fa
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

رفتن به کانال در Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

نمایش بیشتر
3 502
مشترکین
+424 ساعت
+87 روز
+10830 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮጵያን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የአለም አቀፍ ሚስዮን ማህበር ዳይሬተር ቄስ ጥላዬ ዳባ እና እሳቸው የመሩት የሚስዮን ላኪ የስራ ዘርፎች ልዑክ በሰሜን ኬንያ የአገልግሎት ጉብኝት አደረገ * * * * * * የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የአለማቀፍ ሚሲዮን ማህበር የመስክ አግልግሎትን ይበልጥ ዉጤታማ ለማድረግና ሚሲዮናዊያንን ለማበረታታት ብሎም ከታለመለት አንጻር ለመገምገም ላኪ የስራ ዘርፎችን በማስተባበር የመስክ ጉብኝት በሰሜን ኬንያ አድርጎ ተመልሶአል። ይህ ልምድ እያደገ የመጣዉን ይህን አገልግሎት የሚያጠናክር ሲሆን በቀጣይነት መደረግ ስላለበት ስልት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ የጋራ ግንዛቤ ወስደናል። የሚስዮን አገልግሎቱም ጉብኝቱን ተከትሎ ዳይሬክተሩ ባጋሩት መልዕክት "ሚሲዮናዊያን የሚኖሩትን ማየት በጌታ የዳኑ ምእመናንን በእንባ የታጀብ ምስጋና መስማት፣ ወንጌል በአንድ ከበሽታ በተፈወሰ ሰዉ ምክንያት አካባቢዉን ሲያጥለቀልቅ እና ቤተክርስቲያን በየቦታዉ ተተክሎ ከማየት የበለጠ ደስታ ምን አለ?" ብለዋል። ልዑኩም አራት ቀናትን ያስቆጠረ ጉዞ በማድረግ ከምዕመናን ጋር የማምለክ፤ ከሚስዮናውያን ጋር ማዕድ የመካፈል፣ የመፀለይ እና ቀጣይ አገልግሎቶችን አስመልክቶ የመምከር ዕድል አግኝተዋል። በቤተ ክርስቲያኑቱ የአለም አቀፍ ሚስዮን ማህበር በኩል በወንጌል እየተደረሱ ስለሚገኙ በአፍሪካ፣ በኤስያ፣ በላቲን አሜሪካና በመካከለኛ ሩቅ ምራቅ ስላሉ ማህበረሰቦች የሚስዮኑ ባለቤት እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። አገልግሎቱም በተቀረው የአለማችን ክፍል እንዲሰፋ ሁላችንም ስለ አገልግሉቱ እንፀልይ፤ አገልግሎቱንም እንደግፍ።

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ለ8 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት የተሰጠች ሲሆን የሰርትፊኬት የሥነ መለኮት ትምህርታቸውን ያጠናጠናቀቁ 12 አገልጋዮችን በማስመረቅ ወደ አገልግሎት አሰማርታለች። በምዕረብ ግቤ ሲኖዶስ የቃሉንና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ በቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዩናስ ይገዙ ለ8 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት ተሰጥቷል። ፕሬዚዳንቱም በመልዕክታነው እጩ ቀሳውስቱ ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁና በቤተ ክርስቲያኒቱ ለማገልገል ብቁ መሆናቸው የተረጋገጠ መሆኑን በመጥቀስ ነገር ግን እራሳቸውን ለማሳደግና ለምዕመኑ መልካም እረኞች ለመሆን ሁል ጊዜ የሚተጉና የሚማሩ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል። በተመሳሳይ መርሃ ግብር በሲኖዶሱ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ በሰርቲፊኬት ፕሮግራም የሥነ መለኮት እና የአገልግሎት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 12 አገልጋዮች ተመርቀው ወደ አገልግሎት ተሰማርተዋል። በትምህት ቆይታቸውም ጥሩ ውጤት ላመጡ ተመራቂ ተማሪዎች የማበረታቻ ሥጦታ ተበርክቷል። የቤተ ክርስቲያኒቱም የሚስዮንና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል የእግዚአብሔርን ቃል በማስተማር ለእጩ ቀሳውስቱ እና ለተመራቂ ተማሪዎቹ የማበረታቻ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመርሃ ግብሩም የተገኙ የቀድሞ ቀሳውስት እና የሲኖዶሱ መሪዎች ለአገልዩቹ እጅ በመጫን ፀልየዋል። በዕለቱም ለበርካታ አመታት በቤተ ክርስቲያኒቱ ከማህበረ ምዕመናን አንስቶ በተለያዩ ደረጃዎች ያገለገሉት የቄስ በየነ ኩብሩ "የመሪ ጥሪና ሚና" በሚል ርዕስ የተፃፈው መጽሐፍ ተመርቋል። ለምዕመናን ጥበቃና ለቤቱ አገልግሎት አገልጋዮችን የሰጠን ጌታ የተመሰገነ ይሁን!

የምዕራብ ጊቤ ሲኖዶስ 3ኛ መደበኛ ጉባኤ በእርቅ እና አዳዲስ መሪዎችን በመምረጥ በስኬት ተጠናቋል ሲኖዶሱ የጉባኤውን "የመንፈስ አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ 4:3 በሚል መሪ ቃል በሀዲያ ዞን ጊምቢቹ ከተማ ከሐምሌ 10-12 ቀን 2017 ዓ.ም አካሂዷል። የጉባኤው ተሳታፊዎች ባለፉት 4 ዓመታት በሲኖዶሱ የተከናወኑ ተግባራቶችን ከሲኖዶሱ ፕሬዚዳንት መርኀ ንግግር፣ ከጠቅላይ ጸሐፊውና ከዲፖርትመንቶች በቀረቡ ሪፖርት አድምጧል። የጉባኤው ተሳታፊዎችም በቡድኖች ተከፋፍለው በመወያየት የውይይቶቻቸውን ውጤት እና የውሳኔ አቅጣጫዎች ለጉባኤው አቅርበዋል። በተለያዩ አለመግባባቶች ምክንያት ከሲኖዶሱ መዋቅር ተለይተው የነበሩ አራት ሰበኮችና በስራቸው የሚገኙ 56 ማኀበራነ ምዕመናን የነበሩ ችግሮችን በውይይትና በእርቅ በመፍታ ወደ አንድነት መምጣታ ጉባኤውን ልዩ አድጎታል። የቤተ ክርስቲያኒቱም ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ለጉባኤው ማጠቃለያ ባስተላለፉት መልዕክት ተሰናባቹ አመራር በአገልግሎቱ ዘመን ችግሮችን በእርቅ መፍታቱ ታላቅ ስኬት መሆኑን እና ወደ ኋላ በመመልከት የሚያመሰግንበት መሆኑን ገልፀዋል። ጉባኤውም ባካሄደው ምርጫ ለቀጣይ ዓራት ዓመታት ሲኖዶሱን የሚመሩ መሪዎችን የመረጠ ሲሆን፤ በዚህ መሠረት ፦ 1. ቄስ ታምራት ጨቆሬ የሲኖዶሱ ፕሬዚዳንት 2. ቄስ በየነ ኩብሩ የሲኖዶሱ ምክትል ፕሬዚዳንት 3. ገራድ ታደሰ አንሴቦ አቃቤ ንዋይ እንዲሆኑ ተመርጠዋል። የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌልና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል ጉባኤውን ተካፍለዋል። ለአዲሱ አመራር የአገልግሎት ስኬት ቤተ ክርስቲያን ትፀልያለች።

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የፋይናንስ እና አስተዳደር መምሪያ ዓመታዊ የሥልጠና እና የምክክር ስብሰባውን በቤተ ክርስቲያኒቱ ዋና ጽሕፈት ቤት አካሂዷል። በመርሃ ግብሩም ከሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች የመጡ የፋይናንስና አስተዳደር ሀላፊዎች፣ የሲኖዶሶቹ ፀሐፊዎች፣ የጋራ ፕሮግራሞች የፋይናንስ ሀላፊዎች ተካፍለዋል። የቤተ ክርስቲያን የፋይናንስ እና አስተዳደር መምሪያ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰብለ አሰፋ እንደገለፁት የምክክሩ ዓላማ የቤተ ክርስቲያኒቱን የፋይናንስ ሥርዓትና የሀብት አስተዳደር ደረጃውን ጠብቆ እንዲቀጥል፣ ቤተ ከርስቲያ የምትጠቀማነው የፋይናንስ ሥርዓቶች መተግበራቸውን ማረጋገጥ እና ባሳለፍነው የበጀት ዓመት የተስተዋሉ ተግዳሮቶች ላይ ለመምከር መሆኑን ገልፀዋል። አንክሮት በመስጠትም ለውጤታማ የፋይናንስ ሥርዓት ክፍሎቹ የውስጥ ቁጥጥር ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ አሳስበዋል። በተያያዘ መልኩ አጠቃላይ የኦዲት ሪፖርት(Summurized Audit Report)፣ የ2026 በጀት ዝግችት(2026 Budget Proposal) ፣ የሂሳብ ሪፖርት(Financial Report) ፣ የውስጥ ቁጥጥር(Internal Come control) እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ሥልጠናዎች እና ምክክሮች ተካሂደዋል። በስብሰባውም ተጋባዥ ተናጋሪ የነበሩት የቤተ ክርስቲያኒቱ የጡረታ ቦርድ፣ የኢንቨስትመንት እና ኢንሹራንስ ኮምሽን ኮምሽነር የሆኑት አቶ ገመችስ ማቴዎስ "በሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ወቅታዊ የዋጋ ግሽበት(Inflation) እና መደረግ በሚገባቸው ጥንቃቄዎችና ግብረ መልሶች" ዙሪያ ሰፊ ጽሑፍ አቅርበዋል።