የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማኅበር - Ethiopian Federal Advocate's Association (EFAA)
Ir al canal en Telegram
ይህ በአዋጅ ቁጥር 1249/2013 አንቀጽ 57 ጥር 15 ቀን 2014 ዓ.ም የተቋቋመው የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማኅበር ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው።
Mostrar más6 279
Suscriptores
+924 horas
+137 días
+1630 días
Archivo de publicaciones
Earlier this month, the Ethiopian Federal Advocates Association (EFAA), represented by its President, Tesfaye Deresse, took part in the regional consultations held during the East Africa Law Society (Official) Bar Leaders Council meeting in Diani, Kenya.
Bar leaders from across the region discussed shared priorities, including the independence of Bars, the role of professional associations in safeguarding the rule of law, and the emerging impact of artificial intelligence on justice systems.
EFAA’s active participation reflects its commitment to mutual learning, professional self‑regulation, and constructive regional collaboration.
Prior to the Bar Leaders Council meeting in Diani, President Tesfaye—together with the EALS President Ramadhan Abubakar, MBS Abubakar and fellow Council members participated in an important engagement in Nairobi, where the delegation held a significant meeting with H.E. William Samoei Ruto, PhD, President of the Republic of Kenya, at State House.
The discussion highlighted the vital role of the East Africa Law Society (EALS) in promoting the rule of law, strengthening cross‑border legal practice, and deepening cooperation among East African Bars.
We extend our sincere appreciation to EALS for facilitating these impactful and forward‑looking engagements.
This marks a promising start to the year, and the new EFAA leadership remains committed to strengthening its partnership with EALS and expanding collaboration with regional and global Bar associations.
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር (EFAA) በምስራቅ አፍሪካ የሕግ ማህበረሰብ (EALS) ምክር ቤት የምክክር መድረክ ላይ ላይ ተሳተፈ ፣
በዚህ ወር አጋማሽ ላይ የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር (EFAA) ፕሬዝዳንት አቶ ተስፋዬ ደረሰ ፣ በዲያኒ ኬንያ በተካሄደው የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ምክር ቤት ከሌሎች የማህበራት መሪዎች ጋር በቀጠናዊ ምክክር መድረክ ላይ ተሳትፈዋል።
በዚህም መድረኩ ላይ የቀጠናው የጠበቆች ማህበራት መሪዎች በጋራ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል ። ከነዚህም መካከል የምክክር መድረክ ላይ የጠበቆች ማህበራት ነጻነት ፣ የህግ የበላይነትን በሚመለከት ሊኖራቸው ስለሚገባ ጉልህ ሚና እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ለህግ አገልግሎት ያመጣውን ትሩፋት እና የደቀነውን ስጋት በተመለከተ ውይይት ተደርጓል። የኢ.ፌ.ጠ.ማ (EFAA) ንቁ ተሳትፎ ማህበሩ ለጋራ ትምህርት፣ ለሙያዊ የራስ-ቁጥጥር እና ለአዎንታዊ ቀጠናዊ ትብብር ያለውን ቁርጠኝነት የሚያንጸባርቅ ነው።
በዲያኒ ከተካሄደው የመሪዎች ምክር ቤት ስብሰባ አስቀድሞ፣ ፕሬዝዳንት ተስፋዬ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ (EALS) ፕሬዝዳንት ረመዳን አቡበከር እና ከሌሎች የምክር ቤቱ አባላት ጋር በመሆን በናይሮቢ በተካሄደው ጠቃሚ መርሃ-ግብር ላይ ተሳትፈዋል። በዚህም ልዑኩ በኬንያ ብሔራዊ ቤተ-መንግስት (State House) ከኬንያ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶ/ር ዊሊያም ሳሞይ ሩቶ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርጓል።
ውይይቱም የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ (EALS) የሕግ የበላይነትን ለማስፈን ፣ ድንበር ተሻጋሪ የሕግ አገልግሎትን ለማጠናከር እና በምስራቅ አፍሪካ የጠበቆች ማህበራት መካከል ያለውን ትብብር ለማሳደግ ያለውን ወሳኝ ሚና ያጎላ ነበር።
እነዚህን ተፅዕኖ ፈጣሪ እና ወደፊት ተመልካች የሆኑ መድረኮችን ላመቻቸዉ የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ (EALS) ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ይህ ለማህበሩ ተስፋ ሰጪ ጅምር ሲሆን ፣ አዲሱ የኢ.ፌ.ጠ.ማ (EFAA) አመራር የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ (EALS) ጋር ያለውን አጋርነት ለማጠናከር እንዲሁም ከቀጠናዊ እና ዓለም አቀፍ የጠበቆች ማህበራት ጋር ያለውን ትብብር ለማስፋት ቁርጠኛ ነው ።
EFAA Invitation for Expression of Interest – Baseline Financial & Compliance Audit
The Ethiopian Federal Advocates Association (EFAA) invites qualified and licensed audit firms to submit their Expression of Interest to conduct a Baseline Financial and Compliance Audit of the Association.
📅 Submission Deadline: February 8, 2026 (5:30 PM)
📧 Submission Email: info@efaa.et
🔗 Full details available in the attached Invitation Document.
EFAA encourages eligible firms to apply.
Photo from Tesfaye Deresse Law Office
የአስተዳደር_ተቆጣጣሪ_እና_አገልግሎት_ሰጪ_ተቋማትን_የሚመለከቱ_ጥያቄዎች.docx0.28 KB
የፍትህ_አካላትን_የሚመለከቱ_ጥያቄዎች.docx0.27 KB
ለተቋማዊ ውይይት አጀንዳ ቀረጻ ለአባላት የቀረበ መጠይቅ
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር (EFAA) ከፍትህ አካላት ፣ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም ከሌሎች ጠበቆች በስራቸው አጋጣሚ ከሚጎበኟቸው አካላት ጋር በመርህ ላይ የተመሰረተ ተቋማዊ ውይይት ለማካሄድ በሂደት ላይ ነው። ለዚህ ዝግጅት ይረዳም ዘንድ ይህ መጠይቅ ተዘጋጅቷል። የዚህ መጠይቅ ዋና ዓላማ የአባላትን ሙያዊ አስተያየት ለማሰባሰብ ፣ በልምድ ላይ የተመሠረቱ ግንዛቤዎችን ለመጋራት እና ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በተመለከተ ምክረ ሃሳብ ለማግኘት ነው ። እነዚህም ማህበሩ ተቋማዊ ግንኙነቱን የሚቃኝበት ማዕቀፎች ይሆናሉ።
ይህ መጠይቅ የተዘጋጀው ማህበሩ በቀጣይ ለሚያደርገው የትብብር ፣ የውይይት እና የተቀናጀ የለውጥ ጥረት አጀንዳዎችን መለየት እንጂ አባላት በገጠሟቸው ጉዳይ-በጉዳይ ላይ የተመሰረቱ ቅሬታዎችን ለማሰባሰብ አይደለም። በመሆኑም አባላት ተቋማዊ እና አጠቃላይ አሰራርን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ያተኩሩ ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን ።
ማህበሩ ያለአባላቱ ንቁ ተሳትፎ አንዲት ጋት ወደፊት ሊራመድ እንደማይችል የታወቀ ነው ። ተሳትፎአችን ከሚረጋገጥባቸው ሁኔታዎች ውስጥ ደግሞ እንዲህ ላሉ መጠይቆች የምንሰጠው ወቅታዊ ምላሽ ነው ። በመሆኑም ይህን መጠይቅ ከዚህ በታች ያለውን “ፋይል” በማውረድ ወደ “PDF” በመቀየር በማህበሩ ኦፊሴላዊ የኢሜይል አድራሻ info@efaa.et ወይም https://forms.office.com/r/Ds4PpHH8My እና https://forms.office.com/r/hEP39gdErX ሁለቱን ሊንኮቹን በመጫን ቅጾቹን በቀጥታ በመሙላት እስከ ጥር 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲልኩልን በአክብሮት እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ማህበር
የፕሬዚደንት ጽ/ቤት
ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም.
የፌዴራል ጠበቆች ስፓርት ቡድን ጨዋታ ድጋፍ
የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች የጤናና ስፖርት ማህበር ከኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ጋር ከአንድ ዓመት በላይ በመተባበር እየሰራ ቆይቷል ። የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና ስፖርት የጠበቆችን የአካልና የአእምሮ ጤና ለመጠበቅ ፣ የሙያ ጫናን ለመቀነስ እና በጠበቆች መካከል አንድነትን ለማጠናከር አስፈላጊ መሆኑ ይታወቃል።
የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች የጤናና ስፖርት ማህበር በአዲስ አበባ ከተማ በሚካሄድ የስፖርት ውድድር እየተሳተፈ ሲሆን ፣ የመጀመሪያ የነጥብ ጨዋታውን ነገ ቅዳሜ ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡30 ላይ ከኤርፖርት ጉሙሩክ ጋር ያደርጋል።
በመሆኑም ፣ ሁሉም አባላት በ6 ኪሎ FBE ካምፓስ ሜዳ በመገኘት ድጋፋችሁን እንድታሳዩ በክብር ይጋብዛል።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር
ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም.
የኮሚቴ አባላት ምዝገባ
የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር በመተዳደሪያ ደንቡ መሰረት እንዲቋቋሙ በተወሰኑት 9 ኮሚቴዎች ላይ ለመሳተፍ ፍቃደኛ የሆኑ አባላት እንዲመዘገቡ ጥሪ ማድረጋችን ይታወቃል። ማህበሩ በድጋሚ ጥሪ ለማደረግ የተገደደው ከዚህ በፊት በተደረገው ጥሪ መሰረት የተመዘገቡት አባላት ቁጥር አነስተኛ እና በጥቂት የኮሚቴ ኃላፊነቶች ላይ ብቻ በመሆኑ ነው ።
በመሆኑም እስካሁን ያልተመዘገባችሁ አባላት የምዝገባው ግዜ ከመጠናቀቁ በፊት በፍላጎት ፣ በሙያዊ ችሎታ እና በጊዜ አቅም መሠረት እንድትመዘገቡ አሁንም ጥሪ እናቀርባለን ።
ንቁ ተሳትፎአችሁ አይለየን።
የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር
የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት
ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም
የቋሚ_ኮሚቴ_አባልነት_መመዝገቢያ_ቅጽ.docx0.18 KB
የተሳትፎ ጥሪ
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም ባጸደቀው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ፣ የቆይታ ጊዜያቸው ሶስት (3) ዓመት የሆኑ ዘጠኝ (9) ቋሚ ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙ መወሰኑ ይታወቃል፡፡
እነዚህ ቋሚ ኮሚቴዎች ማህበሩ በህግ የተሰጠውን ተልእኮ በተግባር ለማሳካት ወሳኝ ሚና ያላቸው በመሆናቸው ፣ በኮሚቴዎቹ ውስጥ በተግባር በንቁ ተሳትፎ ለማገልገል ፍቃደኛ የሆናችሁ አባላት ከዚህ ጋር በተያያዘው የመመዝገቢያ ቅጽ እንድትመዘገቡ እንጠይቃለን፡፡
የቋሚ ኮሚቴ አባልነት የጊዜ መስጠት ፣ እንዲያከናውኑ የተሰጡን ስራዎች በተሰጠው የግዜ ማዕቀፍ ማከናወንን የሚጠይቁ ፣ እንደአባል ለሙያችን የምናሳየውን መሰጠት በተግባር የምናረጋግጥባቸው ናቸው ።
የቋሚ ኮሚቴዎች ዝርዝር
1. የሕግ ትምህርት፣ ምርምርና ስልጠና ጉዳዮች ኮሚቴ
2. የደንበኞች አደራ ሒሳብ ጉዳዮች ኮሚቴ
3. የደንበኞችና የመደበኛ አባላት ግንኙነት ጉዳይ ኮሚቴ
4. የሕግ የበላይነት እና የሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ኮሚቴ
5. የፍትሕ አካላት ግንኙነት ጉዳይ ኮሚቴ
6. ነጻ የህግ አገልግሎት ጉዳይ ኮሚቴ
7. የሥርአተ ጾታ እና አካታችነት ጉዳይ ኮሚቴ
8. የእውቅና እና የምስጋና ጉዳይ ኮሚቴ
9. የማህበራዊ ግንኙነቶች ጉዳይ ኮሚቴ
በመሆኑም አባላት በፍላጎት ፣ በሙያዊ ችሎታ እና በጊዜ አቅም መሠረት ተገቢ የሚመስላቸውን ኮሚቴ በመምረጥ ፣ ይህ ማስታወቂያ ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ በሰባት (7) ቀናት ውስጥ ከዚህ በታች የተያያዘውን የመመዝገቢያ ቅጽ በማውረድ ምላሻችሁን በWord ወይም PDF (Scan የተደረገ) በማህበሩ ኦፊሴላዊ የኢሜይል አድራሻ info@efaa.et ወይም https://forms.office.com/r/jiQDPuuJDq ሊንክ በመጫን የመመዝገቢያ ቅጹን በቀጥታ በመሙላት እንዲመዘገቡ አክብሮት እንጠይቃለን።
ለጊዜያችሁና ለንቁ ተሳትፎአችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው።
የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር
የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት
ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም
የፌዴራል_ጠበቆች_ማህበር_የሙያ_ስራ_የተቀናሸ_ወጪዎች_ጥናት_ቡድን_የተዘጋጀ_መጠይቅ_.docx2.33 KB
የተሳትፎ ጥሪ ለአባላት
የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ከዚህ ቀደም ለእናንተ ባቀረበው ዝማኔ ኩነት ላይ እንደገለጸው እንደጠበቆች እና ህግ አማካሪዎች የሙያ አገልግሎት በመስጠት ስራ ላይ ለተሰማሩ ግብር ከፋዮች የሚሆን የተቀናሽ ወጪዎች አያያዝ መመሪያ ለማዘጋጀት የሚያገለግል የጥናት ሰነድ ለማቅረብ ኀላፊነት መውሰዱ ይታወቃል ።
ለዚህ ኃላፊነት የተመደቡ ባልደረቦቻችንም ከዚህ በፊት በማህበራችን እና በአባላቱ የተከናወኑ ጥናቶችን ፣ ተዛማጅ ሕጎችን እና ዓለምአቀፍ ተሞክሮዎችን በማሰባሰብና በመመርመር ስራቸውን በማከናወን ላይ ይገኛሉ። በዚህም ሂደት የጥናቱን ጥራት ለማሻሻል ከአባላት ተጨማሪ መረጃና አስተያየት መሰብሰብ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተውታል ። ለዚህም እንዲረዳ የጥናት መጠይቅ አዘጋጅተው ለማህበሩ አቅርበዋል ።
ለጥናቱ ውጤታማነት የማህበሩ የአባላት ተሳትፎ ተገቢ መሆኑን በማመን መጠይቁ እንዲደርሳችሁ ለማድረግ ወስኗል።
በመሆኑም ለመጠይቆቹ ያላችሁን ምላሽ እስከ ጥር 10/2018 ዓ.ም ድረስ ከዚህ በታች በተጠቀሱት አማራጮች እንድትልኩ በአክብሮት እንጠይቃለን፦
፩. ከዚህ በታች የተያያዘውን ፋይል በማውረድ ምላሻችሁን በWord ወይም PDF (Scan የተደረገ) በማህበሩ ኦፊሴላዊ የኢሜይል አድራሻ info@efaa.et ወይም በኢትዮጵያ የፌደራል ጠበቆች ማህበር የቴሌግራም ቻነል - EFAA Members Forum (https://t.me/+M5yXp_1p6JsyMjk8) ላይ በመግባት አጣብቆ በመላክ ፣
፪. የቀረበውን የሕግ ባለሙያዎች ተቀናሽ ወጪዎች ዳሰሳ መጠይቅ – ኢትዮጵያ (2) – Fill out form https://forms.office.com/r/8J2uaHekmh ሊንክ በመጫን ወይም QR Code በመስካን የ «የሕግ ባለሙያዎች ተቀናሽ ወጪዎች ዳሰሳ መጠይቅ – ኢትዮጵያ» ቅጹን በቀጥታ በመሙላት ፣
ለጊዜያችሁና ለንቁ ተሳትፎአችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው።
የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር
የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት
ጥር 3 ቀን 2018 ዓ.ም
