The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
رفتن به کانال در Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
نمایش بیشتر3 291
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+147 روز
+9930 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የወጣቶች በዓል
ከመጋቢት 21- 27/ 2018 ዓ.ም
👉መሪ ጥቅስ፥ ''መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።' ማቴ. 5:16
👉ርዕስ፥ ''ተጽዕኖ ፈጣሪ ህይወት ለሁለንተናዊ አገልግሎት”
👉በሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ማኀበራነ ምዕመናን
#የኢትዮጵያ_ወንጌላዊት_ቤተክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስ_የ2018ዓ_ም #የወጣቶች_በዓል_መልዕክት
👉መሪ ጥቅስ፡ ''መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።'' ማቴ. 5:16
👉ርዕስ፡ ''ተጽዕኖ ፈጣሪ ህይወት ለሁለንተናዊ አገልግሎት”
👉መጋቢት 21- 27, 2018ዓ.ም
#Ergaa_Ayyaana_Dargaggootaa_WKWWMYI_kan_Bara_2018ALI
👉Luqqisii duree: ''Namoonni hojii keessan isa gaarii arganii, Abbaa keessan isa waaqa irraaf ulfina akka kennaniif ifni keessan akkuma kanaatti namoota duratti haa ifu!.'' Maat. 5:16
👉Mata duree: ''Jireenya Dhiibbaa Uumu Tajaajila Hundagaleessaaf''
Bitootessa 21- 27, 2018ALI (April 5, 2026)
#The_EECMY_2026_Youth_Day_Message
👉Leading verse: ''... let your light shine before others, that they may see your good deeds and glorify your Father in heaven.'' Matth. 5:16
👉Theme: 'An Impactful Life For Wholistic Ministry'
👉March 30- April 5, 2026
#EECMY #Youth #Day #የወጣቶች_በዓል #Ayyaana_Dargaggootaa
EECMY Youth Ministry
ዛሬ የዲላ ከተማ ጎዳናዎች እግዚአብሔርን በሚያመሰግኑ ታላላቅ ድምፆች ደምቀው ውለዋል
* * ***
በጌዴኦ ምድር ወንጌል ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰበከበት 77ኛ ዓመት እና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ደቡብ ሲኖዶስ ምስረታ 25ኛ ዓመት ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ በዲላ ከተማ እና በአከባቢዋ የሚኖሩ የመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን አባላት፣ የወንጌል አማኞች፣ የከተማው ነዋሪዎች እና ከፍተኛ የዞኑና የከተማዋ አመራሮች በክልሉ የፖሊሽ ማርሽ ባንድ እየታጀቡ ከዲላ አደባባይ እስከ ሲኖዶሱ ጽሕፈት ቤት የእግር ጉዞ አደረጉ።
በጉዞውም ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የቤተ ክርስቲያኒቱ እና የከተማዋ ከፍተኛ ዓመራሮቸ መልዕክቶችን ያስተላለፉ ሲሆን ወንጌል በብዙ ዋጋ እዚህ መድረሱስ አስታውሰዋል። የጌዴኦን ምድር በወንጌል ለመድረስ ወደ ምድሪቷ በ1941 ዓ.ም የመጡ የኖርዌጂያን ሊተራን ሚስዮን ሚስዮናዊያን አገልግሎት እና በምድሪቷ ብዙ ዋጋ የከፈሉ አባቶች ገድል ታውሷል።
የአተማውም ከንቲባ ዶ/ር መስፍን ደምሴ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በጌዴኦ ዞን ከሰራችው የወንጌል ሥራ ጎን ለጎን በልማት፣ በትምህርት እና ማህበራዊ አገልግሎት ያሳረፈችው አሻራ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል። ለዚህም ውጤት መመዝገብ የአሁን እና የቀደሙ የሲኖዶሱን አመራሮችን አመስግነዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ለ46 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት ሰጠች
* * ***
የቤተ ክርስቲያኒቱን የቃል እና የቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ በደቡብ ሲኖዶስ ዲላ ከተማ ለ46 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት ተሰጥቷል።
ይህንንም የቅስና አሰጣጥ ሥዕአት ልዩ ያደረገው ሲኖዶሱ 25ተኛ የምስረታ በዓል በሚያከብርበት ልዩ መርሃ ግብር ላይ መሆኑን የደቡብ ሲኖዶሱ ፕሬዚዳንት ቄስ ወልዴ አየለ ገልፀዋል።
በዕለቱም የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የቅስና ሀላፊነት ሰጥተዋል። ለእጩ ቀሳውስቱም ባስተላለፉት መልዕክት የቅስና አገልግሎት በሁሉም አውድ ውስጥ የሚሰጥ አገልግሎት እንደሆነ በማንሳ ቀሳውስቱ በሚገኙባቸው ማህበራዊ የግንኙነት ቦታዎች ሁሉ በማስተዋል እንዲገለጡ አሳስበዋል። አክለውም የአገልግሎቱ ጥሪ በሚጠይቀው መሠረት የቤተ ክርስቲያኒቱን የመሰዊያ እና የምስባክ አገልግሎት በታማኝነት እንዲያገለግሉ እና እንዲያስጠብቁ አሳስበዋል።
በቅስና አሰጣጥ ሥርዓቱ ላይ የቤተ ክርስቲያኒቱ እና የሲኖዶሱ መሪዎችና የሥራ ክፍል ሀላፊዎች ለእጩ ቀሳውስቱ ፀሎት አድርገዋል።
ለመከሩ አገልግሎት አገልጋዮችን የሰጠን ጌታ የተመሠገነ ይሁን።
ሁለንተናዊ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት ስልጠና
በምዕራብ ሲኖዶስ ተሰጠ
* *
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ከምዕራብ ሲኖዶስ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ስልጠና በሲኖዶሱ ማዕከል ምዕራብ ወለጋ ዞን ቦጂ/ ቢላ ከተማ ተሰጥቷል::
ስልጠናው 'ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ወጣቶቻችን' በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሲሆን የምዕራብ ሲኖዶስ መሪዎች፣ ከሰበካዎች እና ማ/ምዕመናናት የተወጣጡ መሪዎች እና የልጆችና ወጣቶች አገልጋዮች ተሳትፈዋል።
በስልጠናው ለተሳተፉት ሰልጣኞች ለልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት የሚጠቅሙ: ታቅዶ እየተሰራበት ላለው ቤተመጻህፍትን በእያንዳንዱ ማህበረ ምዕመናን የማስጀመር ራዕይ የሚረዱ የልጆች መጽሐፍ ቅዱሶች፤ የወጣቶች ማስተማርያ መጽሐፍቶች፤ ለአገልጋዮች እና ምዕመናን እና ለሌሎች ለቤተክርስቲያን ስነ መለኮታዊ አስተምህሮ የሚረዱ የተለያዩ መጽሐፍቶች በመምሪያው በኩል በድጋፍ መልክ ተሰጥቷቸዋል::
ስልጠናውን የሰጡት የቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ወንድማገኝ ኡዴሣ የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለቤተክርስቲያኒቱ ድጋፍ ያደረጉትን ተቋማት 'Rafiki Foundation' fi 'Lutheran Heritage Foundation' ናቸው። ዳይሬክተሩም ተቋማትን በማመስገን መጽሐፍቶቹን ለቤተክርስቲያኒቱ ማ/ምዕመናናት፣ ሴሚናሪዎች፣ መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጆች እና ት/ቤቶች ከተባባሪ ድርጅቶች ጋር በመሆን ድጋፍ የማድረጉ ስራ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የሲኖዶሱ ፕረዚዳንት ቄስ ታምሩ ታደሰ ስልጠናው የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎትን ጊዜው በሚፈልግ መልኩ ለማሳደግ አስፈላጊ እና ወቅቱን ያገናዘበ መሆኑን ገልጸዋል። ሰልጣኞችም በወሰዱት ስልጠና መሰረት በታማኝነት እና በትጋት መስራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው መልዕክት አስተላልፈዋል::
ከስልጠናው በኃላም በቦጂ ብርመጂ ማ/ምዕመናን ሁሉንም ምዕመናን ያሳተፈ ሁሉን አቀፍ ኮንፈረንስ ተካሂዷል።
ለተቀሩት ሲኖዶሶችም ተመሳሳይ ስልጠና ከሲኖዶሶች ጋር በመተባበር የሚሰጥ ይሆናል::
_ _ _
Leenjiin Tajaajila Ijoollee fi Dargaggootaa
Sinoodoosii Dhihaatti kenname.
* *
Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Itoophiyaatti, leenjiin karaa Qajeelcha Tajaajila Ijoollee fi Dargaggootaatii fi Sinoodoosii Dhihaatiin qophaa'e giddugala sinoodoosichaa kan taate Godina Wallagga Lixaa Boojjii Birmajjii/Biilaatti kennameera.
Leenjichi mata duree 'Guddina Hundagaleessa Ijoollee fi Dargaggoota Keenyaaf' jedhuun kan qophaa'e yoo ta'e, leenjicha irratti geggeessitootni sinoodoosichaa, kan sabakootaa fi waldaa amantootaarraa dhufan, akkasumas tajaajiltootni ijoollee fi dargaggootaa hirmaataniiru.
Leenjifamtoota leenjii kana irratti hirmaataniif tajaajila ijoollee fi dargaggootaaf kan fayyadan, akkaataa karoorfamee irratti hojjatamaa jiruun Manneen Kitaabaa Waldaa Amantootaa hundumaatti jalqabsiisuuf kan gargaaran, kitaabileen tajaajila ijoollee fi dargaggootaaf, akkasumas tajaajiltootaa fi amantootaaf gargaaranii fi barsiisa bu'uura amantii Kiristaanaatiif kan gargaaran garagaraa karaa qajeelchichaatiin bifa deeggarsaatiin kennameefii jira.
Leenjicha kan kennan Daarektara Qajeelcha Tajaajila Ijoollee fi Dargaggootaa WKWWMYI kan ta'an Lubni Wondmagegn Udessa, dhaabbilee kitaabota hafuuraa tajaajila ijoollee fi dargaggootaa gargaaran garagaraatiin kan deeggarsa Waldattiif taasisan Dhaabbata 'Lutheran Heritage Foundation' fi 'Rafiki Foundation' galateeffataniiru.
Pirezidaantii Sinodosichaa kan ta'an Lubni Taammiruu Taaddasaa leenjicha irratti hirmaachuudhaan, tajaajila ijoollee fi dargaggootaa akka yeroon gaafatutti guddisuuf leenjichi barbaachisaa fi murteessaa ta'uu erga ibsaniin booda, leenjifamtootni leenjii fudhatan kana hojiitti akka hiikan cimsanii ergaa dabarsaniiru. Leenjicha boodas koonfiraansiin amantoota hundumaa hirmaachise Waldaa Amantoota Boojjii Birmajjiitti adeemsifameera.
Leenjiin wal fakkaataan sinoodoosoota kan biroottis walta’iinsaan kennamuu kan itti fufu ta'a.
===
📷 Abrham
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
