The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
رفتن به کانال در Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
نمایش بیشتر3 315
مشترکین
+624 ساعت
+197 روز
+10430 روز
آرشیو پست ها
የኢት/ወ/ቤ/ክ መካነ ኢየሱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ዓመት ክብረ በአልን አስመልክቶ ለማህበራነ ምዕመናን ገለፃ ተደረገ
- - - -
በአዲስ አበባ ሲኖዶስ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ስር በሸገር እና አዲስ አበባ ከተሞች ለሚገኙ ማህበራነ ምዕመናን በበዓሉ መርሃግብሮች ዙሪያ ገለፃና ውይይት ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩም መሪ ቄሶች፣ የሽማሌዎች ተወካዮች እና የወጣቶች አገልግሎት አስተባባሪዎች ተካፍለዋል። ለበአሉ አከከባር የሚግዙ ፖስተሮችና መርሃግብሮችን የያዙ ህትመቶች ተከፋፍለዋል።
በዘንድሮው በዓል ለሶስተኛ ዓመት የሚከበረው የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት በወርሃ ሰኔ በድምቀት የሚከበር ሲሆን በያዝነው ዓመት በልዩ ሁሄታ መጽሐፍ ቅዱስ ወደ አፋን ኦሮሞ ቋንቋ በኦኔስሞስ ነሲብ የተተረጎመበትን 125ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በተለያዩ መርሃግብሮች ዓመቱን በሙሉ ይከበራል።
ከበዓሉም ጋር ተያይዞ በመላው የቤተክርስቲያኒቱ ማህበረ ምዕመናን ከግንቦት 11-25, 2016 ባሉ ሶስት ተከታታይ ዕሁዶች 100 ሺ መጽሐፍ ቅዱስ የማሰባሰብ ንቅናቄ ይደረጋል። ለዚህም ንቅናቄ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አንደሚያደርጉ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።
* * * * *
The Orientational program of the EECMY “Year of the Bible” Celebration was held
- - - -
For congregations from Addis Ababa and Central Ethiopia synod with the boundary of Shuger and Addis Ababa cities orientation program was held about the national celebration. Leading pastors, representatives from congregation elders, and youth ministry coordinators participated in the program. To aid the celebration, posters and printed materials are distributed.
This Years, Bible Week, will be celebrated for the third time on the month June, but uniquely because of the 125th celebration of the full Afaan Oromo Bible transition by Onismos Nesib the celebration will be held in different programs throughout the year.
As part of the celebration, 100 thousand Bible collection movements will be held in all EECMY congregations on three consecutive Sundays from May 19-June 2, 2024. Participants of the programs expressed their commitment to the movement.
#EECMY_Bible_Year
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus
የኢት/ወ/ቤ/ክ መካነ ኢየሱስ የምዕራብ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ 49ኛው የሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ስብሰሰባ ከግንቦት 2-3, 2016 ዓ.ም በጋምቤላ ከተማ ተካሄዷል።
- - - - - - -
Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus West Gambella Bethel Synod 49th Executive Board meeting was held at Gambella city from May 10-11, 2024.
የመላ አፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ አመራር ኮሚቴ ስብሰባ ተካሄደ
==
የመላ አፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ አመራር ኮሚቴ ስብሰባ ከሚያዚያ 29-ግንቦት 01: 2016 ዓ.ም በናይሮቢ ኬኒያ ተካሂዷል:: ከስብሰባው ጎን ለጎን 2025 በአዲስ አበባ: ኢትዮጵያ እንዲካሄድ ለተወሰነው 'የመላ አፍሪካ ወጣቶች ኮንግረስ' ከአንድ አንድ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል:: የአመራር ኮሚቴው በአቡጃ ናይጄሪያ በተካሄደው በ12ኛ የመላ አፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ (ከ2024-2028እኤአ) የተመረጠ ሲሆን: የሥራ መመርያ በመቀበል: የተለያዩ የሥራ ክንውን ሪፖርቶችን በመስማት እና ውሳኔዎችን በማሳለፍ : እና በመጨረሻም በቅርቡ በኬኒያ እና አጎራባች ምስራቅ በደረሰው የጎርፍ አደጋን በማስመልከት መግለጫ በማውጣት: እንዲሁም በአንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት የተከሰቱ ግጭቶች እና ጦርነቶች በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ እንዲያገኙ ጥሪ በማቅረብ ተጠናቋል::
===
Walgahiin Koree Hoggansa Yaa'ii Waldoota Kiristaanaa Guutummaa Afrikaa Gaggeeffame.
===
Walgahiin koree hoggansa Yaa’ii Waldoota Kiristaanaa Guutuu Afrikaa Caamsaa 07-08, 2024; Keeniyaa, Naayiroobiitti gaggeeffameera. Walgahichaan cinaatti 'Kongirasii Dargaggoota Afrikaa Hundaa' bara 2025 Finfinnee: Itiyoophiyaatti gaggeeffamuuf qooda fudhattoota muraasa waliin mariin taasifameera. Miseensotni koree hoggansaa kun Yaa’ii Waldoota Kiristaanaa Guutummaa Afrikaa 12ffaa Abuujaa Naayijeeriyaatti gaggeeffame irratti kan filataman yoo ta'u (2024-2028); qajeelfama hojii fudhachuudhaan: gabaasa hojii adda addaa dhaga’uu fi murtiilee garagaraa dabarsuudhaan, fi dhumarratti balaa lolaa dhiheenya kana Keeniyaa fi biyyoota ollaa keessatti mudate ilaalchisee ibsa baasuun, akkasumas waldhabdee fi waraanni biyyoota Afrikaa tokko tokko keessatti uumame karaa nagaa akka furamuuf waamicha dhiyeessuun xumurameera.
===
===
The Governance Committee Meeting of the AACC
===
The meeting of the Governing Committee of the All African Conference of Churches was held from May 07-09, 2024 in Nairobi, Kenya. On the side of the meeting, there was a discussion with the stakeholders about the 'All African Youth Congress' to be held in Addis Ababa: Ethiopia in 2025.
The AACC Governing Committee was elected at the 12th All African Conference of Churches General Assembly(2024-2028) held in Abuja, Nigeria, and: it ended by receiving work orientations: by hearing various program reports and passing different decisions: and finally, by issuing a statement regarding the recent flood disaster in Kenya and the neighboring East: as well as by stating a call to resolve conflicts and wars in some African countries peacefully.
#AACC #AllAfricaConferenceofChurches
የአለም ሉተራን ፌድሪሲዮን ፕሬዚዳንት ቢሾፕ ሄንሪክ እስቱፕጄር እና ልዑካቸው በታንዛኒያዋ አባል ቤተክርስቲያን የነበራቸውን ጉብኝት አጠናቀው ዛሬ አመሻሹን ኢትዮጵያ ገብተዋል። ፕሬዚዳንቱም ቦሌ ኤርፖርት ሲደርሱ በቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
- - - -
Lutheran World Federation President Bishop Henrik Stubjaer and their team arrived in Ethiopia this evening after completing their visit to the Federation member church in Tanzania. Leader of the Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus welcomed the president when he arrived at Bole Airport, Addis Ababa.
The Lutheran World Federation
#LutheranWorld
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የጡረታ ኢንሹራንስና ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ ያስገነባው ባለ ሰባት ወለል ህንጻ አስመረቀ፡፡
በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዝደንት ቄስ ደ/ር ዮናስ ይገዙ፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ተሾመ አመኑ፣ የኮሚሽኑ የቀድሞ እና አዲስ የተመረጡ የቦርድ አባላት፣ የሲኖዶስ ፕሬደንቶች፣ የጋራ ፕሮግራም ዳይሬክተሮች፣ የማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ የሥራ አመራሮች እና ጥሪ የተገኘላቸው እንግዶች በተገኙበት የህንጻው የምረቃ ፕሮግራም በተለያዩ መርሀ ግብሮች በደማቅ ሁኔታ ተከናውኗል፡፡
በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዝደንት ቄስ ደ/ር ዮናስ ይገዙ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የጡረታ ኢንሹራንስና ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በሀዋሳ ከተማ ያስገነባው ባለ ሰባት ወለል ህንጻ እጅግ ዘመናዊ ከመሆኑ ባሻገር ከሚሽኑ ያስቀመጠውን ጡረተኞችን በዘላቂነት የመደገፍ ራዕይ ግቡን እንዲመታ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡
ቤተ ክርስቲያኒቱም ያላትን ሰፊ ልምድ እና ተሞክሮ በመጠቀም በተለያዩ አከባቢዎች እየሰራች የምትገኘውን የገቢ ማስገኛ ግንባታዎችን አጠናክራ እንደምትቀጥልም የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚደንት ቄስ ደ/ር ዮናስ ይገዙ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የጡረታ ኢንሹራንስና ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከሚሽነር የሆኑት ወ/ሮ አባይነሽ በቀለ በሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ የተገነባው ባለ ሰባት ወለል ሕንጻ ቀድሞ ኮሚሽኑን ሲመሩ የነበሩ መሪዎችና የቦርድ አባላት ቦታው ላይ ኢንቨስት በማድረግ በሚገኘው ገቢ የጡረታ ፈንዱን ለመደገፍ እንዲረዳ በማሰብ ወደ ህንጻ ግንባታ በመግባት ለዛሬ ስኬት መድረሱን አስታውቀዋል፡፡
በ1500 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው ይህ በሀዋሳ ከተማ የተገነባው ባለ ሰባት ወለል ሕንጻ ኮሚሽኑ የተለያዩ ኢንቨስትመንት ስራዎች ላይ በመሰማራት ጡረተኞችን በዘላቂነት ለመደገፍ እንደሚያስችልም ወ/ሮ አባይነሽ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የጡረታ ኢንሹራንስና ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አብዲ ፈይሣ በበኩላቸው የቱሪስት ከተማ በሆነችው ሀዋሳ የተገነባው ባለ ሰባት ወለል ሕንጻ ለኮሚሽኑ ከሚያመጣው ገቢ በተጨማሪ ለበርካታ ሰዎች የሥራ እድልም እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል፡፡
ቤተ ክርስቲያኒቱ በቀጣይም ጊዜንና ሁኔታን በማጤን ያላትን ሀብቶች በጥናት በማረጋገጥ የተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ላይ ብትሰማራ አዋጭ መሆኑን አቶ አብዲ ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የጡረታ ኢንሹራንስና ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በሀዋሳ ያስገነባው ባለ ሰባት ወለል ህንጻ ለተለያዩ ስራዎች የሚውሉ ክፍሎች እና ሰማንያ ሁለት የመኝታ ክፍል ያሉት ሲሆን ህንጻውን ገንብቶ አሁን የደረሰበት ደረጃ ለማድረስ ከአንድ መቶ አስር ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
https://t.me/mekaneyesustv
BAGA AYYAANA DARGAGGOOTAA WKWWMYI ISIN GAHE!
“Guddina Hunda-Galeessa Milkaa'ina Hunda-galeessaaf”
Bitootessa 29/2016 ALI (April 07, 2024ALA)
Luqqisii Duree: "Yesuus...Waaqayyoo fi namoota duratti ayyaana argachaa, namummaadhaa fi ogummaatti in guddata ture." Luqaas 2:52
Kaayoo: Dargaggootni keenya bifa hundagaleessaan guddatanii akka milkaa’aniif; hojii babal’isuu Mootummaa Waaqayyoo keessatti gahee isaanii akka bahanuuf, dabalataan ofirra darbanii dhalootaaf eebba ta’uu akka danda’aniif, ayyaanaa fi kennaa addaa Waaqayyo biraa isaaniif kenname adda baafatanii, guddisanii akka itti fayyadamaniif ciminaan isaanirratti hojjachuu...
#Sagantaalee Guyyichatti Raawwataman:- Mata duree kenname irratti barumsa bal'aa kennuu, yeroo faarfannaa, diraamaa fi tapha gaggabaabaa, walaloo fi wal dorgommiilee garagaraa, yeroo kadhannaa, tajaajila dargaggootaa deeggaruudhaaf galii walitta qabuu, saatiin booda taphaa fi wal-dorgommii ispoortii garagaraa... fi kkf.
Waaqayyo tajaajila keenya haa eebbisu!
እንኳን ለኢት./ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ የወጣቶች በዓል አደረሳችሁ!
“ሁለንተናዊ ዕድገት ለሁለንተናዊ ስኬት”
መጋቢት 29፤ 2016 ዓ.ም (April 07, 2024)
መሪ ጥቅስ: "ኢየሱስም... በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።" ሉቃ. 2:52
#ዓላማ:- ወጣቶቻችን በሁለንተናዊ መልኩ እንዲያድጉ እና ለስኬት እንዲበቁ፤ ለእግዚአብሔር መንግስት አገልግሎት አልፎም ለትዉልዱ በረከት እንዲሆኑ፡ ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን መንፈሳዊ ጸጋ እና የተፈጥሮ ችሎታ አውቀው እና አሳድገው እንዲጠቀሙበት...
#የሚከናወኑ ተግባራት:- በዕለቱ ርዕስ ዙርያ: ትምህርት: ዝማሬ: ድራማ እና ጭውውት: ግጥም ጥያቄና መልስ: የጸሎት ጊዜ: የወጣቶችን አገልግሎት ለመደገፍ የገቢ ማሰባሰቢያ : ከሰዓት በኋላ የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች...እና ወዘተ::
እግዚአብሔር አገልግሎታችንን አብዝቶ ይባርክ!
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
