፍ ገለጹ።
ዳኛው በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዚህ ትልቅ መድረክ ቢመረጥም፣ በዓለም ዋንጫው ሜዳ ላይ ጨዋታዎችን እንዳይመራ መደረጉን (ከሜዳ መገለሉን) ተከትሎ ነው ዶ/ር ቴድሮስ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ የማጽናኛ መልዕክት ያስተላለፉት።
ዶ/ር ቴድሮስ በመልዕክታቸው "ኦማር አርታን የዓለም ዋንጫውን በመቀላቀል ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ ምርጥ እና የመጀመሪያው ሶማሊያዊ ዳኛ በመሆን ትልቅ ታሪክ ሰርቷል፤ ይህ ስኬቱ ደግሞ በምንም አይቀየርም" ብለዋል።
አክለውም ዳኛው የሙያው ማማ ላይ መድረሱ እና ሀገሩን ወክሎ መገኘቱ ብቻውን በትውልድ ሀገሩ ላሉ ወጣቶች ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑን ገልጸው፤ ባገኘው እና ይገባው በነበረው የዓለም ዋንጫ ሜዳ ላይ እንዳይገኝ መደረጉ እጅግ እንዳሳዘናቸው አመልክተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ይህ ክስተት በዓለም አቀፍ መድረክ የዳኛው የመጨረሻ ታሪክ እንደማይሆን በማስመር፣ "ዓለም እንደ አንድ ቤተሰብ ከጎንህ ቆሟል፤ አሁን ላይ ጥንካሬን እመኝልሃለሁ፣ በቀጣይም በሌሎች በርካታ ታላላቅ የፍጻሜ መድረኮች ላይ እንደምንመለከትህ ተስፋ አደርጋለሁ" በማለት ከሶማሊያዊው ዳኛ ጎን መቆማቸውን አረጋግጠዋል።
@Addis_News
@Addis_News | 1 015 |
| 16 | ከ3 ጊዜ በላይ ጥቆማ የሚቀርብባቸውና ከታሪፍ በላይ የሚጭኑ አሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ።
ከነዳጅ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ አጠቃላይ ሁኔታውን ታሳቢ ያደረገ የታሪፍ ማሻሻያ ቢደረግም፣ በርካታ አሽከርካሪዎች ከተቀመጠው ታሪፍ ውጪ እያስከፈሉ መሆኑ በጥናት መረጋገጡን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ለመናኸሪያ ሬዲዮ በሰጠው ገለፃ አስታውቋል።
በመዲናዋ የሚገኙ የሚኒባስ አሽከርካሪዎች ከታሪፍ ውጪ ከማስከፈልም ባለፈ፣ ከተሰጣቸው ስምሪት ውጪ እንደሚያሽከረክሩ የተናገሩት የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው፤ ይህንን ችግር ለመፍታት ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ችግሩን ለመፍታት ካሁን ቀደም በኪሎ ሜትር ይገለጽ የነበረው የጉዞ ታሪፍ ተሳፋሪውን ያወዛግብ እንደነበር አስታውሰው፤ በተያዘው ሰኔ ወር በመነሻና መዳረሻ ላይ ያለውን የጉዞ ታሪፍ የሚገልጽ ዝርዝር እንደሚለጠፍ አስታውቀዋል።
ቢሮው ከታሪፍ በላይ በሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎች ላይ የሚሰራውን የቁጥጥር ስራ በይበልጥ ማሻሻሉን ገልጸው፤ ከ3 ጊዜ በላይ ጥቆማ የሚቀርብባቸውና ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ እንደሚደረግም ተናግረዋል።
ባለፈው የግንቦት ወር ብቻ ከታሪፍ በላይ በማስከፈልና የተቀመጠውን የታሪፍ ዝርዝር ባለመስቀላቸው ከ3 ሺህ 300 በላይ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ያመለከቱት ምክትል ኃላፊው፤ የቁጥጥር ስራውን በይበልጥ ለማጠናከር በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ባለፉት ጊዜያት በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው 9417 አጭር የስልክ መስመር አሁን ላይ በርካታ ጥቆማዎችን እየተቀበለበት መሆኑን አቶ ዳኛቸው ገልጸዋል። በተጠናቀቀው ግንቦት ወር ብቻ ወደ 400 የሚጠጉ ጥቆማዎችን ማስተናገድ መቻሉንና በ300ዎቹ ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው አብራርተዋል።
@Addis_News
@Addis_News | 873 |
| 17 | ኢራን ለአሜሪካ ጥቃት አጸፋ ለመመለስ በባህሬን ኩዌት እና ጆርዳን ላይ ጥቃት ሰነዘረች
አሜሪካ የአንድ ሄሊኮፕተር መውደቅን ተከትሎ በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ በሚገኙ የኢራን ወደቦች ላይ ጥቃት መሰንዘሯን ተከትሎ፣ የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ኃይል በባህሬን፣ ኩዌት እና ጆርዳን በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ የድሮንና የረጅም ርቀት ሚሳይል የአጸፋ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
ኢራን በአጠቃላይ 21 የአሜሪካ ኢላማዎችን ማጥቃቷንና በጆርዳን የሚገኝ የF-35 ተዋጊ ጀት ማቆሚያን ጨምሮ አራቱን ማውደሟን እንዲሁም አንድ የአሜሪካ ድሮን መትታ መጣሏን የገለጸች ሲሆን፣ ከአሜሪካ ወገን ግን እስካሁን የተሰጠ ፈጣን አስተያየት የለም።
ይህንን ጥቃት ተከትሎ በባህሬን እና ኩዌት የአየር ጥቃት ሳይረን የተሰማ ሲሆን፣ የጆርዳን ጦር ደግሞ ከኢራን የተተኮሱ አምስት ሚሳይሎችን ያለ ምንም ጉዳት መትቶ ማክሸፉን አስታውቋል።
የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት የኢራን ፈጣን ምላሽ አሜሪካ ያለምንም ቅጣት ጥቃት እንዳትሰነዝር ለመግታት የታለመ አዲስ መመሪያን የሚያሳይ ቢሆንም፣ በተደጋጋሚ ክስተቶች ምክንያት በሁለቱም ወገኖች መካከል ስምምነት ላይ ለመድረስ ያለው እምነት እየቀነሰ መጥቷል ብለዋል።
ይህ አዲስ የጥቃት ዙር የዓለምን ኢኮኖሚ ካናጋውና የነዳጅ እንዲሁም የምግብ ዋጋን ካናረው የኢራንና እስራኤል ከባድ የተኩስ ልውውጥ ማግስት የተከሰተ ሲሆን፣ የእስራኤል በሊባኖስ በሄዝቦላህ ላይ የምታካሂደው ዘመቻ ደግሞ የሰላም ሂደቱን ይበልጥ አዝጋሚ አድርጎታል።
ምንም እንኳን የቅርብ ጊዜ ጥቃቶች ቢኖሩም ሁለቱም ወገኖች ወደ ሙሉ ጦርነት መመለስ አይፈልጉም፤ ነገር ግን ወደ ድርድር ለመመለስ ያላቸው ፍላጎት በአሜሪካ ላይ ባላቸው እምነት ማነስ ምክንያት ተገቷል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል።
@Addis_News
@Addis_News | 837 |
| 18 | የቻይናው ፕሬዝዳንት ሰሜን ኮሪያን መጎብኘታቸውን ተከትሎ ሁለቱ ሀገራት ከሉዓላዊነት መከበር እስከ ኢኮኖሚ ትብብር የሚዘልቅ አጋርነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ በሰሜን ኮሪያ ፒዮንግያንግ ባደረጉት ጉብኝት፣ ከሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን ጋር በመሆን ስልታዊ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማሳደግ ቃል ገብተዋል። በፒዮንግያንግ በተካሄደው በዚህ ጉባኤ መሪዎቹ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጥበቅ የተስማሙ ሲሆን፣ ሰሜን ኮሪያ ታይዋን፣ የቻይና ጠቅላላ የግዛት አካል መሆኗን በድጋሚ አረጋግጣለች።
የሰሜን ኮሪያ ብሔራዊ የዜና አገልግሎት እንደዘገበው፤ ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። መሪዎቹ ይበልጥ የተቀራረበ ስልታዊ ግንኙነት ለመፍጠር በተስማሙበት ወቅት ኪም ጆንግ ኡን በበኩላቸው፤ ከቻይና ጋር ያለውን ወዳጅነት ማስቀጠል ለሰሜን ኮሪያ “ከሁሉም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ስልታዊ ተግባር” መሆኑን ገልጸዋል።
ኪም ጆንግ ኡን ፕሬዝዳንት ሺን “የላቀ የሀገር እንግዳ” በማለት የጠሯቸው ሲሆን፣ ሺ እ.አ.አ. 2026 የመጀመሪያ የውጭ ሀገር ጉዟቸውን ወደ ሰሜን ኮሪያ ማድረጋቸው ለሀገራቸው የተደረገ “ትልቅ ድጋፍ” መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ፒዮንግያንግ ቤጂንግ ለምትከተለው “አንድ ቻይና መርህ” እና ታይዋን የቻይና የማይነጠል አካል ናት ለሚለው አቋም ያላትን ጽኑ ድጋፍ በድጋሚ ገልጻለች።
በሌላ በኩል የቻይናው ብሔራዊ ቴሌቪዥን እንደዘገበው፤ ቻይና በንግድ፣ በግብርና፣ በኮንስትራክሽን እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ጭምር ከሰሜን ኮሪያ ጋር ያላትን ትብብር ለማስፋፋት ፍላጎት እንዳላት ፕሬዝዳንት ሺ አስታውቀዋል።
ይህ የቻይናው ፕሬዝዳንት የሰሜን ኮሪያ ጉብኝት ከሰባት ዓመታት በኋላ የተደረገ የመጀመሪያው ሲሆን፣ የሁለቱን ሀገራት የወዳጅነት ስምምነት 65ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ግንኙነታቸው “አዲስ ታሪካዊ መነሻ” ላይ መድረሱን መሪዎቹ በጋራ አውጀዋል።
ሰሜን ኮሪያ ከሩሲያ ጋር ያላት ወታደራዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እያደገ ቢመጣም፣ ለህልውናዋ ግን አሁንም በዋናነት በቻይና ላይ ጥገኛ መሆኗን ስለምታውቅ ከቤጂንግ ጋር ያላትን ትስስር ማጠናከር እንደምትፈልግ የፖለቲካ ተንታኞች ያነሳሉ።
ቻይናም በበኩሏ በስትራቴጂካዊ መልኩ ወሳኝ በሆነችው ሰሜን ኮሪያ ላይ ያላትን ተፅዕኖ በድጋሚ ለማረጋገጥ እና ከአሜሪካ ጋር ለምታደርገው ዓለም አቀፋዊ ፉክክር ይህንን ግንኙነት ይበልጥ ተጽዕኖ ለማሳደር እየተጠቀመችበት እንደሆነ ባለሙያዎች ይገመግማሉ።
@Addis_News
@Addis_News | 839 |
| 19 | በኢቦላ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከመቶ በላይ ደረሰ
በምሥራቃዊ ኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ መከሰቱ በይፋ ከታወጀ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሟቾች ቁጥር ከአንድ መቶ ማለፉ ተዘግቧል።
ይህ የሟቾች ቁጥር የተመዘገበው፣ በሽታው ከተቀሰቀሰ ከሳምንታት በኋላ ዘግይቶ መገኘቱን ተከትሎ ስርጭቱን ለመግታት የሚደረገው ጥረት በተጠናከረበት ወቅት ነው ሲል ኤፒ ዘግቧል።
በግንቦት ወር ይፋ በተደረገው የኢቦላ ወረርሽኝ ላይ የሚደረገውን የቁጥጥር ሥራ፤ በአካባቢው ታጣቂዎች የሚፈጸሙ ጥቃቶች፣ ከተወሰኑ ነዋሪዎች ያላቸው ጥርጣሬ እንዲሁም በግጭት ቀጠናዎች ውስጥ ያለው የጸጥታ እንቅፋት ተግዳሮት መሆናቸውን ቀጥለዋል ተብሏል።
እስከ እሁድ ዕለት ድረስ በበሽታው መያዛቸው ከተረጋገጠ 550 ሕሙማን መካከል የ101 ሰዎች ሕይወት ማለፉ የተገለጸ ሲሆን፣ 19 ያህሉ ደግሞ ከበሽታው ማገገማቸውን ትላንት የወጣው ሪፖርት አመልክቷል።
የወረርሽኙ ስርጭት በኮንጎ ምሥራቃዊ ግዛት በምትገኘው ኢቱሪ ላይ የበረታ ሲሆን፣ ይህችው ግዛት ብቻዋን ከአጠቃላይ ታካሚዎች ከ90 በመቶ በላይ የሚሆነውን ትይዛለች።
ከዚህ በተጨማሪም ወረርሽኙ በሰሜን ኪቩ እና በደቡብ ኪቩ ግዛቶች የተመዘገበ ሲሆን፣ የድንበር መስመርን ተሻግሮ ወደ ጎረቤት አገር ኡጋንዳም መሰራጨቱ መረጋገጡን ዘገባው አመልክቷል።
@Addis_News
@Addis_News | 853 |
| 20 | ዩናይትድስቴትስ ኢራንን ደበደበች።
"AH-64 አፓቼ" የአሜሪካ ሄሊኮፕተር መከስከሱን ተከትሎ ዋሽንግተን በቴህራን ላይ የአጸፋ እርምጃ መውሰዷን አስታውቃለች።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሆርሙዝ ሰርጥ ለተከሰከሰው የአሜሪካ ሄሊኮፕተር ኢራንን ተጠያቂ አድርገዋል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ በጥቃቱ ባንዳር አባስ እና ቃሸም ከተሞች ኢላማ መደረጋቸውን ገልጿል።
ሴንትኮም የአየር መከላከያ እና ራዳሮችን አውድሚያለሁ ብሏል።
via_outbreak
@Addis_News
@Addis_News | 883 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
