fa
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

رفتن به کانال در Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

نمایش بیشتر
3 314
مشترکین
-324 ساعت
-137 روز
-3730 روز
آرشیو پست ها
…... ለጠቅላይ ቤተ ክህነት የተጻፈላቸውን ደብዳቤ ይዘው ቤተ ክህነት ሲደርሱ፤ የቤተክህነቱ ባለሥልጣናት ‘እንዴት ለአንድ መምህር ደመወዝ አንድ መቶ ብር ይከፈላል? ለእርስዎ ሃያ ብር ይበቃዎታል’
…... ለጠቅላይ ቤተ ክህነት የተጻፈላቸውን ደብዳቤ ይዘው ቤተ ክህነት ሲደርሱ፤ የቤተክህነቱ ባለሥልጣናት ‘እንዴት ለአንድ መምህር ደመወዝ አንድ መቶ ብር ይከፈላል? ለእርስዎ ሃያ ብር ይበቃዎታል’ ብለው ቀነሱት፡፡ ሆኖም በሁኔታው ያዘኑ የእርሳቸው የሆኑ ሰዎች ‘ንጉሡ የፈቀዱትን እዚህ ያሉት ሠራተኞች ሊቀንሱ ስለማይችሉ አሁንም ሄደው ያመልክቱ’ ይሏቸዋል፡፡ እሳቸውም ‘ሄጄ የማመለክተው እዳ ለምን ተቀነሰልኝ ብዬ ነው? ይኼውም ሲበዛብኝ ነው’ ብለው ያንን ሃያ ብር ደመወዝ ተቀበሉ፡፡ ታዲያ አዲስ አበባ ሄደው በነበሩበት ጊዜ ….. ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን ይሄዳሉ፡፡ ቀደም ሲል ጎንደር አብረዋቸው ይማሩ የነበሩት አለቃ የማነብርሃን የሚባሉ ዳር ሀገር እየተባለ ከሚጠራው ቦታ የሚኖሩ በአጋጣሚ ለጉዳያቸው አዲስ አበባ መጥተው ኖሮ እዚሁ አራዳ ቅዱሰ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን ድንገት ይገናኛሉ፡፡ መንፈሳዊ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ስለኑሯቸው ሲወያዩ፡- ‘አዬ ጥበቡ! ለእኛ ትበጃለህ ብለን የምናምንብህ እዚያ ከገጠር ተሸጉጠህ ቀረህ፡፡ እኔን እንኳ እስኪ ተመልከተኝ’ ብለው በኑሯቸው የደላቸው መሆናቸውን ለማስረዳት ሲሞክሩ፡- ‘አዬ የማነብርሃን! እኔም እኮ የጠላሁት እንዳንተ መሆኑን ነው’ አሏቸው…..” ከውስጥ ገጽ «#የማምሻ_ዕድሜ_ወግ»» 📚ፍኖተ መጻሕፍት t.me/FinoteBooks1623

📚#ዝክረ ቅዱሳን አንስት ዘተዋሕዶ ፩ ...#የጣማፍ_ኄራኒ አኗኗር ገዳማዊነትን በትክክል ላየ ሰማያዊ ሰው ወይም ምድራዊ መልአክ የሚያሰኝ ነው። በዚህ የተቀደሰ ኑርዋ ውስጥ የጥንታውያኑን ገዳማውያን
📚#ዝክረ ቅዱሳን አንስት ዘተዋሕዶ ፩ ...#የጣማፍ_ኄራኒ አኗኗር ገዳማዊነትን በትክክል ላየ ሰማያዊ ሰው ወይም ምድራዊ መልአክ የሚያሰኝ ነው። በዚህ የተቀደሰ ኑርዋ ውስጥ የጥንታውያኑን ገዳማውያን አበውና እማት አኗኗር እንድናይ አድርጋናለች። ሥርዓቱን ከሕይወቷ ጋር እያናበበች ወይም እየኖረች በማሳየት አዲሱ ትውልዳችን የጥንታውያኑን ክርስ ቲያኖች መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሕይወትና ፍቅረ እግዚአብሔርን ገንዘብ ያደርግ ዘንድ፥ እንደ መጽሐፍ የሚነበብ አገልግሎቷንና ተጋድሎዋን ማቅረብ የቤተ ክርስቲያን ቀዳሚ ተግባሯ ነው᎓᎓ ከባሕር የወጣ ዐሣና ከገዳሙ የወጣ መነኰስ አንድ ናቸው እንደሚባለው ሁሉ፡ ከወንጌል የራቀ ክርስቲያንም የነፍስ ድኅነት የለውምና፥ ወንጌል ከሆነው የቅዱሳን አበውና እማት ሕይወት እንማር።በአጠቃላይ የመጽሐፉ ዐላማ ሴቶች በመንፈሳዊ ጉዞአቸው ከወንዶቹ በምንም እንደማይተናነሱና ይህንንም በተለያዩ ዘመናት የነበሩ አንስት በገድል እየኖሩ ያሳዩ መሆ ናቸውን ማሳወቅና መልካም አርአያነታቸውንም መግለጽ ነው። Ⓒለረዥም ጊዜ ከገበያ ጠፍቶ የነበረው ይህ መጽሐፍ በጥሩ ኅትመት በድጋሚ ወደ ገበያ መጥቷል። 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

#ተወዳጆች.... ➮የዕቅበተ እምነቷ ቅመም ባለማወቅ ለተነጠቁት ዓይነተኛ መፍትሔ (መድኃኒት) በመኾን የጠቀመ በእውር ድንብር ለሚመሩት ደግሞ ከዳተኝነታቸው የተነሳ የሚፈሩት የ*መ*ና*ፍ*ቃ*ን 🔨 በ
#ተወዳጆች.... ➮የዕቅበተ እምነቷ ቅመም ባለማወቅ ለተነጠቁት ዓይነተኛ መፍትሔ (መድኃኒት) በመኾን የጠቀመ በእውር ድንብር ለሚመሩት ደግሞ ከዳተኝነታቸው የተነሳ የሚፈሩት የ*መ*ና*ፍ*ቃ*ን 🔨 በጉምቱ መምህራችን በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተቀመመው ድንቁ መጽሐፋችን #መድሎተ ጽድቅ ቅጽ-፩ #ለ20ኛ_ጊዜ_ታትሟል!! ''ለሰው ልጆች መዳኛ ትሆን ዘንድ ከእግዚአብሔር የተሰጠችው አንዲቷ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ክርስትና  በሰዎች ግለሰባዊ አስተሳሰብና 'መሰለኝ' በሚል ግምትና መላ ምት የተገኘች ሳትሆን ከራሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠች ናት፡፡''            [ከውስጥ ገጽ....] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

#ተወዳጆች.... ➮የዕቅበተ እምነቷ ቅመም ባለማወቅ ለተነጠቁት ዓይነተኛ መፍትሔ (መድኃኒት) በመኾን የጠቀመ በእውር ድንብር ለሚመሩት ደግሞ ከዳተኝነታቸው የተነሳ የሚፈሩት የ*መ*ና*ፍ*ቃ*ን 🔨 በ
#ተወዳጆች.... ➮የዕቅበተ እምነቷ ቅመም ባለማወቅ ለተነጠቁት ዓይነተኛ መፍትሔ (መድኃኒት) በመኾን የጠቀመ በእውር ድንብር ለሚመሩት ደግሞ ከዳተኝነታቸው የተነሳ የሚፈሩት የ*መ*ና*ፍ*ቃ*ን 🔨 በጉምቱ መምህራችን በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተቀመመው ድንቁ መጽሐፋችን #መድሎተ ጽድቅ ቅጽ-፩ #ለ20ኛ_ጊዜ_ታትሟል!! ''ለሰው ልጆች መዳኛ ትሆን ዘንድ ከእግዚአብሔር የተሰጠችው አንዲቷ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ክርስትና  በሰዎች ግለሰባዊ አስተሳሰብና 'መሰለኝ' በሚል ግምትና መላ ምት የተገኘች ሳትሆን ከራሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠች ናት፡፡''            [ከውስጥ ገጽ....] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#ሕይወተ_ማርያም_ድንግል .....እንግዲህ ምን እንላለን ሕዝቅኤል ያያትን አዳራሽ ቁራዎች ቢከቧት ምን አደረጉ፤ እንዲያው እነሱ እየታጨዱ ወደቁ እንጅ ፤ ዛሬም #የእመቤታችንን ክብር ያቃለልን መስ
📚#ሕይወተ_ማርያም_ድንግል .....እንግዲህ ምን እንላለን ሕዝቅኤል ያያትን አዳራሽ ቁራዎች ቢከቧት ምን አደረጉ፤ እንዲያው እነሱ እየታጨዱ ወደቁ እንጅ ፤ ዛሬም #የእመቤታችንን ክብር ያቃለልን መስሏቸው ተረፈ ቁራዎች ዙሪያዋን ከበው መጽሐፍ ይጽፋሉ፣ንግግር ያደርጋሉ ግን በአዳራሷ ላይ ቅንጣት ታክል ነውር መጨመር እንደማይችሉ የምናገርበት አጋጣሚ ቢሆነኝ ብዬ እኔም አባቶቼ #ስለእመቤታችን ከተናገሩት የውዳሴ ውቅያኖስ ቀድቼ እንደ ክብሯ ሳይሆን መንፈስ ቅዱስ በረዳኝ መጠን በማብዛት ያይደለ በማሳነስ፤ በማስረዘም ያይደለ በማሳጠር ጥቂት ቃላትን ተናግሬአለሁና እንድታነቡልኝ ‹‹በእንተ ስማ ለማርያም›› እላለሁ። ✍️ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መላክ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

....ክቡር ኃያል መስተጋድል #ሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ማር_ጊዮርጊስ እጅግ ደስ ብሎት #ጌታዬ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ሆይ የማይገባኝን እጅግ አክብረኸኛልና አመሰግንሀለሁ አለ :: ከዚኽ በኋላም #ጌታችን የተ
....ክቡር ኃያል መስተጋድል #ሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ማር_ጊዮርጊስ እጅግ ደስ ብሎት #ጌታዬ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ሆይ የማይገባኝን እጅግ አክብረኸኛልና አመሰግንሀለሁ አለ :: ከዚኽ በኋላም #ጌታችን የተመሰገነ #ሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስን ባርኮት ከእርሱ ተሠወረ #ቅዱስ_ማር_ጊዮርጊስም ወታደሮችን ቀስቅሶ ወንድሞቼ ኑ የታዘዛች ሁትን ፈጽሙ አላቸው ፡፡ ፊቱንም ወደ ምሥራቅ መልሶ #በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስቅዱስ ብሎ በመስቀል ምልክት አማትቦ አንገቱን አቀረበ ፡፡ ያን ጊዜም የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ማር ጊዮርጊስን የከበረች ራሱን ቈረጡት ደምና ውኃ ወተትም ፈሰሰው ፡፡ ጌታም ደሙን በብርሃን ልብስ እንዲቀበለው ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤልን አዘዘለት ፡፡#ጌታችንና መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የኀያሉ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን ነፍስ በእጁ ተቀብሎ ሳማት በሰማያዊ ልብስም አጐናጽፎ ከእርሱ ጋራ ወደ ሰማይ አሳረጋት፡፡ ✨ሰላም ለከ በእንተ #ሃይማኖት_ርትዕት ነፍስ ዚአከ ትሜጡ፣#ጊዮርጊስ ዕፍረት ዘዕፁብ ሤጡ ፣ ገበርተ አፈው እምይጽዕጡ ፡፡ ትርጉም ሽቱን የሚቀምሙ ከሚያጣፍጡት ሽቱ ይልቅ ዋጋህእጅግ ድንቅ የኾነ ስለቀናች ሃይማኖት ነፍስህን የሰጠህ #ሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሆይ ምስጋና ይድረስህ ፡፡ 🍂ለኃያሉ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት በዓል እንኳን አደረሰን! ክብርት ጸሎቱ ትድረሰን ፥ እንደእርሱ የእውነት ምስክርም እንድንኾን ምልጃው ትደግፈን!

📚#መጽሐፈ_አርጋኖን «እምኵሉ ድርሳናት ዘተናገርክዎሙ ይጥዕም ወይትሌዓል፤ ልቦናዬን መንፈስ ቅዱስ አነሣስቶኝ ከተናገርኋቸው ውዳሴያት ኹሉ መጽሐፈ አርጋኖን ጥዑም ነው...» ሲል ታላቁ ሊቅ #ጻድቁ_
📚#መጽሐፈ_አርጋኖን «እምኵሉ ድርሳናት ዘተናገርክዎሙ ይጥዕም ወይትሌዓል፤ ልቦናዬን መንፈስ ቅዱስ አነሣስቶኝ ከተናገርኋቸው ውዳሴያት ኹሉ መጽሐፈ አርጋኖን ጥዑም ነው...» ሲል ታላቁ ሊቅ #ጻድቁ_አባ_ጊዮርጊስ የተናገረውን በከበረ መጽሐፈ ገድሉ ምዕራፍ አምስት አንቀጽ ዐሥራ አንድ ላይ እንመለከታለን ፡፡እነሆ ገቢው ለደብረ ባሕርይ ጻድቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫና ለቅዱስ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል አንድነት ገዳም ይውል ዘንድ በገዳሙ ፈቃድ ይኽ መጽሐፈ አርጋኖን ኢትዮጵያውያን የጻድቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫና የቅዱስ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ወዳጆች ኹሉ ለብዙ ዘመናት ረድኤተ እግዚአብሔርን ለማግኘት የእመቤታቸንን አማላጅነት ሲማፀኑበት ከጠላ ቶቻቸው እጅ ሲጠበቁበትና ሀብተ ሥጋ ሀብተ ነፍስን ሲቀበሉበት ይልቁንም ጸሎቱን ደግመው እየተጠመቁ ሲፈወሱበት ኖረዋል ።-ስለዚህ እመቤታችን ለጻድቁ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በገለጠችላቸው በዚህ በከበረ መጽሐፈ አርጋኖን ድኅነተ ሥጋ፣ድኅነተ ነፍ ስን እናገኝ ዘንድ ልቦናችን በምስጋና ይመላ ዘንድ አዘውትረንም ወደፈጣሪያችን እንጸልይበት ። " የጻድቁ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ጸሎት ኃይልን ታደርጋለች : ታድናለችምና " [የጻድቁ አባታችንአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫና የቅዱስ አባ በጸሎተ ሚካኤስ አንድነት ገዳም] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

«ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወለሥዕለ ወልድኪ እገኒ ማርያም ድንግል ማርያም እመ አዶኒ ማዕበለ ጌጋይ ጽኑዕ ሶበ ለአስጥሞ በጽሐኒ ሐመርየኒ ማዕዶትየኒ ሃይማኖትየኒ ማርያም እግዝእትየ ወእንበሌኪ አልብየ ም
«ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወለሥዕለ ወልድኪ እገኒ ማርያም ድንግል ማርያም እመ አዶኒ ማዕበለ ጌጋይ ጽኑዕ ሶበ ለአስጥሞ በጽሐኒ ሐመርየኒ ማዕዶትየኒ ሃይማኖትየኒ ማርያም እግዝእትየ ወእንበሌኪ አልብየ ምንትኒ::"    ትርጉም:- "በሥዕልሽ ፊት ልስገድ ለልጅሽም ሥዕል ልገዛ ድንግል ማርያም እናቱ  የአዶናይ የዓለሙ ቤዛ ነፍሴን ሊያሰጥማት ደርሶ የበደሌ ማዕበል ሲበዛ ሃይማኖቴ አንቺ ነሽ መርከቤ መሻገሪያ ምሽግ ታዛ ማን አለኝ ያላንቺ እመቤቴ ማርያም የንግግሬ ለዛ::"           "አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መልክአ ሥዕል" "እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ"ከልጅሽ ከወዳጅሽ አማልጂን ሰላም አንድነት ፍቅር ስጭን በመንገዳችን በሕይወታችን ሁሉ አትለይን ዘመናችንን ባርኪልን ርስት ሀገርሽን ኢትዮጵያን ጠብቂልን፥ ከሐሰተኞች መምህራን ጠብቂን ::»

«ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወለሥዕለ ወልድኪ እገኒ ማርያም ድንግል ማርያም እመ አዶኒ ማዕበለ ጌጋይ ጽኑዕ ሶበ ለአስጥሞ በጽሐኒ ሐመርየኒ ማዕዶትየኒ ሃይማኖትየኒ ማርያም እግዝእትየ ወእንበሌኪ አልብየ ም
«ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወለሥዕለ ወልድኪ እገኒ ማርያም ድንግል ማርያም እመ አዶኒ ማዕበለ ጌጋይ ጽኑዕ ሶበ ለአስጥሞ በጽሐኒ ሐመርየኒ ማዕዶትየኒ ሃይማኖትየኒ ማርያም እግዝእትየ ወእንበሌኪ አልብየ ምንትኒ::"    ትርጉም:- "በሥዕልሽ ፊት ልስገድ ለልጅሽም ሥዕል ልገዛ ድንግል ማርያም እናቱ  የአዶናይ የዓለሙ ቤዛ ነፍሴን ሊያሰጥማት ደርሶ የበደሌ ማዕበል ሲበዛ ሃይማኖቴ አንቺ ነሽ መርከቤ መሻገሪያ ምሽግ ታዛ ማን አለኝ ያላንቺ እመቤቴ ማርያም የንግግሬ ለዛ::"           "አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መልክአ ሥዕል" "እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ"ከልጅሽ ከወዳጅሽ አማልጂን ሰላም አንድነት ፍቅር ስጭን በመንገዳችን በሕይወታችን ሁሉ አትለይን ዘመናችንን ባርኪልን ርስት ሀገርሽን ኢትዮጵያን ጠብቂልን፥ ከሐሰተኞች መምህራን ጠብቂን ::»

«ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወለሥዕለ ወልድኪ እገኒ ማርያም ድንግል ማርያም እመ አዶኒ ማዕበለ ጌጋይ ጽኑዕ ሶበ ለአስጥሞ በጽሐኒ ሐመርየኒ ማዕዶትየኒ ሃይማኖትየኒ ማርያም እግዝእትየ ወእንበሌኪ አልብየ ም
«ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወለሥዕለ ወልድኪ እገኒ ማርያም ድንግል ማርያም እመ አዶኒ ማዕበለ ጌጋይ ጽኑዕ ሶበ ለአስጥሞ በጽሐኒ ሐመርየኒ ማዕዶትየኒ ሃይማኖትየኒ ማርያም እግዝእትየ ወእንበሌኪ አልብየ ምንትኒ::"    ትርጉም:- "በሥዕልሽ ፊት ልስገድ ለልጅሽም ሥዕል ልገዛ ድንግል ማርያም እናቱ  የአዶናይ የዓለሙ ቤዛ ነፍሴን ሊያሰጥማት ደርሶ የበደሌ ማዕበል ሲበዛ ሃይማኖቴ አንቺ ነሽ መርከቤ መሻገሪያ ምሽግ ታዛ ማን አለኝ ያላንቺ እመቤቴ ማርያም የንግግሬ ለዛ::"           "አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መልክአ ሥዕል" "እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ"ከልጅሽ ከወዳጅሽ አማልጂን ሰላም አንድነት ፍቅር ስጭን በመንገዳችን በሕይወታችን ሁሉ አትለይን ዘመናችንን ባርኪልን ርስት ሀገርሽን ኢትዮጵያን ጠብቂልን፥ ከሐሰተኞች መምህራን ጠብቂን ::»                

«ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወለሥዕለ ወልድኪ እገኒ ማርያም ድንግል ማርያም እመ አዶኒ ማዕበለ ጌጋይ ጽኑዕ ሶበ ለአስጥሞ በጽሐኒ ሐመርየኒ ማዕዶትየኒ ሃይማኖትየኒ ማርያም እግዝእትየ ወእንበሌኪ አልብየ ም
«ቅድመ ሥዕልኪ እሰግድ ወለሥዕለ ወልድኪ እገኒ ማርያም ድንግል ማርያም እመ አዶኒ ማዕበለ ጌጋይ ጽኑዕ ሶበ ለአስጥሞ በጽሐኒ ሐመርየኒ ማዕዶትየኒ ሃይማኖትየኒ ማርያም እግዝእትየ ወእንበሌኪ አልብየ ምንትኒ::"    ትርጉም:- "በሥዕልሽ ፊት ልስገድ ለልጅሽም ሥዕል ልገዛ ድንግል ማርያም እናቱ  የአዶናይ የዓለሙ ቤዛ ነፍሴን ሊያሰጥማት ደርሶ የበደሌ ማዕበል ሲበዛ ሃይማኖቴ አንቺ ነሽ መርከቤ መሻገሪያ ምሽግ ታዛ ማን አለኝ ያላንቺ እመቤቴ ማርያም የንግግሬ ለዛ::"           "አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መልክአ ሥዕል" "እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ"ከልጅሽ ከወዳጅሽ አማልጂን ሰላም አንድነት ፍቅር ስጭን በመንገዳችን በሕይወታችን ሁሉ አትለይን ዘመናችንን ባርኪልን ርስት ሀገርሽን ኢትዮጵያን ጠብቂልን፥ ከሐሰተኞች መምህራን ጠብቂን ::»                

💧አዲስ መጽሐፍ 📚#መልክአ_ሥዕል_ንባቡና_ትርጓሜው ➥ይኽ የቅዱሳት ሥዕላትን ክብር በግጥም ስንኝ ቋጥሮ የሚያወድስ“መልክአ ሥዕል” አስደናቂ ድርሰት ሲኾን በውስጡም፡- ❖ ስለ ቅዱሳት ሥዕላት ታሪክ
💧አዲስ መጽሐፍ 📚#መልክአ_ሥዕል_ንባቡና_ትርጓሜው ➥ይኽ የቅዱሳት ሥዕላትን ክብር በግጥም ስንኝ ቋጥሮ የሚያወድስ“መልክአ ሥዕል” አስደናቂ ድርሰት ሲኾን በውስጡም፡- ❖ ስለ ቅዱሳት ሥዕላት ታሪክ ❖ ስለ ቅዱሳት ሥዕላት ሠዓሊዎች ❖ ስለ ቅዱሳት ሥዕላት ክብር ❖ ስለ ቅዱሳት ሥዕላት ዓይነቶች (የጌታችን እና የእመቤታችን ሥዕላት) ❖ ከመላእክት ሥዕላት ውስጥ የቅዱስ ሚካኤል፣ የቅዱስ ገብርኤል፣ የቅዱስ ሩፋኤልን ሥዕላት ❖ ከሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስን ሥዕል ❖ በተለያዩ ሀገራት ስለሚገኙ ቅዱሳት ሥዕላት ❖ በቅዱሳት ሥዕላት ስለተደረጉ ተአምራት በግጥም መልኩ በውስጡ ተጽፈዋል፡፡ስለ ቅዱሳት ሥዕላት ክብር የተደረሰው የዚኽ የመልክአ ሥዕል ደራሲ ማነው? ለሚለው ጥያቄ የደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በአታ የአቋቋም ምስክር ጉባኤ ቤት መምህር የነበሩት መጋቤ አእላፍ ሔኖክ ወልደ ሚካኤል ባሳተሙት “መልክአ ጉባኤ” ላይ የግል ምንጭ ኅሩይን በመጥቀስ በገጽ ፫፻፲፰ ላይ ዐጼ ገላውዴዎስ እንደኾኑ ጽፈዋል፡፡ ◈አንባብያን ሆይ መጽሐፉን ሳዘጋጅ ምናልባት በኮምፒውተር ጽሕፈት ጊዜ የሚያጋጥም የፊደልና የቍጥር ግድፈት ካገኛችኍ መልታችኍ እንድታነቡት በአክብሮት እጠይቃለኊ፡፡ ✍️[መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#ሳይንስ_እና_ሃይማኖት ...ተፈጥሯዊ የሆነውን የአጽናፈ ዐለም ምስጢር በገለጥን ቁጥር የእግዚአብሔርን እጅ እየገለጥን ነው፤ ምክንያቱም የሰው ልጅ የዚህን ዐለም ጥበብ የሚመረምርበትንና የሚረዳበት
📚#ሳይንስ_እና_ሃይማኖት ...ተፈጥሯዊ የሆነውን የአጽናፈ ዐለም ምስጢር በገለጥን ቁጥር የእግዚአብሔርን እጅ እየገለጥን ነው፤ ምክንያቱም የሰው ልጅ የዚህን ዐለም ጥበብ የሚመረምርበትንና የሚረዳበትን እውቀት የሰጠው እግዚአብሔር ነውና። ስለዚህ ሳይንስ ከክርስትና እምነት ጋር ይጋጫል ብሎ ማሰብ እግዚአብሔርን ከመተቸት ጋር ተመሳሳይ ነው፤ ምክንያቱም በሳይንስ የምንረዳውን ነገር አስቀድሞ የፈጥረው እርሱ ነውና። በሳይንስ እና በእምነት መካከል በተከፋፈለ ዐለም ውስጥ፣ “ሳይንስ እና ሃይማኖት” ተለምዷዊ ድንበሮችን በመሞገት አንባቢዎች የእውነትን መንገድ እንደገና እንዲያጤኑት ይጋብዛል። ሳይንቲዝምን እንጂ ሳይንስን ባልተቃውመ መልኩ፣ መምህር ያረጋል አበጋዝ ጥልቅ ሐሳቦችን እንዲመረምሩ ይጋብዛል።በአጠቃላይ፣ በሳይንስ እና በእምነት መካከል ያለውን ጥልቅ ግኑኝነት የሚዳስስ አእምሯዊ አነቃቂና በመንፈሳዊ የበለጸገ መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ ስለ ህልውና ምስጢር ለማወቅ ለሚፈልግ ለማንኛውም ሰው በጣም ይመከራል። ✍️ዲያቆን ክብረት መኳንንት 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📜ወይቤሉ በበይናቲሆሙ ፥ አኮኑ ይነድደነ ልብነ ፥ ዘከመ ይነግረነ በፍኖት ፥ ወይፌክር ለነ መጻሕፍተ!📖 «እርስ በርሳቸውም፦ “በመንገድ ሲናገረን መጻሕፍትንም ሲከፍትልን ልባችን ይቃጠልብን አልነበ
📜ወይቤሉ በበይናቲሆሙ ፥ አኮኑ ይነድደነ ልብነ ፥ ዘከመ ይነግረነ በፍኖት ፥ ወይፌክር ለነ መጻሕፍተ!📖 «እርስ በርሳቸውም፦ “በመንገድ ሲናገረን መጻሕፍትንም ሲከፍትልን ልባችን ይቃጠልብን አልነበረምን?” ተባባሉ» [ሉቃ ፳፬፥፴፪]

📚#የበርሃ_ምንጮች📚 [ማላንካራውያን] .....ኢትዮጵያውያን ወላጆችም ልክ እንደ ማላንካራውያን የዛሬ ሕፃናት የነ አባቶች፣ የዛሬ ሕፃናት የነገ ሀገር መሪዎች፣ የዛሬ ሕፃናት የነገ ካህናት ጳጳሳት
📚#የበርሃ_ምንጮች📚 [ማላንካራውያን] .....ኢትዮጵያውያን ወላጆችም ልክ እንደ ማላንካራውያን የዛሬ ሕፃናት የነ አባቶች፣ የዛሬ ሕፃናት የነገ ሀገር መሪዎች፣ የዛሬ ሕፃናት የነገ ካህናት ጳጳሳት መሆናቸውን ተረድተን ልጆቻችን እንዲሆኑ የምንመኘውን የምንፈልጋትን ኢትዮጵያ እና ቤተክርስቲያንን ለማየት እንድንችል ዛሬ ላይ ሆነን ነገን በጋራ ለልጆቻችን እንሥራላቸው፡፡ ሥራችንን ከቤታችን እንጀምር። ቢያንስ የወለድናቸውን ልጆች የእግዚአብሔር እንዲሆኑ እናድርጋቸው እኔ ካየሁት እውነት በመነሳት ይህንን የማትጊያ መጽሐፍ ለነገይቱ ቤተክርስቲያን እና ልጆቿ ይጠቅማል ብዬ ሳበረክት እንደመነሻ ይሆን ዘንድ እንጂ ከዚህ የተሻለ ሥራ ይዘው የሚቀርቡ ወንድሞችና እህቶች እንደሚኖሩ ሙሉ እምነት አለኝ፡፡ የተወደዳችሁ አንባብያን መጽሐፉን ስታነቡት የአጻጸፍ ግድፈትም ሆነ ሌላ ክፍተቶችን ካገኛችሁ የእኔ የጸሓፊው ድክመት እንጂ የማንም አለመሆኑን በቅንነት እንድትረዱኝ እጠይቃለሁ ። [✍️ ጸሐፊው] ➲ማሳሰቢያ የመጽሐፉ ሙሉ ገቢ ለቤተክርስቲያን የተደረገ ሲኾን በኹለት ወገን የምንጠቀምበት መጽሐፍ ነው..! 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#ኅብረ_ሥርዐት ➥ዘመናችን ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን እጅጉን ፈተና ላይ የወደቀበት፤ የቤተ ክርስቲያን ሥርዐቷ ባለቤት ያጣበት ጊዜ መሆኑን መናገር ለቀባሪ የማርዳት ያህል ነው። ነገሩ ሲከፋ ደግሞ የ
📚#ኅብረ_ሥርዐት ➥ዘመናችን ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን እጅጉን ፈተና ላይ የወደቀበት፤ የቤተ ክርስቲያን ሥርዐቷ ባለቤት ያጣበት ጊዜ መሆኑን መናገር ለቀባሪ የማርዳት ያህል ነው። ነገሩ ሲከፋ ደግሞ የቤተ ጉባኤና የቤተ ክርስቲያንን የሥርዐት መጻሕፍት ጠቅሶ ማስተማር የሚያሳፍር የሚመስልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል። "ጸሐፊ" እና "ሰባኪ" የሚል ስም ተሸክመው ፍትሐ ነገሥትን የመሰሉ የሥርዐት መጻሕፍትን ለመጥቀስ እንኳ ፍላጎት የሌላቸው "አገልጋዮች" እጅግ ብዙ ናቸው። ይህ ደግሞ ምእመናንን ለእግዚአብሔር ሥርዐት ግዴለሽ እንዲሆኑ አድርጓል። በውጤቱም ክርስትና ከተግባር ቅድስና ይልቅ ስብከትና ጽሑፍ ብቻ እንዲሆን አስገድዷል። ስለዚህም እንደዚህ ያሉ የሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት በእጅጉ ያስፈልጉናል። ይህ መጽሐፍ ኹሉንም የቤተ ክርስቲያኗን ሥርዐቶች ለማካተት ይዘቱ፣ መጠኑ ባይፈቅድም ወሳኝ የሚባሉትን ነጥቦች በጥያቄና መልስ እያሰናሰለ ይዟል። ትኩረቱን ደግሞ በተለይ የዘመናችን የሥርዐት ክፍተት የሚታይባቸው የቅዳሴ፤ የቤተ ክርስቲያን ዙሪያና መሰል ጉዳዮች ላይ አድርጓል። ጸሐፊው፦ መምህር አብርሃም ከልጅነታቸው ተምረው በዜማ፤ በቅኔና በመጻሕፍተ ትርጓሜ የበሰለ አእምሮ ከጥሩ ብዕር ጋር ያላቸው ናቸውና ለዚህ የመጀመሪያ የጽሑፍ ሥራቸው መርቀናቸዋል። መሰል መጻሕፍትን ከመንፈስ ቅዱስ እርዳታ የተነሣ ከትበው ያበረክቱልናል የሚል ተስፋ አለን፡ [ዲያቆን ዮርዳኖስ ] ◉ስንንጠቁም ለንባብ ስንመርጥ ከምንኮራባቸው መጻሕፍት መካከል አንዱ ነው አዘገጃጀቱም ለአንባቢ የሚገባና ቀላል ነው፤ ጸሐፊውን መርቀናል፥ አንብባችሁ ተጋሩን! 📚ፍኖተ መጻሕፍት [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

📚#ሦስቱ_መጻሕፍተ_መነኰሳት #በተስፋ_ገብረሥላሴ_ዘብሔረ_ቡልጋ የተዘጋጀ.... ...#ታሪክ ፤ የሙሴ ፡ ጸሊም ፡ ጌቶቹ ፡ ፀሐይ ፡ ጨረቃ ያመልኩ ፡ ነበር ፤ እነዚያ ፡ ሙተው ፡ ለልጆቹ ፡ ይገዛ
📚#ሦስቱ_መጻሕፍተ_መነኰሳት #በተስፋ_ገብረሥላሴ_ዘብሔረ_ቡልጋ  የተዘጋጀ.... ...#ታሪክ ፤ የሙሴ ፡ ጸሊም ፡ ጌቶቹ ፡ ፀሐይ ፡ ጨረቃ ያመልኩ ፡ ነበር ፤ እነዚያ ፡ ሙተው ፡ ለልጆቹ ፡ ይገዛል ልጆቹም ፡ ፀሐይ ፡ ጨረቃ ፡ ያመልካሉ ፡ ከዕለታት አንድ ፡ ቀን ፡ ከባልንጀሮቹ ፡ ጋራ ፡ ሊሠርቁ ፡ ሊቀሙ ፡ በረኃ ፡ ለበረኃ ፡ ሲሄዱ ፡ ዋዕየ ፡ ፀሐይ ጸናባ ቸው ፡ ከጥላ ፡ አርፈው ፡ ሳለ ፡ ቀና ፡ ብሎ ፡ ፀሐይን፡ ስትባክን ፡ አይቶ ፡ አሁን ፡ ይች ፡ ፀሐይ ፡ ምን ፡ ምላክ ፡ ናት ፤ አምላክስ ፡ የኔ ፡ ጌቶች ናቸው ፡ በል ተው ፡ ጠጥተው ፡ ከጥላ ፡ አርፈው ፡ የሚውሉ አላቸው ። እነሱም አሻግረው ፡ አይተው ፡ አምላክ አምላክ ፡ ትላለህ ፡ አምላክማ ፡ ከፈለገህ ፡ ያባ ኤስ ድሮስ ፡ ገዳም ፡ ያውልህ አትሄድምን ፡ አሉት ያው ፡ ተነሥቶ ፡ ሄደ ፤ ከገዳሙ ፡ ቢደርስ ፡ ግብሩን፡ ያውቃሉና ፡ ማኅበሩ ፡ ተሸበሩ ፣ አበ ፡ ምኔቱ ፡ አባ ኤስድሮስ ፡ ነው ፤ ጸጋ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጠርታ ፡ አ ምጥታዋለችና ፡ ይልቅ ፡ ተቀበሉት ፡ አላቸው : ተቀብለው ፡ አገቡት ፣ ከዚያ ፡ በኋላ ፡ ልጄ ፡ ምን ፡ አመ ጣህ ፡ አለው ፡ ትመክረኝ ፡ ብዬ ፡ አለ። መከረው አስተማረው ፤ አመነ ፡ ተጠመቀ ፤ ደግ ሰው ሆነ አመንኩሶታል። 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

ጉባኤ ቤታችን [ጉባኤ ደብረ ምጥማቅ] በኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች አማካኝነት ያሠራቸውን የደቀመዛሙርት መኖሪያ ቤቶች አስመረቀ!      ─━━━━━⊱✿⊰━━━━━─ በ«ብፁዕ አባታችን አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ» መልካም ፈቃድ ፣ በክቡር መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ወልደ ጊዮርጊስ በኩል ገዳሙ ባመቻቸልን ቦታ ፣ በጉባኤ ቤቱ መምህር በሊቀ ሊቃውንት ነቢየ ልዑል አዳሙ አስተባባሪነት፦ ፩. በሕፃን ወለተ-ገብርኤል ፪. በኀይለ-ገብርኤል ፫. በወለተ-ብርሃን ፬. በወለተ-አማኑኤል አማክኝነት ሙሉ ውጪው ተሸፍኖ - ገዳማችን በማቻቸልን ቦታ - የተሠሩ የደቀመዛሙርት ቤቶችን ፥ በሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ በ«ብፁዕ አባታችን አቡነ ቀሌምንጦስ» ቡራኬ በዛሬው ዕለት አስመርቋል። በብፁዕ አባታችን መሪነት ሥርዐተ ቅዳሴ በገዳሙ አገልጋይ ካህናት ከተከናወነ በኋላ - የቡራኬ ሥርዐቱ በብፁዕነታቸው ተፈጽሟል። ለእንግዶች የ«እንኳን ደና መጣችኹ» መልእክት ያሰሙት የጉባኤ ቤቱ መምህር - ጉባኤ ቤቱን በተወሰነ ደረጃ ለእንግዶች የሚያስተዋውቅ ከውጥን ኺደቶች አንሥተው አኹን እስካለበት ኹኔታ አውስተው ፥ ጉባኤ ቤቱ በዚኽ ልክ ሰፍቶ ማየታቸው በብፁዕነታቸው የቅርብ ክትትል መኾኑን በማንሣት ለብፁዕነታቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ከጉባኤ ቤቱ ደቀመዛሙርት መካከል የኔታ ዳዊት (የድጓ መምህር) በያሬዳዊ ዜማ ምሥጢርን ከኩነታዊው ኹኔታ አዋድደው ጥዑም ዜማ ያሰሙ ሲኾን - በመ/ር ኢሳይያስና በመ/ር ዕዝራ የቅኔ ቆይታ ተደርጓል። ጉባኤ ቤቱ እያደረገ ያለው አካባቢያዊ አገልግሎት ፣ ነባር አገራዊ ታሪኮችን ድጋሚ በአከባቢው በማንበር ትልቅ ሥራ እያከናወነ ያለ መኾኑን ከገዳሙ መነኰሳትና ከአገር ሽማግሌዎች ከተሰጡ አስተያየቶች ተደምጠዋል። ክቡር የገዳማችን አበምኔታ መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ወልደ ጊዮርጊስ ከተማ - የተሰጡ ሐሳቦችን አጠናክረው ፥ ከጉባኤ ቤቱ መወጠን አንሥቶ የታሪኩ አካል እንደመኾናቸው መጠን ስለ ጉባኤ ቤቱ አጀማመር ካነሡ በኋላ አኹን ያለበትን ኹኔታ ሲመለከቱ እጅግ የሚገረሙ መኾናቸውን አንሥተው ይኽ ኹሉ የኾነው በእግዚአብሔር አጋዥነት ፣ በብፁዕነታቸው አጋዥነት ፣ በጉባኤ ቤቱ መምህር ትጋት መኽኑን ገልጸዋል። በመጨረሻ ንግግር እና ቃለ ምዕዳን የሰጡት ብፁዕነታቸው - እያዩት ባለው ነገር ፥ በቦታው ያለው ትጋት ፣ የአገልግሎት ፍቅር ፣ ያለኹበት ኹኔታ ይበቃኛል ባለማለት ዕለት ዕለት በመሻሻል [በኹሉም ዘርፍ ራሱን ለማብቃት የሚያደርጋቸው ጥረቶች] እያሳየ ያለውን ራእይ የቀደመው አገልግሎት ያጀበው እንቅስቃሴውን ከማድነቅ ጋር አበረታትተዋል። ቤቱንም ለጉባኤ ቤቱ አሠርተው ያስረከቡ፦ ◆ሕፃን ወለተ-ገብርኤልን ◆ኀይለ-ገብርኤልን ◆ወለተ-ብርሃንን ◆ወለተ-አማኑኤልን የሠሩት ቤተክርስቲያን ለአገልግሎት የምትጠብቃቸው አገልጋዮቿ - ተሠርተው በቅተው ነቅተው የሚወጡበት መኾኑን በማስገንዘብ ፤ ከዚኽ የበለጠ መንፈሳዊ ግብርም አለመኖሩን በማንሣት - አባታዊ ቡራኬን ሰጥተዋል። በመጨረሻም ጉባኤ ቤቱ ፍቅሬን ይገልጽልኛል ብሎ ያዘጋጃቸውን ሥጦታዎች ፥ በብፁዕነታቸው እጅ በሥራው ጉልኽ ድርሻ ለነበራቸው አበርክቷል። ለብፅዕነታቸው (ይመጥናል ብሎ ሳይኾን የልጅነት ፍቅሩን ለመግለጽ) - በግል በአታቸው ቅዱሳት መጻሕፍትን የሚመለከቱባ ስማቸው የተቀረጸባት አትሮንስ እና የሊቁ ቅዱስ ቄርሎስን ድርሳን ጉባኤ ቤቱ አበርክቷል። ለክቡር አባታችን መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ወልደ ጊዮርጊስ - የእጅ መስቀል - እንዲኹም ለተራዱን የገዳሙ አገልጋዮች የመጻሕፍት ሽልማትን በብፁዕነታቸው እጅ ሸልሟል። ቤቱን ላሠሩልን፦ እንደ ሽልማት ሳይኾን ማስታወሻ ይኾናቸዋል ብሎ ያሰባቸውን ስጦታዎች - አበርክቷል። በመጨረሻም የቊልፍ ርክክ ከተደረገ በኋላ በብፁዕነታቸው መሪነት ጉብኝት ተደርጎ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ኹኗል። -------------------------- ጉባኤ ቤቱ "ሰፊ" ከሚባሉ በርካታ ደቀመዛሙርትን ተረክበው ከሚያስተምሩ ቤተ ጉባኤዎች መካከል እየኾነ ያለ ጉባኤ ቤት ነው [በመጽሐፍ ቤት ደረጃ ከ90 በላይ ደቀመዛሙርትን ተቀብሎ ማስተማር መቻል ትልቅ ነገር ነው]። ይኼ ታላቅ ጅምር ቢኾንም «በእግዚአብሔር ፈቃድ» አኹን የተመረቁ ቤቶችን ያካተተ በርከታ የጥናት እና የምርምር ማዕከላትን ያቀፈ ዐጸደ ጉባኤ እንደሚኖረን ባለ - ሙሉ ተስፋ ነን!! ----------------------- ስለኹሉም ነገር የጉባኤ ቤት አምላክ ልዑል እግዚአብሔር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም “ቅዱስ” ብላ የገለጸችው ስሙ ለዘለዓለሙ የተመሰገነ ይኹን!! ─━━━━━⊱✿⊰━━━━━─ ©️ጉባኤ ደብረ ምጥማቅ       13/08/2018 ዓ.ም