The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
رفتن به کانال در Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
نمایش بیشتر3 497
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+157 روز
+11030 روز
آرشیو پست ها
በአባታችን ቄስ ስምዖን ሞቻ ዜና ዕረፍት የተሰማንን ሀዘን እንገልጻለን።
* * ***
“ከሰማይም፦ ከእንግዲህ ወዲህ በጌታ የሚሞቱ ሙታን ብፁዓን ናቸው። መንፈስ፦ አዎን፥ ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ፥ ሥራቸውም ይከተላቸዋል ይላል ብለህ ጻፍ የሚል ድምፅ ሰማሁ።” ራእይ 14፥13
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስን በብሔራዊ ደረጃና በበርካታ የሲኖዶስ ሀላፊነቶች በቅንነትና ታማኝነት ሲያገለግሉ የነበሩት፤ የቄስ ስምዖን ዜና እረፍትን በታላቅ ሀዘን ሰምተናል።
አባታችን ቄስ ስምዖን የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስን በምክትል ፕሬዚዳንት፤ ዋና ኮሚቴ አባልነት፤ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባልነት፤ እንዲሁል በማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ በምክትል ፕሬዚዳንትነት፤ የወንጌል ተልዕኮና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተርነት የአገልግሎት ሀላፊነቶች ቤተ ክርስቲያንን አገልግለዋል።
በተጨሪም አባታችን የአማሮና አከባቢው ሲኖዶስ የመጀመሪ ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉ ሲሆን፤ በጡረታ ጊዜያቸውም በምክርና አቅጣጫን በማሳየት የአባትንት ሀላፊነታቸውን እየተወጡ በነበሩበት ጊዜ ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ወደሚወዱትና ወዳገለግሉት ጌታ ሄደዋል።
ቄስ ስምዖኝ በአማሮ፤ በቡርጂ እና በበርካታ የደቡብ ኢትዮጵያ አከባቢዎች የእግዚአብሔር ቃል ያስተናሩ የወንጌል አርባኛ ነበሩ።
የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ነገ በኬሌ ከተማ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን የሚፈጸም ይሆናል።
ለቤተሰባቸው፤ ወዳጅ ዘመዶች፤ ላገለገሏቸው ምዕመናን እና ለሁላችን እግዚአብሔር መጽናናቱን ይስጠን!
ሁሉን አቀፍ የናቪሽን የሂሳብ አስተዳደር ስልጠና ተሰጠ።
* * * * * *
የኢትዮጲያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በአስተዳደር እና ፋይናንስ መምሪያ የተዘጋጀው የናቬሽን የሂሳብ አስተዳደር ስልጠና በስኬት ተካሂዷል። በስልጠናውም ከቤተ ክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች እና የጋራ ተቋማት የመጡ የሂሳብ ባለሙያዎች እና የመምሪያ ዳይሬክተሮች ተካፍለዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ የአስተዳደር እና ፋይናንስ መምሪያ ዳይሬክተ ወ/ሮ ሰብለ ገመችስ በመዝጊያ ንግግራቸው የሥልጠናው ዋና አላማ የሂሳብ ባለሙያዎቹ የሂሳብ ነክ መረጃዎችን በአግባቡ እንዲመዘግብ፤ የቁጥጥርና ጊዜውን የጠበቀ ሪፓርቲንግን ክህሎትን እንዲያዳብሩ መሆኑን የገልፀዋል። አያይዘውም የስልጠናውን ውጤት ማረጋገጥ እንዲያስችል ተግራዊ የሶፍትዌር አጠቃቀም ስልጠና መሰጠቱን አክለዋል።
ሰልጣኞቹም በስልጠናው ከወሰዱት እውቀት ባሻገር በውይይት እና የጥያቄና መልስ ክፍለ ጊዜ ብዙ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልፀዋል።
በመካነ ኢየሱስ ሴሚናሪዮም ቻፕል በተካሄደው ስልጠና ማጠቃለ ለስልጠናው ተካፋዮች የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምክክር አውደ ጥናት ዛሬ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
* * * * * *
የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥነ መለኮት አቋም ማስጠበቅ፤ የአምልኮ ሥርዓተ ጥንቃቄ፤ ሐሰተኛ ትምህርቶችን እና ልምምዶችን መከላከል ላይ ያተኮረው የመሪዎች አውደ ጥናት በጉዲና ቱምሳ ሁለገብ የሥልጣና ማዕከል ባሳለፍነው ዕለት መካሄድ ጀምሯል። በዚህም አውደ ጥናት የሲኖዶስ ፕሬዚዳንቶች፤ ዋና ፀሐፊዎችና የወንጌል ተልዕኮና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተሮች እና ከጋራ ተቋማት የመጡ መሪዎች እየተሳተፉበት ይገኛል።
አውደ ጥናቱን ያዘጋጀው የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልዕኮና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ጥላዬ ከበደ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የምክክር አውደ ጥናቱን አላማ የገለፁ ሲሆን ይህንን የጋራ ጊዜ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና አገልጋዮች እያጋጠሙ ባሉ ውጫዊ ተፅዕኖዎች እና ሊደረጉ በሚገቡ ጥንቃቄዎች ዙሪያ የሚመክሩበት ሰፊ እድል እንደሆነ ገልጸዋል።
በአውደ ጥናቱ ወቅታዊነትና ጠቀሜታ ዙሪያ አጽንዖት በመስጠት ተሳታፊዎች በትኩረት በመከታተል ግብአት በመስጠት አስተዋፆ እንዲያደርጉ ፣ እስከ ማህበረ ምዕመናን በማዉረድ የምክክሩ ዉጤቶች እንዲተገበሩ የቤተ ክርስቲያኒቱ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ዶ/ር ተሾመ አመኑ አሳስበዋል።
አዉደ ጥናቱ በተለያዩ ርዕሶች ላይ ከመምሪያዉ ባልደረቦች ለዉይይት መነሻ የሚሆኑ ፁሑፎች የሚቀርቡ ሲሆን በማለዳውም ክፍለ ጊዜ የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳ "የብልጽግና ወንጌል በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ እያደረሰ ያለዉ ተጽዕኖ" በሚል ርዕስ ሰፊ ጽሑፍ አቅርበዋል።
በተያያዘ መልኩ በዚህ አውደ ጥናት ለመካፈል በአሜሪካ ሐገር ኪንታኪ ከተማ ከምትገኘዉ የሄብሮን ሉተራዊት ማህበረ ምዕመናን የመጡ አገልጋዩች ሰላምታ አቅርበዋል።
አውደ ጥናቱም በተዘጋጀለት የፕሮግራም ሰሌዳ እንደሚቀጥል ከመምሪያው ለመረዳት ተችሏል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ለ33 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት ሰጠች
* * ***
የቤተ ክርስቲያኒቱን የቃል እና የቅዱሳት ሚስጥራዊ አገልግሎት እንዲያግዝ፤ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ፤ ማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ለ33 አገልጋዮች የቅስ ሀላፊነት ሰጥቷል።
ይህም ሥነ-ሥርዓት በሀዋሳ ከተማ ሪፈራል ማህበረ ምዕመናን የተካሄደ ሲሆን የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልእኮና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ጥላዬ ከበደ የእግዚአብሔርን ቃል ለጉባኤው በማስተማር የቅስና አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓቱን መርተዋል።
የማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ሰፊ የቆዳ ስፋት በመሸፈን አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲኖዶስ ሲሆን በርካታ ሲኖዶሶችንም አፍርቷል። አዳዲስ ቀሳውስቱም ወደ መጡባቸው ማኀበራነ ምዕመናን ተመልሰው በሚሰጧቸው አገልግሎች በሲኖዶሱ የሚታየውን የቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት አጥረት በጉልህ እንደሚቀንስ ይታመናል።
የማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ በአሁኑ ሰዓት በ978 ማኀበራ ምዕምናን እና በርካታ የወንጌል ስብከት ጣቢያዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። የሲኖዶሱም ፕሬዚዳንት ቄስ እያሱ ጠጊቾ በሲኖዶሱ የሚሰጠውን የእረኝነት አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ አገልጋዮች በሴሚናሪ ትምህርት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በዕለቱም የሲኖዶሱ ማኔጅመንት፤ የሰበካ ተጠሪዎች፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የእጩ ቀሳውስት ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ለመከሩ አገልግሎት ታማኝ አገልጋዮችን የጨመረልን እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን።
ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም
ሐዋሳ፤ ኢትዮጵያዊ
ፎቶ - EECMY Referal Congregation
