fa
Feedback
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማኅበር - Ethiopian Federal Advocate's Association (EFAA)

የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማኅበር - Ethiopian Federal Advocate's Association (EFAA)

رفتن به کانال در Telegram

ይህ በአዋጅ ቁጥር 1249/2013 አንቀጽ 57 ጥር 15 ቀን 2014 ዓ.ም የተቋቋመው የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማኅበር ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው።

نمایش بیشتر
6 275
مشترکین
+124 ساعت
-117 روز
-4830 روز
آرشیو پست ها
የአስተዳደር_ተቆጣጣሪ_እና_አገልግሎት_ሰጪ_ተቋማትን_የሚመለከቱ_ጥያቄዎች.docx0.28 KB

የፍትህ_አካላትን_የሚመለከቱ_ጥያቄዎች.docx0.27 KB

ለተቋማዊ ውይይት አጀንዳ ቀረጻ ለአባላት የቀረበ መጠይቅ የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር (EFAA) ከፍትህ አካላት ፣ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም ከሌሎች ጠበቆች በስራቸው አጋጣሚ ከሚጎበኟቸው አካላት ጋር በመርህ ላይ የተመሰረተ ተቋማዊ ውይይት ለማካሄድ በሂደት ላይ ነው። ለዚህ ዝግጅት ይረዳም ዘንድ ይህ መጠይቅ ተዘጋጅቷል። የዚህ መጠይቅ ዋና ዓላማ የአባላትን ሙያዊ አስተያየት ለማሰባሰብ ፣ በልምድ ላይ የተመሠረቱ ግንዛቤዎችን ለመጋራት እና ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በተመለከተ ምክረ ሃሳብ ለማግኘት ነው ። እነዚህም ማህበሩ ተቋማዊ ግንኙነቱን የሚቃኝበት ማዕቀፎች ይሆናሉ። ይህ መጠይቅ የተዘጋጀው ማህበሩ በቀጣይ ለሚያደርገው የትብብር ፣ የውይይት እና የተቀናጀ የለውጥ ጥረት አጀንዳዎችን መለየት እንጂ አባላት በገጠሟቸው ጉዳይ-በጉዳይ ላይ የተመሰረቱ ቅሬታዎችን ለማሰባሰብ አይደለም። በመሆኑም አባላት ተቋማዊ እና አጠቃላይ አሰራርን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ያተኩሩ ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን ። ማህበሩ ያለአባላቱ ንቁ ተሳትፎ አንዲት ጋት ወደፊት ሊራመድ እንደማይችል የታወቀ ነው ። ተሳትፎአችን ከሚረጋገጥባቸው ሁኔታዎች ውስጥ ደግሞ እንዲህ ላሉ መጠይቆች የምንሰጠው ወቅታዊ ምላሽ ነው ። በመሆኑም ይህን መጠይቅ ከዚህ በታች ያለውን “ፋይል” በማውረድ ወደ “PDF” በመቀየር በማህበሩ ኦፊሴላዊ የኢሜይል አድራሻ info@efaa.et ወይም https://forms.office.com/r/Ds4PpHH8My እና https://forms.office.com/r/hEP39gdErX ሁለቱን ሊንኮቹን በመጫን ቅጾቹን በቀጥታ በመሙላት እስከ ጥር 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲልኩልን በአክብሮት እንጠይቃለን። የኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ማህበር የፕሬዚደንት ጽ/ቤት ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም.

የፌዴራል ጠበቆች ስፓርት ቡድን ጨዋታ ድጋፍ የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች የጤናና ስፖርት ማህበር ከኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ጋር ከአንድ ዓመት በላይ በመተባበር እየሰራ ቆይቷል ። የአካል ብ
የፌዴራል ጠበቆች ስፓርት ቡድን ጨዋታ ድጋፍ የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች የጤናና ስፖርት ማህበር ከኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ጋር ከአንድ ዓመት በላይ በመተባበር እየሰራ ቆይቷል ። የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና ስፖርት የጠበቆችን የአካልና የአእምሮ ጤና ለመጠበቅ ፣ የሙያ ጫናን ለመቀነስ እና በጠበቆች መካከል አንድነትን ለማጠናከር አስፈላጊ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች የጤናና ስፖርት ማህበር በአዲስ አበባ ከተማ በሚካሄድ የስፖርት ውድድር እየተሳተፈ ሲሆን ፣ የመጀመሪያ የነጥብ ጨዋታውን ነገ ቅዳሜ ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡30 ላይ ከኤርፖርት ጉሙሩክ ጋር ያደርጋል። በመሆኑም ፣ ሁሉም አባላት በ6 ኪሎ FBE ካምፓስ ሜዳ በመገኘት ድጋፋችሁን እንድታሳዩ በክብር ይጋብዛል። የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም.

የኮሚቴ አባላት ምዝገባ የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር በመተዳደሪያ ደንቡ መሰረት እንዲቋቋሙ በተወሰኑት 9 ኮሚቴዎች ላይ ለመሳተፍ ፍቃደኛ የሆኑ አባላት እንዲመዘገቡ ጥሪ ማድረጋችን ይታወቃል።
የኮሚቴ አባላት ምዝገባ የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር በመተዳደሪያ ደንቡ መሰረት እንዲቋቋሙ በተወሰኑት 9 ኮሚቴዎች ላይ ለመሳተፍ ፍቃደኛ የሆኑ አባላት እንዲመዘገቡ ጥሪ ማድረጋችን ይታወቃል። ማህበሩ በድጋሚ ጥሪ ለማደረግ የተገደደው ከዚህ በፊት በተደረገው ጥሪ መሰረት የተመዘገቡት አባላት ቁጥር አነስተኛ እና በጥቂት የኮሚቴ ኃላፊነቶች ላይ ብቻ በመሆኑ ነው ። በመሆኑም እስካሁን ያልተመዘገባችሁ አባላት የምዝገባው ግዜ ከመጠናቀቁ በፊት በፍላጎት ፣ በሙያዊ ችሎታ እና በጊዜ አቅም መሠረት እንድትመዘገቡ አሁንም ጥሪ እናቀርባለን ። ንቁ ተሳትፎአችሁ አይለየን። የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም

የቋሚ_ኮሚቴ_አባልነት_መመዝገቢያ_ቅጽ.docx0.18 KB

የተሳትፎ ጥሪ የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም ባጸደቀው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ፣ የቆይታ ጊዜያቸው ሶስት (3) ዓመት የሆኑ ዘጠኝ (9) ቋሚ ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙ መወሰኑ ይታወቃል፡፡ እነዚህ ቋሚ ኮሚቴዎች ማህበሩ በህግ የተሰጠውን ተልእኮ በተግባር ለማሳካት ወሳኝ ሚና ያላቸው በመሆናቸው ፣ በኮሚቴዎቹ ውስጥ በተግባር በንቁ ተሳትፎ ለማገልገል ፍቃደኛ የሆናችሁ አባላት ከዚህ ጋር በተያያዘው የመመዝገቢያ ቅጽ እንድትመዘገቡ እንጠይቃለን፡፡ የቋሚ ኮሚቴ አባልነት የጊዜ መስጠት ፣ እንዲያከናውኑ የተሰጡን ስራዎች በተሰጠው የግዜ ማዕቀፍ ማከናወንን የሚጠይቁ ፣ እንደአባል ለሙያችን የምናሳየውን መሰጠት በተግባር የምናረጋግጥባቸው ናቸው ። የቋሚ ኮሚቴዎች ዝርዝር 1. የሕግ ትምህርት፣ ምርምርና ስልጠና ጉዳዮች ኮሚቴ 2. የደንበኞች አደራ ሒሳብ ጉዳዮች ኮሚቴ 3. የደንበኞችና የመደበኛ አባላት ግንኙነት ጉዳይ ኮሚቴ 4. የሕግ የበላይነት እና የሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ኮሚቴ 5. የፍትሕ አካላት ግንኙነት ጉዳይ ኮሚቴ 6. ነጻ የህግ አገልግሎት ጉዳይ ኮሚቴ 7. የሥርአተ ጾታ እና አካታችነት ጉዳይ ኮሚቴ 8. የእውቅና እና የምስጋና ጉዳይ ኮሚቴ 9. የማህበራዊ ግንኙነቶች ጉዳይ ኮሚቴ በመሆኑም አባላት በፍላጎት ፣ በሙያዊ ችሎታ እና በጊዜ አቅም መሠረት ተገቢ የሚመስላቸውን ኮሚቴ በመምረጥ ፣ ይህ ማስታወቂያ ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ በሰባት (7) ቀናት ውስጥ ከዚህ በታች የተያያዘውን የመመዝገቢያ ቅጽ በማውረድ ምላሻችሁን በWord ወይም PDF (Scan የተደረገ) በማህበሩ ኦፊሴላዊ የኢሜይል አድራሻ info@efaa.et ወይም https://forms.office.com/r/jiQDPuuJDq ሊንክ በመጫን የመመዝገቢያ ቅጹን በቀጥታ በመሙላት እንዲመዘገቡ አክብሮት እንጠይቃለን። ለጊዜያችሁና ለንቁ ተሳትፎአችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው። የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የፌዴራል_ጠበቆች_ማህበር_የሙያ_ስራ_የተቀናሸ_ወጪዎች_ጥናት_ቡድን_የተዘጋጀ_መጠይቅ_.docx2.33 KB

የተሳትፎ ጥሪ ለአባላት የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ከዚህ ቀደም ለእናንተ ባቀረበው ዝማኔ ኩነት ላይ እንደገለጸው እንደጠበቆች እና ህግ አማካሪዎች የሙያ አገልግሎት በመስጠት ስራ ላይ ለተሰማሩ ግብር ከፋዮች የሚሆን የተቀናሽ ወጪዎች አያያዝ መመሪያ ለማዘጋጀት የሚያገለግል የጥናት ሰነድ ለማቅረብ ኀላፊነት መውሰዱ ይታወቃል ። ለዚህ ኃላፊነት የተመደቡ ባልደረቦቻችንም ከዚህ በፊት በማህበራችን እና በአባላቱ የተከናወኑ ጥናቶችን ፣ ተዛማጅ ሕጎችን እና ዓለምአቀፍ ተሞክሮዎችን በማሰባሰብና በመመርመር ስራቸውን በማከናወን ላይ ይገኛሉ። በዚህም ሂደት የጥናቱን ጥራት ለማሻሻል ከአባላት ተጨማሪ መረጃና አስተያየት መሰብሰብ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተውታል ። ለዚህም እንዲረዳ የጥናት መጠይቅ አዘጋጅተው ለማህበሩ አቅርበዋል ። ለጥናቱ ውጤታማነት የማህበሩ የአባላት ተሳትፎ ተገቢ መሆኑን በማመን መጠይቁ እንዲደርሳችሁ ለማድረግ ወስኗል። በመሆኑም ለመጠይቆቹ ያላችሁን ምላሽ እስከ ጥር 10/2018 ዓ.ም ድረስ ከዚህ በታች በተጠቀሱት አማራጮች እንድትልኩ በአክብሮት እንጠይቃለን፦ ፩. ከዚህ በታች የተያያዘውን ፋይል በማውረድ ምላሻችሁን በWord ወይም PDF (Scan የተደረገ) በማህበሩ ኦፊሴላዊ የኢሜይል አድራሻ info@efaa.et ወይም በኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ማህበር የቴሌግራም ቻነል - EFAA Members Forum (https://t.me/+M5yXp_1p6JsyMjk8) ላይ በመግባት አጣብቆ በመላክ ፣ ፪. የቀረበውን የሕግ ባለሙያዎች ተቀናሽ ወጪዎች ዳሰሳ መጠይቅ – ኢትዮጵያ (2) – Fill out form https://forms.office.com/r/8J2uaHekmh ሊንክ በመጫን ወይም QR Code በመስካን የ «የሕግ ባለሙያዎች ተቀናሽ ወጪዎች ዳሰሳ መጠይቅ – ኢትዮጵያ» ቅጹን በቀጥታ በመሙላት ፣ ለጊዜያችሁና ለንቁ ተሳትፎአችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው። የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ጥር 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ማሳሰቢያ ከኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማሕበር የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማሕበር 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን መስከረም 27/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ማካሄዱ ይታወሳል። በዚህም ለጠቅላላ ጉባኤው ቀርበው ከፀደቁት ደንብና መመሪያዎች መካከል "የአባላት ክፍያ መመሪያ” ይገኝበታል፡፡ በዚሁ መሠረት ረቂቅ መመሪያው በጉባኤው አባላት በአብላጫ ድምጽ የፀደቀ በመሆኑ ይህ መመሪያ ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ አባላት በፀደቀው የክፍያ መመሪያ መሰረት የክፍያው አፈፃፀም እንደሚከተለው መሆኑን እንገልፃለን። 1) በመመሪያው አንቀጽ 6 (1) መሰረት ዓመታዊ የመዋጮ ገንዘብ መጠን ብር 3000(ሦስት ሺ ብር) ሲሆን፤ 2) የሚከፈልበት አግባብ በአንቀጽ 6(2) ፈቃድ በሚታደስበት ወቅት በአንድ ግዜ ሲሆን (ወደፊት ማህበሩ የሚያወጣው የክፍያ አሰባሰብ እንደተጠበቀ ሆኖ)፤ 3) በፀደቀው መመሪያ አንቀጽ 6(3) መሰረት የጥብቅና ድርጅት በራሱ እንደ አንድ አባል ክፍያ የሚፈፅም ሲሆን ይህም ሁሉም የጥብቅና ድርጅቱ አባል የፌደራል ጠበቆችን ዓመታዊ የክፍያ መዋጮ ግዴታን የማያስቀር መሆኑን እንገልፃለን። በመሆኑም ይህ የክፍያ መመሪያ ከፀደቀበት ቀን ጀምሮ ሁሉም የማህበሩ አባላት የክፍያ ግዴታቸውን እንዲወጡ እያሳሰብን ይህንን ተግባራዊ ላላደረጉ አባላት የፍቃድ እድሳትን ጨምሮ ማናቸውም አገልግሎት የማይሰጣቸው መሆኑን እናሳውቃለን።