fa
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

رفتن به کانال در Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

نمایش بیشتر
3 502
مشترکین
+424 ساعت
+87 روز
+10830 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሚስዩን እና ቲኦሎጂ መምሪያ ከፒ-ኤል-አይ ኢንተርናሽናል(PLI International) ጋር በትብብር የሚሰጠው የመጋቢነት አመራር ሥልጠና የደቡብ ክላስተር፤ ዛሬ በደቡብ ሲኖዶስ አዘጋጅነት በዲላ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል። ሥልጠናውም ላለፉት ሶስት ዓመታት የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችና አገልጋዮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በተለያዩ ዓርዕስት ሥልጠና በመስጠት ሲያበቃ የቆየ ሲሆን የማጠቃለያ ዓመት በሆነው የዓራተኛው ዓመት ሥልጠና "ደቀመዛሙርትን፣ ደቀመዛሙት አድራጊዎችን እና መሪዎችን ማባዛት" በሚል ዋና ዐርስት ላይ መሠረት በማድረግ በመላው ኢትዮጵያ በተለያዩ ክላስተሮች ሥልጠናው በመካሄድ ላይ ይገኛል። በዚህም ክላስተር ሥልጠና በደቡብ ኢትዮጵያ ከሚገኙ 14 ሲኖዶሶች የመጡ በሲኖዶስ፣ በሰበካ እና ማ/ም ጀረጃዎን የሚያገለግሉ መሪዎች እና አገልጋዮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በመካፈል ላይ ይገኛሉ። የቤተ ክርስቲያኒቱም የሚስዩንና ፒኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤልን፣ የአዲስ አበባ ሲኖዶስ ኘሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ጽጌ በረሃ እና የቤ/ክኒቱ የካምፓስ አገልግሎትና ከተማ ወንጌል ማዳረስ የሥራ ክፍል አስተባባሪ የሆኑት ቄስ ወርቁ ኤባ ሥልጠናውን በመስጠት ላይ ይገኛሉ። ሐምሌ 7/ 2017 ዲላ ኢትዮጵያ

ሀገርአቀፍ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መሪዎች የህብረት: የስልጠና: እና የምክክር ጊዜ ተካሄደ === የኢት./ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ አመታዊው ሀገር አቀፍ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መሪዎች የህብረት: የስልጠና: እና የምክክር ጊዜ በጉዲና ቱምሳ ሁለንተናዊ የስልጠና ማዕከል ተካሂዷል፡፡ በምክክሩም ከቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች የተወጣጡ የአገልግሎቱ መሪዎች የተሳተፉ ሲሆን፡ የቤተክርስቲያኒቱ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ዶ/ር ተሾመ አመኑ በምክክሩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። በንግግራቸውም ልጆችና ወጣቶችን የእግዚአብሔርን ቃል እና የቤተ ክርስቲያኒቱን መሰረተ እምነት አስጠብቆ፣ ጊዜውንና ትውልዱን በሚመጥን መልኩ ማሳደግ እና ማብቃት አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት ለዚህም ጠንክሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት መልዕክት አስተላልፈዋል። በፕሮግራሙም እየተሰራበት ባለው ሁለንተናዊ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ ዙርያ ሰፊ የምክክር እና ልምድ ልውውጥ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን፡ ከምክክሩ በኃላ ተሳታፊዎች በሳይንስ ሙዝየም ጉብኝት አድርገዋል። የቤተክርስቲያኒቱ ፕረዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ በፕሮግራሙ ማጠቃለያ በመገኘት በልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ተቀርጾ እየተሰራበት ያለው ፓኬጅ ልጆች እና ወጣቶችን በሁለንተናዊ መልኩ ቀርጾ ለማሳደግ በጣም አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት : ለስኬቱ የአገልግሎቱ መሪዎች እና አስተባባሪዎች በትጋት መስራት እንደሚጠበቅባቸው ምክር ለግሰዋል። በተጨማሪም በምክክሩ በተነሱ አንዳንድ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በፕሮግራሙም እየተሰራበት ባለው ሁለንተናዊ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ ዙርያ የምክክር እና ልምድ ልውውጥ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን፡ ፓኬጁን በማስፈጸም ከፍተኛ: አበረታች እና መልካም ጅማሮ ላሳዩ ሲኖዶሶች የማበረታቻ የምስክር ወረቀት እና ስጦታ ተሰጥቷቸዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ ኡዴሳ አመታዊው የምክክር እና የስልጠና መርሃግብሩ የጋራ ህብረት ያደረጉበት: ውጤታማ ስልጠናዎች የተሰጡበት እና በልጆችና ወጣቶች አገልግሎት ላይ ልምድ ልውውጥ የተደረገበት : እንዲሁም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር የተደረገበት ነበር:: በሳይንስ ሙዚየም በተደረገው ጉብኝትም በ Artificial Intelligence, Climate Effect, Modern Agriculture, Water & Energy & Aviation Technology ጥሩ ግንዛቤ ማግኘት ተችሏል። *** *** *** Yeroo Tokkummaa, Leenjii fi Marii Gaggeessitoota Tajaajajila Ijoollee fi Dargaggootaa Adeemsifame === W/K/W/W/Makaana Yesuus Itoophiyaatti, yeroo Tokkummaa, Leenjii fi Marii Gaggeessitoota Tajaajajila Ijoollee fi Dargaggootaa biyyoolessaa Dhaabbta Leenjii Hundagaleessa Guddinaa Tumsaatti adeemsifameera. Saganticha irrattis sinoodoosii waldattii hundumaarraa daayrektarootnii fi qindeessitootniiq gaggeessitootni tajaajilichaa kan hirmaatan yoo ta’u, Muummicha Barreessaa Waldattii kan ta’an Lubni Dr. Tashoomaa Ammaanuu baniinsa sagantichaa irratti argamuudhaan ergaa dabarsaniiru. Ergaa isaaniitiinis, ijoollee fi dargaggoota Sagalee Waaqayyoo bu’uura tolfachuudhaan, barsiisaa fi eenyummaa Waldaasaanii hubachiisanii; bifa yerichaa fi dhaloota madaaluun guddisuun barbaachisaa ta’uusaa kaasuudhaan, isa kanaafis ciminaan irratti hojjachuun barbaachisaa akka ta’e kaasuun ergaa dabarsaniiru. Saganticha irrattis Paakeejii Hundagaleessa Ijoollee fi Dargaggootaa irratti hojjatamaa jiru irratti yeroo marii fi muuxannoo wal jirjiiruu kan adeemsifame yoo ta’u, sagantaa marii booda immoo hirmaattotni Muuziyeemii Saayinsiittin daawwannaa taasisaniiru. Pirezidaantiin WKWWMYI xumura sagantichaa irratti argamuudhaan, paakeejiin hundagaleessi tajaajila ijoollee fi dargaggootaa ijoollee fi dargaggoota bifa hundagaleessaan guddisuudhaaf baay’ee barbaachisaa ta’uusaa kaasuudhaan, milkaa’ina tajaajila kanaaf gaggeessitootnii fi qindeessitootni tajaajila kanaa kan taatan hundumtuu ciminaan hojjachuun isinirraa eegama jechuun ergaa dabarsaniiru. Dabalataanis haala yeroo tokko tokko irratti ibsa bal’aa kennaniiru. Saganticha irratti, sinoodoosota paakeejicha hojiitti hiikuu irratti hojii adda duree hojjatan, kan sochii gaarii mul’isanii fi jalqabbii gaarii agarsiisaniif waraqaan ragaa fi kennaan kennameeraaf. Daarektarri Qajeelcha Tajaajila Ijoollee fi Dargaggoo Wondmagegn Udessa, sagantichi yeroo tokkummaa fi marii bal’aan kan irratti gaggeeffame, leenjiin bu’a qabeessa ta’es kan itti kenname, yeroon muuxannoo wal jirjiiruus kan itti gaggeeffame, haala yeroo irrattis mariin kan irratti godhame ta'uu ibsaniiru. Daawwannaa muuziyeemii saayinsiitti godhamettis,waa’ee Artificial Intelligence, Climate Effect, Modern Agriculture, Water & Energy, & Aviation Technology irratti hubannaa gaarii argachuun danda’ameera. ''Isa mootummaadhaa fi Waaqayyo abbaa isaatiif luboota akka taanu nu godhate sanaaf, ulfinnii fi aangoon baraa hamma bara baraatti haa ta'u! Ameen.'' Mul'ata 1:6 === EECMY- Annual Consultation of Children & Youth Ministry Directors, & Coordinators @GTWTC #EECMY #DepartmentOfChildrenAndYouthMinistry #MekaneYesus

MYS Announcement! We are thrilled to announce the new intake for the 2025-26 academic year at Mekane Yesus Seminary! Explore our diverse theological study programs, including: - Master of Arts in Theology (with various specializations) - Post-Graduate Diploma in Biblical and Theological Studies - Bachelor of Theology 🔍 Important Dates: - Entrance exams: July 1-4, 2025 - Regular classes start: August 25, 2025 For details on admission requirements and to prepare for your future in theology, check out the full announcement above! 📞 For inquiries, please contact us at: 0911485345 | 0911943347 | 0911089078 | 0917821573 Join us in this journey of faith and education! #MYS #Theology #Education #NewIntake2025

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አመታዊው የልጆች እና ወጣቶች አገልጋዮች የህብረት: የስልጠና እና የምክክር ጊዜ በጉዲና ቱምሳ ሁለንተናዊ የስልጠና ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል:: በምክክሩም ከቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች እና ሥራ ክፍሎች የተወጣጡ የአገልግሎቱ መሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ:: የቤተክርስቲያኒቱ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ዶ/ር ተሾመ አመኑ በምክክሩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፤ ልጆችን እና ወጣቶችን የእግዚአብሔርን ቃል እና የቤተ ክርስቲያኒቱን መሰረተ እምነት አስጠብቆ፣ ጊዜውንና ትውልዱን በሚመጥን መልኩ ማሳደግ እና ማብቃት አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት ለመሪዎቹ መልዕክት አስተላልፈዋል። የቤተ ክርስቲያኒቱም የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ ኡዴሳ ለአመታዊው የምክክር እና የስልጠና መርሃግብሩ ለመሪዎቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በማስተላለፍ፤ ይህ ጊዜ በጉጉት የሚጠበቅ ጊዜ መሆኑን በማንሳት መሪዎቹ በቆይታቸው፤ ባሳለፉት የአገልግሎት አመት ስላጋጠማቸው ተግዳሮቶችና ፈተናዎች የሚመክሩበት፣ ስላሉ መልካም ዕድሎችና ስኬቶች የልምድ ልውውጦችን የሚያደርጉበት እና በየሲኖዶሶቻቸውና የሥራ ክፍላቸው ስለሚኖረው ቀጣይ አገልግሎት ከስልጠናው እና ከምክክሩ አዳዲስ ስልቶችን እና ሃሳቦችን የሚሰንቁበት እንደሚሆን ገልፀዋል። ከምክክሩ በመቀጠል የአገልግሎቱ ዳይሬክተሮችን እና ከየሲኖዶሱ የተወከሉ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት በጎ ፈቃድ አምባሳደሮችን ያሳተፈ ወጣቶችን ለመሪነት የማሳደግ ስልጠና የሚካሄድ ይሆናል።