fa
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

رفتن به کانال در Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

نمایش بیشتر
3 303
مشترکین
-224 ساعت
-107 روز
-3830 روز
آرشیو پست ها
ድርሳነ ማርያም ......እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከታቦተ ጽዮን ጋር ያላትን የትርጕምና የምሥጢር አንድነት በዝርዝር ያስረዳል፡፡ የእመቤታችንን የትውልድ ሐረግ፣ አስተዳደግ፤ በአዳም አካል
ድርሳነ ማርያም ......እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከታቦተ ጽዮን ጋር ያላትን የትርጕምና የምሥጢር አንድነት በዝርዝር ያስረዳል፡፡ የእመቤታችንን የትውልድ ሐረግ፣ አስተዳደግ፤ በአዳም አካል ስታበራ የነበረች ዕንቊ መሆኗን /ከጥንተ አብሶ ነጻ መሆኗን/፤ በቤተ መቅደስ ስለደረሰባት ፈተና፤ ለዮሴፍ የመሰጠቷ ምሥጢር፤ ክርስቶስን ስለመፅነሷ ስለ ክርስቶስ ማንነት፣ ግብፅ ስትሰደድ ስለገጠማት ሰቆቃና ስለአደረገችው ተአምራት፤ ቅዱሳን ሐዋርያት ለእመቤታችን ስለአቀረቡት ምስጋና፤ ስለዘካርያስ ሞት፤ ስለ ኤልሳቤጥና ዮሐንስ መሠወር፤ ክርስቶስ ስለተቀበለው መከራ፤ ስለ ድንግል ማርያም መራራ ኀዘን፤ አባታችን ያዕቆብ ስለ ዮሴፍ፣ ድንግል ማርያም ስለ ክርስቶስ ያለቀሱትን ልቅሶ በንጽጽር ያስነብበናል፡፡ በሦስት ድንጋዮች የቤተ ክርስቲያን መሠራትና የሐዋርያትን መሰባሰብ ያስረዳናል፡፡ ...በዚህ.. ድርሳንም ለምእመናን ለአጠቃቀም እንዲመቻቸው በማሰብ በወራት ተከፋፍሎ የቀረበ ሲሆን እንደሌሎቹ ድርሳናት ሁሉ ምእመናንና አቢያተ ክርስቲያናት በየወሩ መተቀመጠው መሠረት እመቤታችንን የሚመለከቱ ጉዳዮች እንዲቀርቡበት ተደርጓል ፡፡ አንባብያንም ለጸሎት ከመጠቀም ባሻገር በየወራቶቹ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ተያይዞ በቤተ ክርስቲያናችን ያሉትን አስተምህሮዎች እንዲያውቁበት ያደርጋል። በማለት በሊቃውንት ተመርምሮ የቀረበ ይህን ድርሳን በግዮን መጽሐፍት ያገኙታል።   https://t.me/GhionBookStore1623

“በዚህ መጽሐፍ ለማድረግ የሞከርኩት አበው (አባቶቻችን) ያቆዩልንን የባሕረ ሐሳብ ትምህርት በትውልዳችን ቋንቋ ማቅረብ ሲሆን ዓላማዬ ለማንም የአራት መደብ የቍጥር ትምህርት ለተማረ ሰው (ከልሂቅ እስ
“በዚህ መጽሐፍ ለማድረግ የሞከርኩት አበው (አባቶቻችን) ያቆዩልንን የባሕረ ሐሳብ ትምህርት በትውልዳችን ቋንቋ ማቅረብ ሲሆን  ዓላማዬ ለማንም የአራት መደብ የቍጥር ትምህርት ለተማረ ሰው (ከልሂቅ እስከ ደቂቅ) ባሕረ ሐሳብ የማውጣት ችሎታን ማስተማር ነው” (ገጽ 14)። “የዛሬው ትውልድ ታሪክ ሲጠቅስ ብዙ ጊዜ ከአፄ ቴዎድሮስ ወደኋላ ሲሄድ ስለማልሰማ ከመጻሕፍቱ ጋራ በመስማማት ከሳቸው በፊት ያሉትን ዘመናት ለማስተዋወቅ ብዙ ገጾች ወስጃለሁ። አፄ  ተከታዮቻቸው ቴዎድሮስና ነገሥታት ኢትዮጵያን ከወደቀችበት እናንሣ ሲሉ አገራችን ያሸበረቀችበትና የወደቀችበት ዘመን ነበረ ማለታቸው ነው” (ገጽ 229)።   “በምዕራፍ ፭ የተመዘገበው በዓውደ ሰማዕ(ታ)ት መጀመሪያ ጀምሮ በዓመተ ምሕረት (ዓ.ም.) እና በዓመተ እግዚእ (A.D.) መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሳየው (ሠንጠረዥ) ( በኛ ዘመንቈጠራዎች የተመዘገበን የታሪክ ድርጊት ወደ እነሱ የዘመን ቈጠራ (ወደ ዓመተ እግዚእ A.D.)፣ በነሱ (በዓመተ እግዚእ) የዘመን ቈጠራ የተመዘገበን  የታሪክ ድርጊት ወደኛ (ወደ ዓመተ ቈጠራ ምሕረት) የዘመን ለማዞር ነው” (ገጽ 17)። ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ይህን  መጽሐፍ በግዮን መጽሐፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። t.me/GhionBookstore1623

❞#ይህ የዲያቆን ታደሰ ወርቁ “ጽዋዔ" የተሰኘውን መጽሐፍ በርካታ ታዳሚ ፅንሰ ሐሳባት የታደሙበት ታላቅ የእልፍኝ አዳራሽ ይመስላል፡፡ መጽሐፉን ለማዘጋጀት በርካታና ጠቃሚ ዋቤ፣ ማጣቀሻ መጻሕፍትን መጠቀሙን ከመጽሐፉ የኅዳግ ክፍል ውስጥ መረዳት እንችላለን፡፡ የመጽሐፉም ዝግጅት በዋቤ መጻሕፍት ላይ ብቻ የተደገፈ የዕውቀትና የምርምር ጽሑፍ ብቻ ሳይሆን የአንባብያንን ኅሊና የሚሞግትና በሰው የአኗኗር ዘይቤ ውስጥ የማኀበራዊ ፍትሕ ፅንሰ ሐሳብ ምን መምሰል እንዳለበት የሚያስገነዝብ ኃይል ያለው ነው፡፡ መጽሐፉ የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን የትውልድ ዘመን፣ የፍልስፍናና የሥነ መለኮት ትምህርት፣ የሥነ ልቦና ውቅር፣ ስለሰው ያለው ጥልቅ ፍቅር፤ እንዲሁም ለነፍሳት የሚያሳየው ፍጹም ርኅራኄ፣ በአንጾኪያ የነበረው የክህነት አገልግሎትና አስተምህሮ፣ በማኅበራዊ እኩልነትና በምጣኔ ሀብት ፍትሐዊ ክፍፍልነት ላይ ያለው ሙግት በጥልቀት የሚያነሣ በመሆኑ፤ መጽሐፉን አነበብኩት ብቻ ሳይሆን አጠናሁት ለማለት እችላለሁ፡፡ አንባብያንም ሆንን በዚህ ዘመን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተለያየ የሥራ ዘርፍ የምንገኝ ሁሉ ስለ ማኅበራዊ ፍትሕ ፅንሰ ሐሳብ በይበልጥ የምንማርበት ስለሆነ ሁሉም ሰው መጽሐፉን አንብቦ እንዲጠቀምበት ግብዣዬ ነው፡፡ አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ (ዶ/ር) በአሜሪካን ሀገር በትምህርት አገልግሎት ተቋም ውስጥ የትምህርት ሥራ ባለሙያና ተመራማሪ "ጽዋዔ" በሚል ርእስ የተጻፈው የዲያቆን ታደሰ ወርቁ መጽሐፍ፣ ቃለ እግዚአብሔርን በሚገርም ጸጋ በማስተማርና በመስበክ የሚታወቀውን የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን ጥሪ እና አገልግሎት ድንቅ በሆነ መልኩ ያስቃኘናል፡፡ ሰዎች መስማት የሚፈልጉትን ሳይሆን፣ በቅዱሳት መጻሕፍት የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ በእውነትና በኃይል በመስበክ፣ በሀብታቸው የሚመኩ ባለጸጎችን እየገሠጸ፣ ለድኾች ጥብቅና በመቆም ዮሐንስ አፈ ወርቅን የሚያክል አባት እስካሁን አልተነሣም፡፡ ዲያቆን ታዴ የዚህን ኦርቶዶክሳዊ ቅዱስ አባት ጥሪና እስከ ሊቀ ጵጵስና የደረሰ አገልግሎት፣ ከታሪክ ጸሐፊዎቹ ከእነ ሶቅራጥስ፣ ፓላዲየስ፣ አውሳብዮስ ዘቂሣርያ ወዘተ... አንደበት የሰማ እስኪመስል ድረስ ተነብቦ በማይጠገብ ሥነ ጽሑፍ (የአጻጻፍ ውበት) አቅርቦልናል፡፡ የታሪኩ ፍሰት፣ በየገጹ የሚታዩት ማራኪ ንኡሳን አርእስት እና የተወሳሰበው ታሪክ ተብራርቶ የቀረበበት መንገድ መጽሐፉን ተወዳጅም ያደርገዋል፡፡ ይህ መጽሐፍ በዋነኝነት ለነገረ መለኮት (theology) ተማሪዎችና መምህራን፣ ለሰባክያን፣ እንዲሁም ለሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች የቤተ ክርስቲያናቸው ታሪክ አካል የሆነውን የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን ሕይወት አጽንኦት ሰጥተው እንዲያጠኑት በማድረግ ታላቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ ራሳቸውን ልሂቃን (elites) አድርገው የሚቆጥሩ ወገኖቻችንም የተሰጣቸውን ሓላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ከዚህ መጽሐፍ ብዙ የሚማሩት ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡ ቀሲስ መብራቱ ኪሮስ (ዶ/ር) የቀድሞ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ዋና ዲን እና የ“አኰቴተ ቊርባን“ መጽሐፍ ደራሲ ጽዋዔን ሳነብ ሀገሬ ትዝ አለችኝ፡፡ከአንድ ሺሕ ስምንት መቶ ዓመት በፊት አንጾኪያና አንጾኪያውያን የገቡበትን ሁለንተናዊ አረንቋ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ዛሬ ገብተንበታል፡፡ በርግጥም ከልብ አንብቦ ለተረዳው ለትንሣኤያችን መነሻ አሳብ አበርካች መጥሐፍ ነው። የጳጳሳቱ፣ የካህናቱ፣ የምእመናኑ፣ የመለካውያኑን ጠባያት በገሐድ ያሳያል። ኢትዮጵያውያን ከአዚማችን ከአልነቃን እንደ አንጾኪያ የሰዓታት ሳይሆን የዓመታት ዐመፅ አይቀሬ መሆኑን ያመላክታል፡፡ ሀገሬ ዛሬም ዮሐንስ አፈ ወርቅን ታስሳለች፡፡ ዘረኝነት፣ ክፋት፣ ምቀኝነት፣ መጠፋፋት፣ አሳልፎ መሰጣጣት ሁሉ በሚከወንባት ሀገሬ ከመጥፋቷ፤ እኛም ከመጥፋታችን በፊት መድኃኒት የሚሆን መጽሐፍ ነው፡፡ የታዴ የቃላት አመራረጡ፣ ክብደቱና አዋሐዱ የዐሥራ አምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የሀገሬን ጠሐፍት አባቶቸን አስታወሰኝ፡፡ የቃላት ድርቅ ለመታንና በአማርኛ ጽሑፎቻችን እንግሊዝኛ ቃላትን ለምናዘወትረው “ተመየጡ ሀበ ዘቀዳሚ ፊደልክሙ" ይለናል። መጽሐፉን ብዙ ተመራምሮ አጣቅሶ የጣፈው እንደሆነ ከኅዳጎቹና ከጥቅሶቹ መረዳት ይቻላል፡፡ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኛ ብዙኅን አገልግሎት ሥርጭት ድርጀት ዋና ሥራ አስኪያጅ ታላቁ አባት ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ አንጾኪያ በነበረበት ወቅት የአደረጋቸው ነገሮችና የአስተማራቸው ትምህርቶች ቤተ ክርስቲያን እና ሀገር በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ላይ በሚሆኑበት ጊዜ ሕዝብን እንዴት ማገልገልና አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ማሻገር እንደሚቻል በተግባር ያስተምሩናል፡፡ ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ሰፊ ጥናትና ዳሰሳ በማድረግ የአዘጋጀው ይኽ መጽሐፍ፤ በቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ የአንጾኪያ የተጋድሎ ሕይወት አንጻር ካህናት ሕዝባቸውን በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ እንዴት መምራትና ማሻገር እንደሚገባቸው ያሳየናል፡፡ ተግባራዊ ትምህርት የሚሰጥ የሆነውን ይህን መጽሐፍ በመጻፉም ሊመሰገን ይገባዋል፡፡ መምህር ያረጋል አበጋዝ ጸሐፊና ሰባኬ ወንጌል

✞  ጥር 4 የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ዓመታዊ በዓል የወንጌላዊ ዮሐንስ ድንቅ ታሪክን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለዮሐንስ በደረሰለት ውዳሴ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ኮከብን ብለን ጠራንህ፤ የጽድቅ ፀሓይ ያሳደገህ ባጠገቡ (በጉያውም) ያስቀመጠህ ኮከብን ብለን ጠራንህ፤ በአፉ የሳመኽ በመታጠቂያውም ያስታጠቀኽ ኮከብን ብለን ጠራንኽ፤ የተሰወረውን ምስጢር ያሳየኽ የጸጋውን ወንጌል የሰጠኽ ኮከብን ብለን ጠራንኽ፤ ዮሐንስ እንዳንተ ያለ ማን ነው ታማልደን ዘንድ ማለድንኽ። √ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በዚህ ክፍል ላይ ተጋድሎው ሕይወቱ እንደ ኮከብ የደመቀውን ዮሐንስን አመስግኖታል፤ ይህ ዮሐንስ ቊጥሩ ከ12ቱ ሐዋርያት መካከል ሆኖ የዘብዴዎስ እና የሰሎሜ ልጅ ሲሆን በእኛ ትውፊት እናቱን ማርያም ባውፍልያ ይላታል። √ ጌታችን ያዕቆብንና ወንድሙን ዮሐንስን ከአባታቸው ከዘብዴዎስ ጋር በታንኳ መረባቸውን ሲያበጁ ዐየ፤ ጠራቸውም እነርሱም ወዲያው ታንኳይቱንና አባታቸውን ትተው ተከትለውታል። [ማቴ. 4፥21-22] √ ጌታም ኹለቱን ወንድማማቾችን ቦአኔርጌስ ብሏቸዋል፤ ትርጓሜውም የነጐድጓድ ልጆች ማለት ነው። [ማር. 3፥17] √ ጌታችን ምስጢረ መንግሥትን ለመግለጽ ወደ ታቦር ተራራ ይዞት ወጥቷል፤ በጌቴሴማኒም ምስጢረ ጸሎትን ሲያሳይ ከጌታ ጋር ነበርና "የምስጢር ሐዋርያ" ይባላል። √ ጌታችን ይወድደው የነበረው ደቀ መዝሙር ርሱ ነውና "ፍቁረ እግዚእ" (የጌታ ወዳጅ) ሲባል በምሴተ ኀሙስም ምስጢረ ቊርባንን ሲመሠርት ከጐኑ የተጠቀመጠው ርሱ ዮሐንስ ነበርና ሊቁ “የጽድቅ ፀሓይ ያሳደገኽ ባጠገቡ ያስቀመጠኽ” ብሎታል፡፡ √ ጌታችን ሲጠራው የ25 ዓመት ወጣት እንደ ነበር ሄሬኔዎስ የተባለ ደቀ መዝሙሩ ጽፏል፡፡ √ ቅዱስ ጳውሎስ “Pillars of the Church- አዕማደ ቤተክርስቲያን” ብሎ ከሚጠራቸው ሐዋርያት አንዱ ዮሐንስ ነው። [ገላ. 2፥9] [ሊቁ ዮሐንስ አፈ ወርቅና አውግስጢኖስ ስለ ዮሐንስ ሲመሰክሩ] √ “ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን እስከ መስቀል ድረስ የተከተለ ብቸኛ ሐዋርያ ነውና ጌታም ዮሐንስ ካሳየው ፍቅር ከ100 (መቶ) ዕጥፍ በላይ እናቱን እናት አድርጎ ሰጠው፡፡ ምንኛ የታደለ ሐዋርያ ነው” ይላሉ፡፡ [ዮሐ. 19፥20-27] √ ጌታችን በጸሎተ ኀሙስ ለደቀ መዝሙርቱ ትሕትናን ሊያስተምር ከእራት በኋላ ተነሥቶ ልብሱን አኑሮ “ወነሥአ መክፌ ዘለንጽ ወቀነተ ሐቌሁ” ይላል ዘርፍ ያላት ዝናር አንሥቶ ወገቡን ታጠቀ ሥራ የምታሠራ የምታስጌጥ ስትኾን ኢዮአብ ወደ ሰልፍ ሲገባ እየለበሳት ይገባ እንደነበረች ያለች ናት፤ ልብሰ መንድያ ይላታል በሺሕ ዘሓ (ድር) የተሠራች ናት። √ “ወወደየ ማየ ውስተ ንብቲራ ወአኀዘ ይሕጽብ እገሪሆሙ ለአርዳኢሁ ወመዝመዘ በውእቱ መክፌ ዘቀነተ” በመታጠቢያው ውሃ ጨመረ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ ይላል። √ ይህቺ የታጠቀበትን ለዮሐንስ ወንጌላዊ ሰጥቶት ጌታ በታጠቀበት ቢታጠቅ ሕገ ሥጋ ጠፍቶለታል ፍቁረ እግዚእ ያሰኘው ይኽ ነውና ሊቁ “በመታጠቂውም ያስታጠቀኽ” በማለት አመስግኗል፡፡ √ “በአፉ የሳመኽ” ማለቱ የሮሙ ንጉሥ ጢባርዮስ ቄሳር የጌታን ነገር አይሁድ በግፍ ጠልተው ተመቅኝተው ሰቅለውት እንደሞተ እንደተነሣ እንዳረገ ሰምቶ የጌታዬን እናት ማን ባመጣልኝ እኔ ቋሚ ለጓሚ፤ ሚስቴ ገረድ ደንገጥር በኾንላት ብሎ ተመኘ፤ ተመኝቶም አልቀረ “ወለአከ ኢየሩሳሌም ሰራዊተ ወሐራ ወአዋልደ ብዙኃተ ወኅጽዋነ” ይላል ወደ ኢየሩሳሌም ብዙ ደንገጥሮች ሰራዊትና ጭፍራ እንደዚሁም የሴት ደናግልና ባለሟሎችን በክብር አጅበው ያመጧት ዘንድ ላከ። √ ጌታም የእናቱን ተድላ ነፍስ እንጂ ተድላ ሥጋን አይሻምና እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም መንግሥት ክብር የሚበልጥና የሚያስደንቅ የጌትነቴን ክብር ታዪ ዘንድ በጎ ዕረፍት ወዳለበት ወደ ሰማይ አሳርግሽ ዘንድ ተነሥተሸ ቁሚ አላት፤ ከዚያም ወደ ገነት አግብቶ በገነት ላሉ ነፍሳት መድኀኒታችኊ እነኋት ርሷን አመስግኑ ብሏቸው አመስግነዋታል፡፡ በእርሱም ሐዘን እንዳይጸናበት ዮሐንስ ወንጌላዊን ላከለት ከዚያም ንጉሡን ስለ ጌታችን ሥጋዌ አስተማረው፤ ንጉሡም የሚቻልህም ከሆነ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ እንዳየኸው ሥዕሉን ሥለህ አሳየኝ አለው፤ ዮሐንስም ንጉሥ ሆይ እሺ በርሱ ላይ የተፈጸመውን ሁሉ ሥዬ አሳይሆለኊ አለው፤ ከዚያም ዮሐንስ በዕለተ ዐርብ ጌታን እንደሰቀሉት አድርጎ ሣለው። ብፁዕ ዮሐንስም የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥዕል ሠርቶ ከፈጸመ በኋላ ራሱን ወደታች ዝቅ አድርጎ የሕያው እግዚአብሔርን ልጅ ሥዕል ተሳለመ፤ በዚችም ዕለት የዚሆ ሥዕል ከናፍር ከብፁዕ ዮሐንስ ከናፍር ጋር ለብዙ ሰዓት ተያይዞ ቆየ ይህም ጽንዐ ፍቅራቸውን ለማጠየቅ ነው፡፡ በዚያን ጊዜ የመድኅን ጌታ ሥዕል ንጉሥና በዚያም የቆሙ ሁሉ እያንዳዳንዳቸው እየሰሙት ወዳጄ ዮሐንስ ዮሐንስ እያለ ድምፅ አሰምቷልና ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ይኽነን ተናገረ፡፡ [ሊቁ አባ ጊዮርጊስ በዚኽ መጽሐፉ ላይ] የተሰወረውን ምስጢር ያሳየኽ የጸጋውን ወንጌል የሰጠኽ ኮከብን ብለን ጠራንኽ በማለት ለዮሐንስ የተገለጸለትን ሰማያዊ ምስጢር ተናግሯል። ይኸውም ቅዱስ ዮሐንስ ንጽሐ ሥጋ፣ ንጽሐ ነፍስ፣ ንጽሐ ልቡና ተሰጥቶት ሰማያዊ የአንድነት የሦስትነት ምስጢር ተገልጾለት። “በመጀመሪያው ቃል ነበረ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ” እያለ ወንጌሉን ሲጽፍ መልአኩ ከውቅያኖስ አስኳሉ በወጣለት እንቊላል እየቀዳ ውሃውን ሲያፈስስ ዐየው። ዮሐንስም በአድናቆት ሆኖ “ምን ያደርግልኻል” ብሎ መልአኩን ጠየቀው፤ “ይህንን ውሃ በዚኽ እየቀዳኊ አፍስሼ ለማድረቅ ነው” አለው፤ ዮሐንስም “ያልቅልኻልን” አለው፤ መልአኩም “ይኽስ ፍጡር ነው ቁም ነገር የለውም ይፈጸማል፤ አንተስ የማይፈጸመውን ባሕርየ እግዚአብሔርን እፈጽማለኊ ብለኽ ጀምረህ የለም” አለው፤ ያን ጊዜ ዮሐንስ “ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ” በማለት ወንጌሉን መጻፍ ጀምሯል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ከወንጌል በተጨማሪ ሦስት መልእክታትን ሲጽፍ፤ በ98 ዓ.ም በፍጥሞ ደሴት ሳለ የዓለም ፍጻሜ ነገር ተገልጾለት ራእዩን ከጻፈ በኋላ ጥር 4 እንደተሰወረ ይነገራል፤ የቅዱስ ዮሐንስ በረከት በዝቶ ይደርብን፡፡ ማጣቀሻ መጽሐፈ ሰዓታት ንባቡና ትርጓሜው ከመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ

✞  ጥር 4 የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ዓመታዊ በዓል የወንጌላዊ ዮሐንስ ድንቅ ታሪክን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለዮሐንስ በደረሰለት ውዳሴ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ኮከብን ብለን ጠራንህ፤ የጽድቅ ፀሓይ ያሳደገህ ባጠገቡ (በጉያውም) ያስቀመጠህ ኮከብን ብለን ጠራንህ፤ በአፉ የሳመኽ በመታጠቂያውም ያስታጠቀኽ ኮከብን ብለን ጠራንኽ፤ የተሰወረውን ምስጢር ያሳየኽ የጸጋውን ወንጌል የሰጠኽ ኮከብን ብለን ጠራንኽ፤ ዮሐንስ እንዳንተ ያለ ማን ነው ታማልደን ዘንድ ማለድንኽ። √ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በዚህ ክፍል ላይ ተጋድሎው ሕይወቱ እንደ ኮከብ የደመቀውን ዮሐንስን አመስግኖታል፤ ይህ ዮሐንስ ቊጥሩ ከ12ቱ ሐዋርያት መካከል ሆኖ የዘብዴዎስ እና የሰሎሜ ልጅ ሲሆን በእኛ ትውፊት እናቱን ማርያም ባውፍልያ ይላታል። √ ጌታችን ያዕቆብንና ወንድሙን ዮሐንስን ከአባታቸው ከዘብዴዎስ ጋር በታንኳ መረባቸውን ሲያበጁ ዐየ፤ ጠራቸውም እነርሱም ወዲያው ታንኳይቱንና አባታቸውን ትተው ተከትለውታል። [ማቴ. 4፥21-22] √ ጌታም ኹለቱን ወንድማማቾችን ቦአኔርጌስ ብሏቸዋል፤ ትርጓሜውም የነጐድጓድ ልጆች ማለት ነው። [ማር. 3፥17] √ ጌታችን ምስጢረ መንግሥትን ለመግለጽ ወደ ታቦር ተራራ ይዞት ወጥቷል፤ በጌቴሴማኒም ምስጢረ ጸሎትን ሲያሳይ ከጌታ ጋር ነበርና "የምስጢር ሐዋርያ" ይባላል። √ ጌታችን ይወድደው የነበረው ደቀ መዝሙር ርሱ ነውና "ፍቁረ እግዚእ" (የጌታ ወዳጅ) ሲባል በምሴተ ኀሙስም ምስጢረ ቊርባንን ሲመሠርት ከጐኑ የተጠቀመጠው ርሱ ዮሐንስ ነበርና ሊቁ “የጽድቅ ፀሓይ ያሳደገኽ ባጠገቡ ያስቀመጠኽ” ብሎታል፡፡ √ ጌታችን ሲጠራው የ25 ዓመት ወጣት እንደ ነበር ሄሬኔዎስ የተባለ ደቀ መዝሙሩ ጽፏል፡፡ √ ቅዱስ ጳውሎስ “Pillars of the Church- አዕማደ ቤተክርስቲያን” ብሎ ከሚጠራቸው ሐዋርያት አንዱ ዮሐንስ ነው። [ገላ. 2፥9] [ሊቁ ዮሐንስ አፈ ወርቅና አውግስጢኖስ ስለ ዮሐንስ ሲመሰክሩ] √ “ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን እስከ መስቀል ድረስ የተከተለ ብቸኛ ሐዋርያ ነውና ጌታም ዮሐንስ ካሳየው ፍቅር ከ100 (መቶ) ዕጥፍ በላይ እናቱን እናት አድርጎ ሰጠው፡፡ ምንኛ የታደለ ሐዋርያ ነው” ይላሉ፡፡ [ዮሐ. 19፥20-27] √ ጌታችን በጸሎተ ኀሙስ ለደቀ መዝሙርቱ ትሕትናን ሊያስተምር ከእራት በኋላ ተነሥቶ ልብሱን አኑሮ “ወነሥአ መክፌ ዘለንጽ ወቀነተ ሐቌሁ” ይላል ዘርፍ ያላት ዝናር አንሥቶ ወገቡን ታጠቀ ሥራ የምታሠራ የምታስጌጥ ስትኾን ኢዮአብ ወደ ሰልፍ ሲገባ እየለበሳት ይገባ እንደነበረች ያለች ናት፤ ልብሰ መንድያ ይላታል በሺሕ ዘሓ (ድር) የተሠራች ናት። √ “ወወደየ ማየ ውስተ ንብቲራ ወአኀዘ ይሕጽብ እገሪሆሙ ለአርዳኢሁ ወመዝመዘ በውእቱ መክፌ ዘቀነተ” በመታጠቢያው ውሃ ጨመረ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ ይላል። √ ይህቺ የታጠቀበትን ለዮሐንስ ወንጌላዊ ሰጥቶት ጌታ በታጠቀበት ቢታጠቅ ሕገ ሥጋ ጠፍቶለታል ፍቁረ እግዚእ ያሰኘው ይኽ ነውና ሊቁ “በመታጠቂውም ያስታጠቀኽ” በማለት አመስግኗል፡፡ √ “በአፉ የሳመኽ” ማለቱ የሮሙ ንጉሥ ጢባርዮስ ቄሳር የጌታን ነገር አይሁድ በግፍ ጠልተው ተመቅኝተው ሰቅለውት እንደሞተ እንደተነሣ እንዳረገ ሰምቶ የጌታዬን እናት ማን ባመጣልኝ እኔ ቋሚ ለጓሚ፤ ሚስቴ ገረድ ደንገጥር በኾንላት ብሎ ተመኘ፤ ተመኝቶም አልቀረ “ወለአከ ኢየሩሳሌም ሰራዊተ ወሐራ ወአዋልደ ብዙኃተ ወኅጽዋነ” ይላል ወደ ኢየሩሳሌም ብዙ ደንገጥሮች ሰራዊትና ጭፍራ እንደዚሁም የሴት ደናግልና ባለሟሎችን በክብር አጅበው ያመጧት ዘንድ ላከ። √ ጌታም የእናቱን ተድላ ነፍስ እንጂ ተድላ ሥጋን አይሻምና እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም መንግሥት ክብር የሚበልጥና የሚያስደንቅ የጌትነቴን ክብር ታዪ ዘንድ በጎ ዕረፍት ወዳለበት ወደ ሰማይ አሳርግሽ ዘንድ ተነሥተሸ ቁሚ አላት፤ ከዚያም ወደ ገነት አግብቶ በገነት ላሉ ነፍሳት መድኀኒታችኊ እነኋት ርሷን አመስግኑ ብሏቸው አመስግነዋታል፡፡ በእርሱም ሐዘን እንዳይጸናበት ዮሐንስ ወንጌላዊን ላከለት ከዚያም ንጉሡን ስለ ጌታችን ሥጋዌ አስተማረው፤ ንጉሡም የሚቻልህም ከሆነ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ እንዳየኸው ሥዕሉን ሥለህ አሳየኝ አለው፤ ዮሐንስም ንጉሥ ሆይ እሺ በርሱ ላይ የተፈጸመውን ሁሉ ሥዬ አሳይሆለኊ አለው፤ ከዚያም ዮሐንስ በዕለተ ዐርብ ጌታን እንደሰቀሉት አድርጎ ሣለው። ብፁዕ ዮሐንስም የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥዕል ሠርቶ ከፈጸመ በኋላ ራሱን ወደታች ዝቅ አድርጎ የሕያው እግዚአብሔርን ልጅ ሥዕል ተሳለመ፤ በዚችም ዕለት የዚሆ ሥዕል ከናፍር ከብፁዕ ዮሐንስ ከናፍር ጋር ለብዙ ሰዓት ተያይዞ ቆየ ይህም ጽንዐ ፍቅራቸውን ለማጠየቅ ነው፡፡ በዚያን ጊዜ የመድኅን ጌታ ሥዕል ንጉሥና በዚያም የቆሙ ሁሉ እያንዳዳንዳቸው እየሰሙት ወዳጄ ዮሐንስ ዮሐንስ እያለ ድምፅ አሰምቷልና ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ይኽነን ተናገረ፡፡ [ሊቁ አባ ጊዮርጊስ በዚኽ መጽሐፉ ላይ] የተሰወረውን ምስጢር ያሳየኽ የጸጋውን ወንጌል የሰጠኽ ኮከብን ብለን ጠራንኽ በማለት ለዮሐንስ የተገለጸለትን ሰማያዊ ምስጢር ተናግሯል። ይኸውም ቅዱስ ዮሐንስ ንጽሐ ሥጋ፣ ንጽሐ ነፍስ፣ ንጽሐ ልቡና ተሰጥቶት ሰማያዊ የአንድነት የሦስትነት ምስጢር ተገልጾለት። “በመጀመሪያው ቃል ነበረ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ” እያለ ወንጌሉን ሲጽፍ መልአኩ ከውቅያኖስ አስኳሉ በወጣለት እንቊላል እየቀዳ ውሃውን ሲያፈስስ ዐየው። ዮሐንስም በአድናቆት ሆኖ “ምን ያደርግልኻል” ብሎ መልአኩን ጠየቀው፤ “ይህንን ውሃ በዚኽ እየቀዳኊ አፍስሼ ለማድረቅ ነው” አለው፤ ዮሐንስም “ያልቅልኻልን” አለው፤ መልአኩም “ይኽስ ፍጡር ነው ቁም ነገር የለውም ይፈጸማል፤ አንተስ የማይፈጸመውን ባሕርየ እግዚአብሔርን እፈጽማለኊ ብለኽ ጀምረህ የለም” አለው፤ ያን ጊዜ ዮሐንስ “ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ” በማለት ወንጌሉን መጻፍ ጀምሯል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ከወንጌል በተጨማሪ ሦስት መልእክታትን ሲጽፍ፤ በ98 ዓ.ም በፍጥሞ ደሴት ሳለ የዓለም ፍጻሜ ነገር ተገልጾለት ራእዩን ከጻፈ በኋላ ጥር 4 እንደተሰወረ ይነገራል፤ የቅዱስ ዮሐንስ በረከት በዝቶ ይደርብን፡፡ ማጣቀሻ መጽሐፈ ሰዓታት ንባቡና ትርጓሜው ከመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ

           በዓለ ጌና(የገና ባህል) የገና በዓል እና ባህል በሀገራችን እጅግ የተከበረ ቅዱስ በዓል ነው።ትቂት ስለ ገና ባህል እንመልከት፦ [  ] ፩.ገን፣ገነት፡- ማለት ተክል የተክል የፍሬ ቦታ (ገነት)ማለት ነው(ቃሉ የዕብራይስጥ ነው) በዚህ ትርጉም በዓለ ጌና ማለት በገነት የተመሰለችው የእመቤታችን እና በፍሬ የተመሰለው የጌታ በዓል ማለት ነው።እመቤታችንን በገነት ተክል ጌታን በገነት ፍሬ መስሎ መናገር በመጻሕፍት ዘንድ የተለመደ  ነውና። [  ] ፪.በዓለ ጌና ማለት፡-የእመቤቲቱ በዓል ማለት ነው በዳውሮኛ ልሳን እመቤታንን የሚገልጽ ቃል ነው።በዳውሮ ልሳን እመቤታችን ለማለት ጌና በማለት ይጠራል። [  ] ፫.በዓለ ጌና ማለት ፡-በለ አምኃ ፣በዓለ አምልኮ ማለት ነው። ከሰብአ ሰገል ጋር ባለው ታሪክ መሠረት ሦስቱ ነገሥታት ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤ ለክርስቶስ ከመገበራቸው ጋራ የተዛመደ ነው። [  ] ፬.በዐለ ገንህ፡-ሁሉ ወደ እርሱ የሚጮህለት፣ሁሉ  የሚገዛለት የጌታ በዓል ማለት። በበዓሉ ዕለትም ንጉሥ ሳይቀር ከዙፋኑ ወርዶ የሚጫወትበት በዓል ማለት ነው።(በገና ጫወታ አይቆጡም ጌታ)የሚባለው ሁሉ እኩል በትህትና ስሊሚጫወቱ ነው።        የገና ጫወታ እና አጀማምሩ በትውፊት፦ [  ] ፩.የገና ጭወት አጀማምሩ መልአክ ለኖሎት የልደትን ብሥራት ሲነግራቸው በደስታ ወደ ቤተ ልሔም ሲሄዱ ኳስ ኳስ የመሰለ የብርሃን ጥንግ ያገኙ ነበር። ያንን ከደስታቸው ብዛት የተነሣ እየሞጩ እየቀሉ ወደ ቤተ ልሔም ሂደዋል። [  ] ፪.ከሄሮድስ ሠራዊት አንዱ እሩህ የሚባለው ሰው ተሠውሮ መዳረሻቸውን ለማወቅና ጌታቸውን ንጉሣቸውን ለመግደል ለሥለላ መጥቶ ነበር። በዚህ ምክንያት ባዕድ ሲገባባቸው ይመራቸው የነበረው ብርሃን ሲሠወራቸው ተፈላልገው ለይተው ገርፈውታል በዚያ ልማድ የዕሩህ ጭዎት ተጀምሯል። [  ] ፫.የአዳምን ነፍስ እስከ ክርስቶስ ቀዳማዊ ምጽአት ድረስ አጋንንት አበድነው በመንጸፈ ደይን ጥለው በእግራቸው ጠቅጥቀው መከራ አጽንተውባት ነበር። በዚያ ምሳሌ ዛሬም ከወዲያ ወዲህ እሩር በመጫወት ይገልጹታል። [  ] ፬.መላእክት ሰይፈ እሳት በትረ እሳት ይዘው ለልደት ፳፬ ቀን ሲቀር ጀምረው ዓውደ ቤተ ልሔምን ሲጠብቁ ያሳዩት የነበረው ግብር ነው። በዚህ ጊዜ ዲያብሎስ ወደ ቤተ ልሔም ሲቀርብ ቅዱሳን መላእክት በሀጸ እሳት በበትረ እሳት እየሞጩ እየቀሉ አባረውታልና በዚያ ምሳሌ የገና ጫወታ ይካሄዳል። [  ] ፭.ኖሎት ከብት እየጠበቁ እሩር ከሚበትጫወቱ ቦታ መላእክት  ዮም ተወልደ ብለዋቸዋልና በዚያ ትውፊት እስከ ዛሬ ድረስ የገና ጭዎት የተወቀ በዓል ነው። ፮.ዕሩር የአዳም ነፍስ ምሳሌ ናት።ያሸነፉ ገነኞች እየዘመሩ ወደ መንደራቸው ይዘዋት ይሄዳሉ።የመንደሩ ሰውም ድግስ ደግሶ እልል እያለ ይቀበላቸዋለል። ይሄውም የጠፋውን በግ አዳምን ጌታችን ከዲያብሎስ ቀምቶ በሄደ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት እየዘመሩ የቀብለውታልና በዚያ ምሳሌ። የገና ጭወት ንጉሥ ከነ ሠራዊቱ፣ምስለኔ ከነ መኳንንቱ፣ዓለቃ ከነ ካህናቱ የሚጫወትበት በዓል ነው። ምክንያቱም በንጉሥ ክርስቶስ ልደት፡-ሰማያውያን መላእክት.ምድራውያን ኖሎት፣ሦስቱ ነገሥታት አንድ ሁነው ተባብረው ያከበሩት በዓል ስለሆነ በመካከል ሁሉም ክብሩን ለቆ ዝቅ ብሎ በገናው ቦታ በመገኘት ትህትናውን ይገልጻል። ዕለቱ ዕለተ ምርያ፣ዕለተ ሣህል፣ዕለተ ምህረት፣ዕለተ ድኅነት፣ዕለተ ፍጻሜ ተስፋ፣ዕለተ ትህትና ስለሆነች ቁጣ ጠብ የሌለው በዓል ነው።በበዓሉ ጌታችን፣እመቤታችን፣ዮሴፍ ሰሎሜ፣መላእክት፣ኖሎት፣ሰብአ ሰገል ይታሰቡበታል።የነገሥታት ጫወታ የሆነው ለዚህ ነው፡፡                     ከና ጫዎታ መልስ፦ [  ] ፩.ገናውን ሰዎች ተጫውተው ጨርሰው ወደ መንደር ሲደርሱ ሰው ሁሉ በደስታ በድግስ ይቀበላቸዋል።ይሄውም የሚጠተ ሰብአ ሰገል መገለጫ ነው። ሰብአ ሠገል ሰግደው ሲመለሱ ሰው ሁሉ በእልልታ በደስታ ስለተቀበላቸው ነው። [  ] ፪.ሚጠተ ኖሎት ነው።ኖሎት እነሆ እውነትም ተወልዷል በጎል ተጥሎ በጨርቅ ተጠቅልሎ በገግዕዘ ሕፃናት ሳያለቅስ ሲያነጥስ አየነው ሰማነው እያሉ በደስታ ለመመለሳቸው ምሳሌ ነው። ፫.አምላካችን ሰው ሁኖ አዳምን ከጨለማ ወደ ብርሃን ከሞት ወደ ሕይወት በመለሰው ጊዜ መላእክት ደስ እያላቸው ስለተቀበሉት ነው። [  ] ፬.በነጋው ወተት ያለው ሁሉ ዱቄት እና ወተት ሜዳ ከትልቅ ዛፍ ሥር ከብቶች እና እረኞች ባሉበት የወተት ገንፎ ተዘጋጅቶ የተገኘው ሁሉ ይመገባል። ምክንያቱም እመቤታችን ለመጠየቅ ኖሎት ከላሞቻቸው ወተት፣ ከስንቃቸው ዱቄት አምጥተው መግበው፣ተመግበው ስለነበር በዚያ ልማድ ነው፡፡ዛሬም በዚያ ልማድ አንዲት ሴት ስትወልድ ቀድሚያ ወተትና ገንፎ የሚያቀርቡላት ለዚያ መሠረት ነው።                የገና ስጦታ፦ ፩.የገና ሥጦታ (ጋዳ) ይባላል፡-ሦስቱ ነገሥታት ወርቅ፣ዕጣን፣ከርቤ ያበረከቱለትን መሠረት አድርጎ ያንን በማሰብ የሚተገበር ነው። ፪.ይልቁንም የሀገራችን ቀደም ብላ ንግሥተ ሳባ ለንጉሥ ሰሎሞን፤ንጉሥ ባዚን እና ሊቀ ካህናት ዮአኪን ለጌታችን  ያቀረቡትን አምኃ። የሚያትት ነው ፫.ኖሎት ወተት እና ዱቄት ለእመቤታችን አቅርበውላት ስለነበር  በዚያ ምሳሌ ነው። ፬.መላእክት የምስጋና ግብር ለጌታችው አቅርበው ነበር በዚያ  አርአያ የሚሆን ነው። [  ] ፭. እመቤታችን ሰብአ ሰገል ስንቅ ቢያልቅባቸው"ወአስነቀቶሙ ህብስተ ሰገም-የገብስ እንጎቻ ሰጠቻቸው"ይላል እና በዚያ አርአያ ነው ነው የገና ሥጦታ የሚበረከተው። ፮.ራሱ ቃል በሥጋ ለሰው ልጅ መሰጠቱን ለማሰብ ጭምር ነው የምናበረክተው፡፡ይህም አብ አንድያ ልጁን ልጁን ለሕማም ለሞት አሳልፎ ስለሰጠልን ያንን በማሰብ የሚከናዎን ነው።.. [  ] በዓላትን ስናከብር ከእነ ዕሤቱ፣ከነ ታሪኩ፣ከነ ምሥጢሩ፣ከነ ክብሩ ሊሆን ይገባል።ባዕድ ከሆኑ የባህል ከረራዎች ራሳችንን እንጠብቅ።ይህ ባህል ሕይወታችን እንጂ  ምናብ አይደለም። አንድ ሃይማኖት ሲኖሩት ባህል ለትውልድ ሲያቀብሉት ትዉፊት ይባላል፡፡ ባህል እና ትውፊት የሌለው ሃይማኖት ወደ ሕይወት ዘልቆ መግባት ያልቻለ ትምህርት ነው። ባህል የማይጨበጥ ቅርስ አይደለም የዕለት ከዕለት ሕይወት ነው እንጂ፡፡ ባህል ትናንትን ለዘሬ ዛሬን ለትናንት የሚያቀብል የሕይወት መምህር ነው።

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በደኅና አደረስዎ! በዓለ ልደት ለሰው ልጆች ሁሉ ሰላምና ፍቅርን ያሰፈነ፣ የትኅትና አባት ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም በበረት የተወለደበት አንክ
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በደኅና አደረስዎ! በዓለ ልደት ለሰው ልጆች ሁሉ ሰላምና ፍቅርን ያሰፈነ፣ የትኅትና አባት ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም በበረት የተወለደበት አንክሮ የሚገባው በዓል ነው፡፡በዓሉ የሰላም ፣የፍቅርና የመተሳሰብ ይሁንልን!

#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሐቲ ድንግል 4ኛ ግዜ ታትማለች በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ። እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢዎች በDh
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሐቲ ድንግል 4ኛ ግዜ ታትማለች በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ። እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢዎች በDhl እና በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት መጽሐፍትን እንልካለን ይዘዙን። አድራሻ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ። t.me/GhionBookStore1623

#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሐቲ ድንግል 4ኛ ግዜ ታትማለች በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ። እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢዎች በDh
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሐቲ ድንግል 4ኛ ግዜ ታትማለች በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ። እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢዎች በDhl እና በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት መጽሐፍትን እንልካለን ይዘዙን። አድራሻ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ። t.me/GhionBookStore1623

#ዜና_መጽሐፍ #ርእስ፦ ሐተታ ዘቅዱስ አትናቴዎስ- ተስእሎተ አንትያኮስ #ይዘት፦ ቅዱስ አትናቴዎስ በዘመኑ የተለያዩ መጻሕፍትን አዘጋጅቷል፡፡ ከሥራዎቹ አንዱ አንትያኮስ የሚባል መኰንን ለጠየቀው ጥያቄ
#ዜና_መጽሐፍ #ርእስ፦ ሐተታ ዘቅዱስ አትናቴዎስ- ተስእሎተ አንትያኮስ #ይዘት፦ ቅዱስ አትናቴዎስ በዘመኑ የተለያዩ መጻሕፍትን አዘጋጅቷል፡፡ ከሥራዎቹ አንዱ አንትያኮስ የሚባል መኰንን ለጠየቀው ጥያቄ መልስ የሰጠበት ይህ “ተስእሎቶ አንትያኮስ" የተባለ መጽሐፍ ነው፡፡ የመኰንኑ ጥያቄና የሊቁ መልስ በሁለት ክፍል የተከፈለ ነው፡፡ የመጀመሪያው ክፍል ሰባ ስምንት ጥያቄዎችንና መልሶቻቸውን የያዘ ሲሆን የሁለተኛው ክፍል ደግሞ አርባ ጥያቄዎችንና መልሶቻቸውን ይዟል፡፡ መጽሐፉ በድምሩ በሊቁ የተመለሱ የ118 ጥያቄዎች መልሶችን ይዟል ፡፡ በእነዚህ ጥያቄዎች ውስጥ ሥነ ፍጥረት፣ ነገረ መለኮት፣ ሥርየተ ኃጢአት፣ ልዩ ልዩ የምግባር ሥራዎችና ሌሎችም ጥያቄዎች ተካተውበታል፡፡ አብዛኞቹ በዚያ ዘመን የነበሩ መናፍቃን ኑፋቄዎች ለመሆናቸው የጥያቄዎች መንፈስ ያስረዳል። #የገጽ_ብዛት፦ 180 #የሽፋን_ዋጋው፦ 290 ብር ___   ያልደረሳችሁ እያለቀ ስለሆ የተዎሰነ ቅጅዎች አለን ከግዮን ቅናሽ ጋር እንጠብቅዎታለን - ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ።

በግዮን መጻሕፍት ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ።እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢዮቻችን በተለያዩ አማራጮች መጽሐፍትን እንልካለን ይዘዙን። አድራሻ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ። t.me/GhionBookStore1623

በግዮን መጻሕፍት ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ።አድራሻ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ። t.me/GhionBookStore1623

#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት "ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚ
#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት "ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚነት ያለው መጽሐፍ ይህ መጽሐፍ መሆኑ በስፋት የተነገረለት ነው፡፡ እስከ ዛሬ ወደ እኛ ባለመምጣቱ የቀረብንን ይኸው ዛሬ መጽሐፉ ተተርጉሞ በመቅረቡ አንድ ጉድለት ተሸፍኗል፡፡ መጽሐፉ የክርስትና ሕይወትን ምንነት በአግባቡ ለመረዳትና ለመኖር በሚሹ ዘንድ ሁሉ የሚፈለግና የሚጠቅም መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ በተለይ ደግሞ እግዚአብሔር አምላካቸውን በገዳማዊ ሕይወት ለሚያገለግሉ ጠቀሜታው እጅግ የጎላ ነው፡፡"             ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ይህ ለረጅም ጊዜ ከገበያ ጠፍቶ የነበረውና ግሩም የሆነ መጽሐፍ አሁን በድጋሚ ታትሞ  ለገበያ ቀርቧል። በግዮን መጻሕፍት መደብርም ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።

#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት "ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚ
#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት "ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚነት ያለው መጽሐፍ ይህ መጽሐፍ መሆኑ በስፋት የተነገረለት ነው፡፡ እስከ ዛሬ ወደ እኛ ባለመምጣቱ የቀረብንን ይኸው ዛሬ መጽሐፉ ተተርጉሞ በመቅረቡ አንድ ጉድለት ተሸፍኗል፡፡ መጽሐፉ የክርስትና ሕይወትን ምንነት በአግባቡ ለመረዳትና ለመኖር በሚሹ ዘንድ ሁሉ የሚፈለግና የሚጠቅም መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ በተለይ ደግሞ እግዚአብሔር አምላካቸውን በገዳማዊ ሕይወት ለሚያገለግሉ ጠቀሜታው እጅግ የጎላ ነው፡፡"             ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ይህ ለረጅም ጊዜ ከገበያ ጠፍቶ የነበረውና ግሩም የሆነ መጽሐፍ አሁን በድጋሚ ታትሞ ለገበያ ቀርቧል። በግዮን መጻሕፍት መደብርም ታገኙታላችሁ።

#የመላእክት-ተልእኮ-በሰው-መዳን ያለው ድርሻ!!! """""""""""""""""""""""""""""""""""""""" #እግዚአብሔር መላእክትን ሲፈጥራቸው #ለሦስት ጉዳዮች ነው፦ #አንደኛ፦የባሕርይ ክብሩን በፀጋ እንዲሳተፉ ነው፡፡ #ሁለተኛ፦ሁልጊዜም እርሱን ያለ እረፍት እንዲያመሰገኑ ነው፡፡ #ሦስተኛ ለሰው ልጅና ለፍጥረታት ሁሉ ጥበቃ ነው፡፡ #ዛሬ የመልአኩ የቅ/ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል ከመሆኑም አንጻር የሰውን ልጅ ጠብቆት እናያለን፡፡ #እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ይሁን ብሎ በልዑል ሥልጣኑ እንደፈጠረው በይሁንታ መጠበቅ ይችላል፡፡ "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና" ሉቃ1፥37፡፡ #ነገር ግን እግዚአብሔር የባሕርይ ጠብቆቱን መላእክት በጸጋ እንዲሣተፉትና የሰውን ልጅ እንዲጠብቁት አድርጓል፡፡የሰው ልጅ አማኒም ይሁን መናፍቅ ደግም ይሁን ክፉ ጻድቅም ይሁን ኀጥእ በመላእክት ጠብቆት ውስጥ ጸንቶ የሚኖር ነው፡፡የሰው ልጅ አይ እኔ ኦርቶዶክስ ስላልሆንኩ የመላእክት ጠብቆት አያስፈልገኝም ሊል አይችልም፡፡ምክንያቱም የእግዚአብሔር መግቦት በሁሉም ፍጥረት ላይ ስለሆነ ነው፡፡ "በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ:የሚረግሟችሁንም መርቁ ለሚጠሏችሁም መልካም አድርጉ: ስለሚያሳድዷችሁም ጸልዩ:እርሱ በክፉዎችና በበጎዎች ላይ ፀሓይን ያወጣልና:በጻድቃንና በኀጢአተኛዎችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና። የሚወዷ፟ችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?:: ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ?አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?፡፡እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተ ፍጹማን ሁኑ" ማቴ. 5:45-48 #እግዚአብሔር ለፍጡራን የሚያደርጋቸው መግቦታቱ በሙሉ የሚከናወኑ በመላእክት ተልእኮ ነው፦ ዝናሙ፣ደመናው፣ጠሉ፣ፀሐይ፣ጨረቃ፣ከዋክብት፣ነፋሳት፣መባርቅት፣ነጎድጓት...እነዚህ ሁሉ የሚመግቡን በመላእክት ተልእኮና ሥልጣን ነው፡፡ስለዚህ ዓለም በእኒዚህ መግቦት እስካለ ድረስ መላእክትን አይጠብቁኝም ማለት እኔ ከእግዚአብሔር ጠብቆትና መግቦት እልፍም ሲል በእራሴ ዓለምነት ነው የምኖር ያሰኛል፡፡ "መላእክተ ገጽንም የሚያመሰግኑ መላእክትንም በእሳት አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም በጨለማና በብርሃን አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም በውርጭና በበረድ አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም፡፡በውኃ ላይ በመብረቅና በነጐድጓድ ላይ የተሾሙ መላእክትንም በነፋሳት ላይ የተሾሙ መላእከተን በቁርና በውርጭ በመጾውና በክረምት በበጋና በጸደይ በምድርና በሰማይ ባሉ ነፋሳት ሁሉ ላይ የተሾሙ መላእክትን በወንዙ ሁሉ በብርሃንና በጨለማ እግዚአብሔር በባሕርይ እውቀቱ ባዘጋጃቸው በምሽትና በመንጋት ላይ የተሾሙ መላእክትን ፈጥሮአልና። የፍጥረትን ነገር ሁሉ ጻፍ ብሎ ነገረው። ኩፋ.2፥6-7:: "ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ዑርኤል በመብረቅ በነጐድጓድ የተሾመ ነው።በሰው ቁስል የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሩፋኤል ነው፡፡ ዲያብሎስን የሚበቀለው አጋንንትንም የሚበቀላቸው ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ራጉኤል ነው።ለሰው ባደረገው በጎነት ላይ ለሕዝቡ ታዛዥ ነውና ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሚካኤል ነው።በባቦች ላይ በገነትም ባሉ ጻድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ገብርኤል ነው። ሄኖ.6:2-7:: "አንዱም አንዱም በየወገናቸው እንዳሉ አንዱም አንዱ በየዘመናቸውና በየሥልጣናቸው አንዱም አንዱም በየመውጫቸውና በየስማቸው ከኔ ጋራ ያለ መሪያቸው የሚሆን የከበረ መልአኩ ዑርኤል ባሳየኝ በየወራታቸውም ጸንተው እንዲኖሩ የሚናገር መጽሐፍ ይህ ነው። ሄኖ.21:2:: #ስለዚህ መላእክት ለሰው ልጅ በሁለተናው የሚጠብቁት ናቸው፦ ከእሳት ሲገባ አብረው ገብተው አድነውታል፡፡ከአንበሳ አፍ አድነውታል፡፡ባሕር ከፍለውለታል፡፡ከጠላት ጋር ተዋግውለታል፡፡ትንቢት ተናግረውለታል፡፡ራዕዮችን ሕልሞችን ተርጉመውለታል፡፡የክርስቶስን ሰው መሆን አብሥረውታል፡፡የክርስቶስን ልደት አብሥረውታል፡፡በጎል አብረውት አመስገነዋል፡፡በሥደት አብረው ተሰደዋል፡፡ሚጠቱን ነግረውታል፡፡በገዳም አገልገለውታል፡፡ትንሳኤውን እርገቱን አብሥረውታል፡፡ዳግም ምጽአቱን ነግረውታል፡፡ከእስርቤት አውጥተውታል፡፡ከሰይፍ አድነውታል፡፡ አጠቃላይ መላእክት ለሰው ልጅ ለደስታውም ለመከራውም በዓለ ወጎች ናቸው፡፡ስለዚህ ሰው ከመላእክት ጠብቆት መራቅ ፈጽሞ አይችለም፡፡ "ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን??" ዕብ.1:14:: "ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፡፡ መላእክታቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁና" ማቴ.18:10፡፡ "በዚያም ዘመን ስለሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል:ሕዝብም ከሆነ ዠምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል:በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል" ትን.ዳን.12:1:: "እንሆም:የጌታ መልአክ ቀረበ በቤትም ውስጥ ብርሃን በራ:ጴጥሮስንም ጐድኑን መቶ፟ አነቃውና ፦ ፈጥነህ ተነሣ አለው።ሰንሰለቶቹም ከእጁ ወደቁ። መልአኩም፦ታጠቅና ጫማህን አግባ አለው፡ እንዲሁም አደረገ" ሐዋ.12:7-8:: #የክርስቶስ ሰው መሆን መጸነስ፣መወለድ፡መሠደድ፡መጠመቅ ማስተማር፣ሕግ መሥራት፣መሰቀል፣መሞት፣መቀበር፡መነሳት ማረግ፣ዳግም፡መምጣት ለሰው ልጅ እንደሆነ ሁሉ የመላእክትም ጥበቃ ለሁሉም ፍጥረት ነው፡፡ ስለዚህ ከመላእክት ጠብቆት ፈጽሞ መውጣት አይቻልምና የመላእክት በዓል ማክበር ለክርስትና ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ በሙሉ ነው፡፡ ✞ ቅዱስ ገብር እንደ ሠለስቱ ደቂቅ እኛንም ከሦስት ነገር ይጠበቀን፦ ☞ ዳያብሎስ!!! ☞ ስስእት!!! ☞ ኃጢአት!!! ☞ ፍቀረ ንዋይ!!! ☞ ፍዳ ሞት!!! ☞ ትእቢት!!! ❖እናመልከው ዘንድ ለፈጠረን እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው እንላለን!!!              ❖አ.ዘ.ያዕቆብ፡፡             © ጌዴዎን ዘለዓለም፡፡

#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሁኑ ጊዜ ‹‹ሃይማኖት እንጂ ሥርዓት አያድንም! በሚል ፈሊጥ እምነቱን ፍጻሜ የሚሰጠውና በሥራ የሚያስተረገመው ሥርዓትና ቀኖና በምን አለበት» አዘናጊ ብሂል ፈተና ሲገጥመው ይታያ
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሁኑ ጊዜ ‹‹ሃይማኖት እንጂ ሥርዓት አያድንም! በሚል ፈሊጥ እምነቱን ፍጻሜ የሚሰጠውና በሥራ የሚያስተረገመው ሥርዓትና ቀኖና በምን አለበት» አዘናጊ ብሂል ፈተና ሲገጥመው ይታያል፡፡ እውነታው እንዲህ እንዳልሆነና በእንዴት ያሉ ደጋግ አበው፣ በመቼ ጊዜና ቦታ፣ በምን ምክንያትና ምን ዐላማን ለማሳካት እንደ ተጻፈ በዚህ መጽሐፍ እንረዳለን፡፡ መጽሐፉ ብሔራውያን ምንጮች ከውጭ ቅጂዎች በማስተናበር የተጻፈ በመሆኑ የቤተ ክርስቲያናችንን ያልተፋለሰና ያልተቋረጠ የእምነትና የሥርዓተ አምልኮ ጥንታዊነት በውስጥም በአፍአም ማስረጃ ያረጋግጥልናል። እያንዳንዱ ጉባኤ የተደረገበትን፣ የእያንዳንዱን ጉባኤ አናቅጽ ይዘት፣ የድንጋጌያቸውን ምክንያት፣ በጉባኤያቱ የነበሩ ተሳታፊዎችን ማንነትና ከጉባኤው በኋላ የነበረውን የአፈጻጸም ሁኔታ፣ በጉባኤው ሂደትና አፈጻጸም ያጋጠመውን ፈተና፣ የጉባኤያቱ ዓይነት፣ ያነጋገሩትን ጭብጦች፡ ያላስማሙትን ቁልፍ ቃላትና ሌሎችም ተያያዥ ሃይማኖታውያንና ታሪካውያን ሁነቶች መጥኖ አቅርቧል፡፡ እንደዚህ ያለ ታሪክንና ዐውድን ያገናዘበ አቀራረብ፡- ቃለ ሃይማኖትንና ሥርዓትን ቀዳምያኑ ሠሪዎች (ሐጋጊዎች) ባፀደቁበት ዐውድና በእኛ የዛሬ መረዳት መካከል የሚኖረውን ክፍተት በመሙላት ረገድ ዐቢይ ድርሻ ይኖረዋል፡፡ የምንጩ ልሳነ ብዙኅ መሆን የቲዎሎጂ መምህራንና ተማሪዎች ከአብነቶቹ ያላቸውን ተዋሥኦ ያዳብራል፡፡ የወንድማችን የዲያቆን አዶንያስ ብርሃነ ‹የቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎች» መጽሐፍ ለዚህ ተዋሥኦና ጥናት ብዙ ርቀት የሚያስጉዝ ስንቅ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ ከኢየሩሳሌሙ የሐዋርያት ጉባኤ እስከ ቊስጥንጥንያ የነበሩትን ጉባኤያት በግሩም አቀራረብ ቃኝቶ በመልካም ትርጓሜ አቅርቦልናል፡፡ መልካም ንባብ! በአማን ነጸረ ደብተራና የሕግ ባለሙያ በግዮን መጻሕፍት ታገኙታላችሁ።

#የተባረከች_አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች #የተባረከች_ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች #የተባረከ_ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል #የተባረከች_ምላስ የአምላ
#የተባረከች_አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች #የተባረከች_ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች #የተባረከ_ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል #የተባረከች_ምላስ የአምላኳን ስጋና ደምን ትቀበላለች #የተባረከ_አንደበት ላይ እግዚሐብሔር ይመስገን የሚል ቃል አይጠፋበትም #የተባረከች_አንገት የአምልኮ ደም የፈሰሰበትን ቅዱስ መስቀል ትሸከማለች #የተባረከች_ልብ ኢየሱስን እስከ እናቱ አንግሳ በፍቅር ትሞላለች #የተባረከች_እጅ የቀረበላትን ምግብ በአምልኮ ስም ትባርካለች #የተባረከች_እግር ጠዋትና ማታ የአምላኳን መቅደስ ትረግጣለች "እኔ እግዚሐብኤር አምላካቹ ነኝና ሰውነታችሁን ቀድሱ ቅዱስም ሁኑ እኔ ቅዱስ ነኝና" ዘሌ. 11፥44 #አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ