5killo Jem'a official Channel
رفتن به کانال در Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
نمایش بیشتر1 160
مشترکین
-124 ساعت
+27 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
Repost from AAU - Muslim Students Union
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያወጣውን ጨቋኝ መመሪያ ስንቃወም የነበረው ከመፅደቁ በፊት በረቂቅነት ደረጃ ካለበት ጀምሮ ነበር። መመሪያው የፀደቀው ጥቅምት 2017 ዓ.ል ቢሆንም መስከረም ወር ውስጥ ተማሪዎች ግቢ እንደገቡ የተማሪዎችን ሐሳብ ሳይቀበሉ ኦረንቴሽን በሚል ከቨር ለተማሪዎች በትዕዛዝ መልክ አስተላለፉ። ሆኖም ተማሪዎች ከዚያው ከመድረክ "ጥያቄ አለን!" በማለት አስተጋቡ። አመራሮቹ ግን መልስ ከመስጠት ይልቅ የተማሪዎቹን የጥያቄ አለን ማብራሪያ ስጡን ጩኸት በመሸሽ ወደ ቢሯቸው አመሩ። ተማሪዎቹም እንደተሰባሰቡ ከቢሯቸው ሄዱ። በሰዓቱ ለአሁን በረቂቅነት ደረጃ ያለ መመሪያ ስለሆነ መፍትሔ ይመጣል በውይይት እናድርገው ብለው ቃል የገቡ ቢሆንም ቃላቸውን አጥፈው መመሪያውን በማፅደቅ ጆሮ ዳባ ልበስ እንዳሉ እስስካሁን አሉ።
ተማሪውም ሳይሰለች ሳያፍር ሳይፈራ እስካሁን አለ። አመት ከመንፈቅ ቢሞላም "ጥያቄ አለን!" የሚለው መፈክር ሳይደበዝዝ እስካሁን አለ። ተማሪዎች በሚዲያ፣ ቢሮ ውስጥ፣ በአደባባይ ጥያቄ አለን እያሉ እስካሁን አሉ። ፍትሐዊ መልስ መጥቶ ገፊ መግፋቱን እስኪያቆም፤ በዳይም በደሉን እስኪገታ ድረስ ጥያቄው ይቀጥላል።
አይደለም ወይ?
እኛ የምንሰለች ትውልድ አይደለንም። የጀመርነውን ጥያቄ ከግብ ሳናደርስ የምናቆምበት ምክንያትም ሆነ ሁኔታ አይኖርም።
ቪድዮ፦ ረቡዕ መስከረም 15 / 2017 ጨቋኙ መመሪያ በረቂቅነት ሳለ ለ5ኪሎ ተማሪዎች ትዕዛዝ ሲተላለፍ እና ተማሪዎችም ጥያቄ አለን ሲሉ የተቀረፀ
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
11ዱ የአፄ ኀይለ ስላሴ ሙስሊሙን ከትምህርት ማግለያ ፖሊሲዎች
ድምፃችንን ለማሰማትና ትግላችንን ለማጠናከር የቲክቶክ ገፃችንን Follow, Share እና Copy link በማድረግ ተደራሽነቱን ያስፉ። ሌሎችንም ወደ ገፁ ይጋብዙ።
Follow ያደረጋችሁበትን እና Follow ያስደረጋችሁበትን Screenshot በዚህ @Niqab_issueBot ይላኩልን።
https://www.tiktok.com/@aaumsu/video/7618885590536228116?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7504249112218240518
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ጥያቄ አለን፦ በሁሉም ኢትዮጵያዊ ሀብት የተገነባው አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት የሚጥስ መመሪያ ለምን እንዳወጣ ጥያቄ አለን! መማር ማስተማሩ በሰላም እየሄደ ባለበት ድንገት ተነስቶ ሒጃብ ለባሽ ሙስሊም ተማሪዎችን በር ላይ፤ ካፌ ውስጥ ብሎም በመማሪያ ክላስ ለምን ሊያንገላታ እንደፈለገ ጥያቄ አለን!!
ጥያቄ አለን፦ በሕዝብ ሐብት የተቋቋሙ የሕዝብ ሚዲያዎች (EBC: Addis media network ወዘተ...) ፤ ለሕዝበ ሙስሊም ድምፅ ይሆኑ ዘንድ የተቋቋሙ ሚዲያዎች ፤ ስለ ሰብዓዊ መብት ይገደናል የሚሉ አለምአቀፍ ሚዲያዎች (DW, BBC, Anadolu, TRT, Al-jezira etc...) ብሎም በሀገር ውስጥ ያሉ ተፅዕኖ ፈጣሪ የማህበራዊ ሚዲያ አውታሮች (ቲክቫህ፣ ATC etc..) እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው ሁሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ከአመት በላይ ሕገ-ወጥ መመሪያን ተገን ያደረገ የመብት ጥሰት ሲካሄድ ተገቢውን የሚዲያ ሽፋን ለምን እንዳልሰጡ ጥያቄ አለን!!!
ጥያቄ አለን፦ ስለ ሴቶች ተብሎ በሚኒስቴር መስሪያ ቤት ደረጃ የተቋቋመው የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የሙስሊም ሴቶች መብት ሲጣስ ለምን ዝም እንዳለ ጥያቄ አለን። ስለ ሰብዓዊ መብት ተብሎ የተቋቋመው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሰብዓዊ መብት ሲጣስ አስቸኳይ እርምጃ ስለምን እንዳልወሰደ ጥያቄ አለን።
መልስም እንፈልጋለን። መልስ ፍትሐዊ መልስ እስኪሰጡም በሁሉም መንገድ እንጠይቃለን። መብታችን ስለሆነ። ተቋማቱ የእኛም ጭምር ስለሆኑ። መጠየቅ ግዴታችን ስለሆነ። መመለስም ግዴታቸው ስለሆነ።
ለመጠየቅ ዝግጁ ናችሁ? ለመጠየቅ ዝግጁ ነህ? ለመጠየቅ ዝግጁ ነሽ?
@aaumsu
#Ramadan30
💥 ዒድ - ህግጋትና ስርአቱ 💥
➡️ ተክቢራ
📌 የሚባልበት ጊዜ፡-
* በዒደል ፊጥር - የረመዷን ወር መጨረሻ ቀን ፀሐይ ከጠለቀችበት ወይም የሸዋል ጨረቃ ከታየችበት ጊዜ ጀምሮ ነው። ምክንያቱም አላህ ተክቢራውን ከረመዷን ፍፃሜ ጋር አያይዞ ነውና የገለፀው። [አልበቀረህ፡ 185] ተክቢራው እስከ ዒድ ሶላት ድረስ ይዘልቃል።
📌 ድምፅን በተክቢራ ከፍ ማድረግ የተወደደ ነው። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 4934]
👉🏻ተክቢራው ሴቶችንም በተመሳሳይ የሚመለከት ነው። [አልቡኻሪይና ሙስሊም] ድምፃቸውን ግን ዝቅ ሊያደርጉ እንደሚገባ ዑለማዎች ይመክራሉ።
👉እነዚህን ተክቢራዎች ማለት በጀማዐ ለሰገደም፣ ብቻውን ለሰገደም የተወደደ ነው። ግዴታ ግን አይደለም። [ሸርሑል ሙምቲዕ፡ 5/165]
➡️ የዒድ ሶላት፡-
👉🏻 ሶላቱን በተመለከተ ሚዛን የሚደፋው አቋም “ግዴታ ነው” የሚለው እንደሆነ ኢብኑ ተይሚያ፣ ሶንዓኒይ፣ ሲዲቅ ሐሰን ኻን፣ ሸውካኒይ፣ አልባኒይ፣ ኢብኑ ዑሠይሚን እና ሌሎችም አስረግጠው ተናግረዋል።
👉🏻ወቅቱ፡- ፀሀይ ወጥታ ቢበዛ ሩብ ሰዓት አካባቢ ከፍ ካለች ጀምሮ እስከ እኩለ ቀን ድረስ ያለው ነው። የዒደል ፊጥር ሶላት ዘግየት ቢል ተመራጭ ነው። [አተልኺስ፡ 144] [ሙስነዱ ሻፊዒይ፡ 74] ምክንያቱም የዒደል ፊጥር ጊዜ ዘግየት ማለቱ ዘካተል ፊጥር ለሚሰጡ ሰዎች ጊዜ እንዲኖራቸው ያደርጋቸዋል።
👉🏻ለዒድ ሶላት አዛንም ኢቃማም አይደረግም። [አልቡኻሪይ፡ 962] [ሙስሊም፡ 886]
👉🏻የረከዐው ብዛት፡- 2 ነው። [አልቡኻሪይ፡ 964] [ሙስሊም፡ 884]
👉 የዒድ ሶላት ውስጥ ያሉት ተጨማሪ ተክቢራዎቹ ሙስተሐብ እንጂ ግዴታ አይደሉምና በመርሳትም ሆነ ሆን ተብሎ ቢቀሩ ሶላቱ አይበላሽም። [አልሙግኒ፡ 3/275]
👉🏻ቁጥራቸውም የመጀመሪያው ረከዐ ላይ ከመክፈቻው ተክቢራ ውጭ 7፤ ሁለተኛው ረከዐ ላይ ደግሞ ከመነሻው ተክቢራ ውጭ 5 ተክቢራ ነው። ይሄ ከብዙሃኑ ሶሐቦችና አኢማዎች የተገኘው እንደሆነ ኢብኑ ተይሚያ ገልፀዋል።
Ramadan Daily Virtue _ የረመዳን ወርን በኢስቲጝፋር (ምህረትን በመለመን) እንሰናበት
👉 የረመዿን የመጨረሻ ቀን ላይ እንደመሆናችን መጠን፣ ይህንን ታላቅ ወር እንዴት ማጠናቀቅ እንዳለብን ሸይኽ ዐብዱስሰላም አል-ሹወይዒሪ እንዲህ በማለት ይመክሩናል፦
👉 ራስን ከኩራት መጠበቅ፦ በራሱ ዒባዳህ የሚኩራራ ሰው ጥፋት ላይ ነው።
👉 የሥራችንን ጉድለት ማመን ይገባናል፦ ስራችን ምንም ያህል ቢበዛ፣ በውስጡ ጉድለት ሊኖር እንደሚችል አውቀን አላህን ምህረት መጠየቅ ይገባል።
👉 ነቢዩ ሰ. ወ ግዴታ ሶላቶችን እንኳን ሰግደው ሲጨርሱ "አስተግፊሩላህ" (አላህ ሆይ ማረኝ) በማለት ሶስት ጊዜ ይሉ ነበር። ይህም ስራን በምህረት ፍለጋ ማጠናቀቅ ያለውን ትልቅ ቦታ ያሳያል።
👉 እንደ ዑመር ኢብኑ ዐብዱልዓዚዝ ያሉ ታላላቅ መሪዎች የረመዳን ወር ሲጠናቀቅ «ረመዿንን በእስቲጝፋር አጠናቁ!» በማለት መልዕክት ያስተላልፉ ነበር።
✨✨ أستغفر الله وأتوب إليه ✨✨
#FiqhusiyyamiRamadan
#DailyVirtue
💥አምናቹ እንደሰጣችሁን እኛም ለሚገባው አማናችሁን አድርሰናል!!!!💥
በ5 ኪሎ ጀምዓ አካባቢያችን ላይ ላሉ የቲሞች ፣ መሳኪን ፣ ችግርተኛ ቤተሰቦች ዒድን በደስታ እንዲያሳልፉ የአስቤዛ ድጋፍ እናድርግ በሚል 62,845 ብርር ተሰብስቦ ነበር ፤ አልሃምዱሊላህ አስቤዛውም ተገዝቶ ቦታው ደርሷል። በዋነኝነት 5 ኪሎ አካባቢ ላሉ መሳኪኖች የተሰጠ ሲሆነ የተወሰኑት ደግሞ ፈረንሳይ ፣ ጃልሜዳ ፣ ሜክሲኮ ፣ ደምበል ፣ ዳለቲ...ለሚገኙ መሰጠት ለሚገባቸው ሙስተሂቅ ቤተሰቦች አስቤዛውን አስረክበናል።
👉አልሃምዱሊላህ አስቤዛው ለ20 (የቲም፣ መሳኪን ፣ ችግርተኛ) ቤተሰቦች ሊዳረስ ተችሏል ።
👉ለእያንዳንዱ ቤተሰብ በነፍስ ወከፍ :-
📌5 ኪሎ ዱቄት
📌5 ሊትር ዘይት
📌5 ፓስታ
📌2.5 ኪሎ ሩዝ ........ተሰጥቶታል።
✨አጠቃላይ የተገዙ አስቤዛዎች ዝርዝር ወጪዎች
🌟 1ኪሎ ሩዝ ዋጋ = 115 ብር
👉🏻ጠቅላላ 50 kg ሩዝ ተገዝቷል = 5750 ብርር
🌟 1ኪሎ ዱቄት ዋጋ = 108 ብር
👉🏻ጠቅላላ 100 kg ዱቄት ተገዝቷል=10,800 ብርር
🌟 5L ዘይት = 1965 ብር
👉🏻ጠቅላላ 20 pieces ዘይት ተገዝቷል=39,300 ብር
🌟1 ካርቶን ፓስታ (20 piece)=1950ብር
👉🏻ጠቅላላ 5 ካርቶን ፓስታ ተገዝቷል= 9750 ብር
👉 ለትራንስፖርት =2500 ብር
👉ለማሸጊያ እና መጫኛ = 760 ብር
⚡️ በአጠቃላይ የወጡ ወጪዎች ድምር:-
(5750+10,800+39,300+9750+2500+760 ====68,860ብር)
👉ከተሰበሰበው 62,845 ብር ላይ የተቀረው 6015 ብር በጀምዓው የተሸፈነ ሲሆን ጠቅላላ ወጪ 68,860ብር ተግባር ላይ ውሏል!
🌙 እቃውን የተረከቡን ወንድም/ እህቶች ደስታቸው እጅጉን የሚያስደስት ነበር። ለጀመዓው እንዲሁም ለአጠቃላይ ሰዳቂው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
➡️ በዚህ ኸይር ስራ ላይ የተሳተፋችሁ ከማስተባበር ጀምሮ ፣ ሰደቃ በመስጠት ፣ በማከፋፍል....ስትሳተፉ የነበራችሁ አላህ በገንዘባችሁ ፣ በጊዜያችሁ ላይ በረካን ይጨምርላችሁ ፣ አላህ ኸይር ስራችሁን ይቀበላችሁ !!!
Repost from AAU - Muslim Students Union
ሰበር ዜና!
ዛሬ የሸዋል ጨረቃ በሳዑዲ አረቢያ ባለመታየቷ ነገ ኃሙስ የረመዳን ሰላሳኛ ቀን ሆኖ ከነገ ወዲያ ጁሙዓ ዕለት ኢድ የሚሆን ይሆናል።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
🔥ከ ሙተነቂቦች መንደር ~ 3🔥
ለግቢው አዲስ የመሆኑ ስሜት ሳይላቀቀኝ ከልደታ 5ኪሎ ከከተምኩ 1ኛ አመትን ተሻግሮ ሁለተኛው ላይ ገብቷል። ፋይናል ሳንፈተን ወደ ቤታችን መልሰውን ነበር እና ወደ ግቢ ስንመጣ ትኩረታችን ጊዜው ወዳለፈበት ፋይናል መዘጋጀት ነበር::
ግቢው ከኛ ሁለተኛ አመቶች ውጪ ማንም ስላልነበረ ግቢውን በደንብ እየቃኘሁ የተቀረኙን አመታት እዚህ እንዴት እንደማሳልፍ እያሰብኩኝ ነው።
ታዲያ በዚህ መሀል ነበር ዝግጅታችንም ሳይጠናቀቅ ፈተናውም ሳይጀመር የ ሶስተኛ አመት እና ከዛ በላይ ያሉ ተማሪዎችን መግባት ተከትሎ " በዚህ ህገ-ደንቤ ነው ከዚህ በኋላ የምትመሩት" ብሎ ዩኒቨርሲቲው ለኛ አዲሱን መመሪያ ማስተዋወቅ የጀመረው ።
ግቢው ነገሩንም ከወረቀት ወደ ተግባር ለመቀየር ጥቂት ጊዜያትን ብቻ ነበር የፈጀበት። መጀመሪያ ላይብረሪ አካባቢ ያሉ ፊቶች ጠቆር ኮምሸሽ ማለት ጀመሩ ከዛ ደግሞ ካፌ በር ላይ ተቀምጠው ወጣ ገባውን የሚቃኙ ጥበቆች ማስጠንቀቂያ የቀላቀሉ ቃላቶችን ጣል ማድረግ ቀጠሉ ፤ በዛውም ልክ የኔ ልብ ድንግጥ እግሮቼም ብርክርክ ማለታቸውን ተያይዘዋል ። በር ላይ ካለው ጥበቃ ጀምሮ እላይ እስካለው ድረስ የመማር መብቴን ነጥቆ በሰከንዶች ውስጥ ከግቢው ሊያባርረኝ እንደሚችል ነበር የሚሰማኝ! ኒቃቤንም ከለበስኩኝ ገና አመትን አልደፈንኩኝምና " ያ አላህ! ለምን እኔን? ለምን አሁን? " ተደጋጋሚ ቃላቶቼ ነበሩ ። ከዛ ደግሞ መለስ እልና " የሚወደውን ነው የሚፈትነው ፣ ለሂጃቤ ያለኝን ታማኝነት ሊያይ " እላለው ። በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆኜ አዕምሮዬ ሀሳቦችን መሰብሰብ እያቃተው ፈተናችሁ ሰኞ ይጀመራል ተብለን ወደ ፈተናችን መግባት ጀመርን።
ታሪካዊው ቀን ፤ረቡዕ መስከረም 15/2017 አሁን ድረስ የምንደጋግመው መፈክራችን "ጥያቄ አለን! "ን ያስጀመረው ክስተት ተከሰተ።
የካምፓሱ አስተዳደሮች የ 5ኪሎ ተማሪን በሙሉ በአንድ አዳራሽ ሰብስበው መመሪያቸውን ያብራሩ ይዘዋል ። ከ ሀ እስከ ፐ ድረስ ይሄ የናንተ መብት ፣ ይሄ ደግሞ ግዴታችሁ ነው እያሉ ይገኛሉ። በመሀል የአዋጁ አንቀፅ 6.6 ላይ ሲደርሱ ነገሩን ጠበቅ ጊዜያቸውንም ወሰድ አድርገው በምንም ዓይነት መልኩ ፊትን መሸፈን እንደማይቻል ተናገሩ እንደውም "ጥቁር በጥቁር የምትለብሱ" ብለዉ ኒቃቢስት ያልሆኑ እህቶችንም አለባበሳቸውን እንደማይፈቅዱ ተናገሩ። የዛኔ ነበር ስለመብታችን ዘብ ለመቆም የተነሱ ወንድሞች "ጥያቄ አለን! " እያሉ አዳራሹ ውስጥ ማስተጋባት የጀመሩት (አላህ መልካም ስራቸውን ይቀበል)። ይሄ ሁሉ ሲፈጠር እኔ ከ አዳራሹ በርቀት ሆኜ ነገሩን እያየሁኝ ነበር፤ እንዲህ መባረርን ሳይፈሩ ለኛ መብት ሲጮሁ የነበሩትን ሳይ ልቤ ውስጥ አንዳች ነገር ተሰማኝ! "ኒቃቤ የሚወልቀው ለህድ ስገባ ነው " ብዬ ለራሴም ቃል ገባሁ። እስከመጨረሻውም ድረስ ለዲኔ ስል እንደምታገስ ለራሴ ተናገርኩኝ!
ይህ የኔ ታሪክ ነው! ሁሉም ሙተነቂቦች በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ ተመሳሳይ ነገርን አሳልፈዋል። አላህ ለኛ ሂጃብ ዘብ ለሚቆሙት ወንድሞች እና እህቶች ምንዳቸውን ይክፈል! እኛንም ፅናቱን ይስጠን!
ወልሀምዱሊላሂ ረቢል ዓለሚን !!
@aaumsu
ተቀበለላሁ ሚንኩም!
አላህ ከሁላችንም ይቀበል!!
⚡️ አንድ ወንድም/እህት ከሐኪሞቹ መንደር 95 ብር አስገብተዋል አላህ ይቀበላቸው ፤ ያሰቡትን አሳክቶ ዱኒያ አኺራቸውን ያሳምር ፣ በጀነተል ነዒም ለዘላለም የሚቀማጠሉ ያድርጋቸው !
💥
እኛም በዚሁ እናጠናቅ!!
📌 በ5 ኪሎ ጀመዓህ ሲከናወን የነበረው ሰደቃ የመሰብሰብ ስራ ተጠናቋል።
አካባቢያችን ላይ ላሉ ደካማ ቤተሰቦች ዒድን ያለ ችግር እንዲያሳልፉ የአስቤዛ እና የኪስ ገንዘብ ድጋፍ እናድርግ በሚል የጀመርነው ገቢ ማሰባሰቢያ አጠናቀናል አልሃምዱሊላህ!!!!!
🌟የሰደቃችሁ ወንድሞች/እህቶች አላህ ይቀበላችሁ፤ አላህ ኸይር ጀዛኡን ይመንዳችሁ፤አላህ ኸይር ስራችሁን ይቀበል ! የመልካም ስራችሁን ዋጋ በዱኒያም በአኺራም አጊኙት! ያሰባችሁትንም ያሳካላችሁ!ነገራችሁን ሁሉ ያስተካክልላችሁ፤ረመዷናችሁን ይቀበላችሁ፤ዱንያ አኺራችሁን ያሳምርላችሁ።
አጠቃላይ 62,845ብር መድረስ ችለናል። ፈሊላሂልሃምድ! በቅርቡም አማናችሁን የምናደርስ ይሆናል።
@fivekjemaa
#Ramadan29
ዒድ - ህግጋትና ስርአቱ
👉ዒደል ፊጥር ረመዳን እንዳለቀ በሸዋል ወር የመጀመሪያ ቀን ላይ ይውላል።
1. እለቱ የደስታ ቀን ነው፡-
👉🏻 “ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም” እያሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት መለዋወጥ ከሶሐቦች ተገኝቷል። [አልፈታዋ፡ 24/253]
👉🏻 የምንደሰትበት ግን ፈፅሞ በሐራም ነገር መሆን የለበትም። “የትም ብትሆን አላህን ፍራ!” የሚለው ሐዲሥ አይረሳ።
2. ወደ መስገጃው ቦታ መውጣት፡-
👉🏻 ወደ መስገጃ ቦታ ሲወጣ መታጠብን፣ ሽቶ መቀባትን የሚመለከት ከሶሐቢዩ ኢብኑ ዑመር ተገኝቷል። [አልኢርዋእ፡ 104]
👉🏻 በእለቱ አቅም በፈቀደ ባማረ ልብስ ሽክ ማለት ተወዳጅ ነው። [አልቡኻሪይናሙስሊም]
👉🏻 ለቻለ ሰው ወደ መስገጃው ቦታ በእግር መሄዱ ሱና ነው። [አልኢርዋእ፡ 636]
👉🏻 የወር አበባ ላይ ያሉ ሴቶች ወደ መስገጃው ሜዳ መውጣታቸው ከሱና ነው። ከመስገጃው ቦታ ግን ገለል ይላሉ። [አልቡኻሪይ] ሴቶች ወደ መስገጃው ቦታ ሲወጡ ሽቶ ከመቀባትና ካላስፈላጊ አለባበስ መራቅ አለባቸው።
👉🏻ከመስገጃው ቦታ ሲመለሱ መንገድ ቀይሮ መመለሱ ሱና ነው። [አልቡኻሪይ:986]
🌙 Ramadan Day 29 – Stay Consistent
Tonight may be the last night of Ramadan…
Tomorrow could be Eid.
No more Taraweeh.
No more long nights like this.
But don’t let your عبادات end with Ramadan…🤲 Keep Going
عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " أَحَبُّ الأَعْمَالِ إِلَى اللَّهِ تَعَالَى أَدْوَمُهَا وَإِنْ قَلَّ " . قَالَ وَكَانَتْ عَائِشَةُ إِذَا عَمِلَتِ الْعَمَلَ لَزِمَتْهُ . 'A'isha reported Allah's Messenger (ﷺ) as saying: The acts most pleasing to Allah are those which are done continuously, even if they are small. and when 'A'isha did any act she did it continuously. Sahih Muslim, 783👉Be a person of consistency… not just a person of Ramadan. #FiqhusiyyamiRamadan #DailyVirtue
+1
አላሁ አክበርርር🔥 !! አላሁ አክበርርር🔥 !! አላሁ አክበርርር🔥 !!
100 ብር + 100 ብር ለጀመዓችን ገቢ ሆኗል !!
የየቲሞች ደስታ ሰበብ እንደሆናችሁት አሏህ በሀያታችሁ ሁሉ ያስደስታችሁ! በፀጋው የምትብቃቁ ያድርጋችሁ! በረመዷን ከእሳት ነፃ ከተባሉት አሏህ ያድርጋችሁ!
🤲🤲አሚን ያረበል አለሚን!🤲🤲
ረሱል (ሰ.0.ወ) ትንሽም ብትሆን ኒያዋ የተስተካከለ ሰደቃን ሲገልፁ እንዲህ ብለዋል፦
“አንዲት ዲርሃም (ብር) መቶ ሺህ ዲርሃምን ቀደመች (በለጠች)። ሶሐቦችም ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ? በማለት ጠየቁ። እሳቸውም እንዲህ በማለት ልዩነቱን አብራሩ፦ አንድ ሰው ሁለት ዲርሀም (ብር) ብቻ ነበሩት፤ አንዷን ለሰደቃ (ለምፅዋት) ሰጠ። ሌላው ሰው ደግሞ ወደ ከከፊል ገንዘቡ (ሀብቱ) በመሄድ ከብዙ ሀብቱ ላይ መቶ ሺህ ዲርሀም (ብር) አንስቶ ለሰደቃ ለገሰ።”
🌴 የመጨረሻው የረመዷን ቀን ሊሆን ይችላል፣ በሁሉም ዒባዳዎች በኢኽላስ መበራታት አለብን!በኸይር ስራ ላይ እንጣደፍ! የቲሞችን እናስደስት !
አካውንት፡ 1000626274718
(Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.)
ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !
+2
ተክቢርርርር ! አላሁ አክበር !!
ተክቢርርርር ! አላሁ አክበር !!
ተክቢርርርር ! አላሁ አክበር !!
ተቀበለላሁ ሚንኩም!
አላህ ከሁላችሁም ይቀበል!!
⚡️ አንዳንድ ልቦች ደግሞ ይገርማሉ፣ የራሳቸውን ሪከርድ ለመስበር ከራሳቸው ጋር ይሽቀዳደማሉ!
ከዚህ በፊት ሁለት ጊዜ 1000 ብር አስገብቶ የነበረ ወንድማችን ለሶስተኛ ጊዜ ደግሞ 500 ብር አስገብቷል! ከዚያስ? አንዲት እህት ከSoftware 200 ብር አስገብታ የነበረው ላይ 750 ብር ጨምራበታለች! 💥
ሌላ አላህ ያገራለት ወንድም እንደዚሁ 600 ብር!!!
ሱብሀንአሏህ!
እንደነዚህ ልቦች ደጋግሞ መስጠትን አሏህ ያግራልን!
ለነሱም ከለገሱት በላይ አሏህ ከማያልቀው ችሮታው ይለግሳቸው! ከአርሽ ጥላ ስር ያኑራቸው! ግባችን ጀነት አይደል? ጀነትን ይስጣቸው!
🤲🤲አሚንንንንንንን!🤲🤲
ይህንን የትልቅ አጅር መቋደሺያ እድል እስካሁን ያልተጠቀማችሁ ጊዜው አልረፈደም!
የቲሞችን መሳኪኖችን እናስደስት ! አላህ ባለሰብነው መልኩ ያስደስተናል ።
አካውንት፡ 1000626274718
(Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.)
ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !
+2
አላሁ አክበር 🔥ወሊላሂል ሐምድ !!
አላሁ አክበር 🔥ወሊላሂል ሐምድ !!
750 ብር + 600 ብር + 100 ብር ገቢ ሆኗል!
አላህ ይቀበላችሁ ያ ኡመተል ኢስላም!
ጀመዓው ግን ትንሽ ቀዝቀዝ ብሏል ፤ ተኛችሁ እንዴ?
አንድ ወንድም "65ሺ መግባት እንችል ይሆን?" ብሏል 750 ብር ካስገባ በኋላ!
አሏህ ተስፋህን እውን ያድርገው!
"ያ ጀመዐ ዱአ!" ተብለናል ፣ አሚን በሉ እንግዲህ!
የሰደቃችሁ ወንድም እና እህቶች አሏህ ይቀበላችሁ! አሏህ በወደደው ነገር ላይ ያዋላችሁት ሀቃችሁ ከእሳት ነፃ መውጫ፣ ወደ ጀነት መግቢያ ይሁናችሁ!
🤲🤲አሏሁመ አሚን🤲🤲
⚡️ወንድማችን እንዳለው 65,000 ብር እንድፈን እንጂ!
ማን ጀግና ነው 65,000 ሞልቶ የሚያስደስተን ??
አሏህ እንዲህ ይለናል :- እነዚያ ገንዘቦቻቸውን በሌሊትና በቀን በድብቅም በግልጽም የሚለግሱ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው፡፡ በእነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም እነርሱም አያዝኑም፡ ፡
📌 አትከፉም አታዝኑም እያለን ነው አላህ !
🌼 ምንኛ ያማረ ብስራት ነው!
አካውንት፡ 1000626274718
(Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.)
ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !
አላሁ አክበርርር🔥!
አላሁ አክበርርር🔥!
አላሁ አክበርርር🔥!
60,000 ለመሙላት ቀርታን የነበረውን 1350 ብር ግማሿን 600 ብርርርር አንድ ወንድማችን ከ electric Department ሰድቁአል !!
አስደስቱን ስንል እሺ እንዳልከን ፣ የጠየቅከውን ሁሉ አላህ እሺ ይበልህ! በዲንህም በዱኒያህም አላህ ከፍተኛ ቦታ ላይ ያብቃህ ሃጃዎችህን አላህ ገር በገር ያድርግልህ ኡማውን የምታገለግል ጠቃሚ ሰው ያድርግህ !!
ለዚህ ወንድማችን ይሄን ያነበብን ሁሉ ዱዓ እናድርግለት!
✨የለይሉን ግማሽ አልፈንዓል! ይቺን የተባረከች ለሊት ሳታመልጠን እንጠቀምባት ፣ በረመዳን የተደረገ ሸመታ በጣም ትርፋማ ነውና !✨
ማን ጀግና ነው እስኪ ይቺን የሚጨርሳት (1350- 600 =750)
👉 60,000 አስገብቶን የሚያስደስተን ጀግና/ኒት ??
አካውንት፡ 1000626274718
(Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.)
ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !
+1
📌ለጀመዓችን አንድ እህት/ወንድም 400 ብር እንዲሁም አንድ እህት 100 ብር አስገብተዋል !! ጀዛኩሙላሁ ኸይራ!
አላህ ኸይር ስራችሁን ይቀበል ! የመልካም ስራችሁን ዋጋ በዱኒያም በአኺራም አጊኙት! ያሰባችሁትንም ያሳካላችሁ!
🌟የሰደቃችሁ ወንድሞች/እህቶች አላህ ይቀበላችሁ !
ጀመዓው ግን ትንሽ ቀዝቀዝ ብሏል ፤ ተኛችሁ እንዴ? ዛሬኮ 29'ነኛ ሌሊት ናት የመጨረሻዋ ሌሊት በ(خير) ስራ እንሽቀዳደም እንጂ!
وَفِي ذَٰلِكَ فَلۡيَتَنَافَسِ ٱلۡمُتَنَٰفِسُونَ ቁርአን (83:26) በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡👉60,000 ብር እንድፈን እንጂ! ስንት ነው የቀረን መሰላችሁ .. 60,000 - 58 650 ብር = 1350 ብር ብቻ ይቀረናል ! ማን ጀግና ነው እስኪ ይቺን ሞልቶ የሚያስደስተን ?? አሏህ እንዲህ ይለናል :- እነዚያ ገንዘቦቻቸውን በሌሊትና በቀን በድብቅም በግልጽም የሚለግሱ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው፡፡ በእነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም እነርሱም አያዝኑም፡ ፡ 📌 አትከፉም አታዝኑም እያለን ነው አላህ ! 🌼 ምንኛ ያማረ ብስራት ነው! አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !
አላሁ አክበር 🔥! ወሊላሂል ሐምድ🔥 !!
አላሁ አክበር 🔥! ወሊላሂል ሐምድ 🔥!!
ሰደቃው ተጧጡፏል ማሻአሏህ!
ታስታውሳላችሁ ከላይ አንዲት እህት "አደራ አደራ በዱአ አትርሱኝ" ያለችውን? በዚች እህት በኸይር የቀናች ሌላ ነፍስ "እኔንም በዱአ አትርሱኝ" ትለናለች።
200 ብር ከ Civil ዲፓርትመንት!
አሏህ የከጀልሽውን ኸይር ይመንዳሽ ፣ የፈራሽውን ሸር ያርቅልሽ ፣ በመንገድሽ ሁሉ መሪ ይሁንሽ!!!
🤲አሚን በሉ፣ እናንተም ተቀበሉ🤲
የመልካም ስራችሁን ሽልማት በብዙ እጥፍ ተባዝታ አግኟት!
ከጀነት ሰዎች አሏህ ያርጋችሁ!! በዚያም የነብያችን ሰ.ዐ.ወ ጎረቤት ለመሆን ያብቃችሁ!
🤲አሏሁመ አሚን🤲
ውዱ ነቢይ ሙሀመድ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
"እኔና የየቲም (የቲም) ተንከባካቢ በጀነት ውስጥ ልክ እንደነዚህ ነን" አሉ። ይህንንም ሲሉ አመልካችና መካከለኛ ጣቶቻቸውን በማጣመርና በመካከላቸው ትንሽ ክፍተት በመተው አሳዩ። (ቡኻሪ ዘግበውታል)የኸይር ስራ ጥሪያችን ሊጠናቀቅ ይህ ግማሽ ለሊት ብቻ ቀረን ፣ አደራ እንበርታ ፣ በተሰጠን ፀጋ የጌታችንን ውዴታ እናትርፍበት። አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !
+1
ተክቢር !!አላሁ አክበርርር🔥!
ተክቢር !!አላሁ አክበርርር🔥!
ተክቢር !!አላሁ አክበርርር🔥!
አንድ ወንድም/እህት 1000 ብር በማስገባት ሪከርድ ተጋርተዋል!!!
ሌላ የአሏህ ባሪያ እንደዚሁ ከElec and Computer ዲፓርትመንት 300 ብር አስገብቷል/አስገብታለች።
አላህ ይቀበላቸው!
በመስጠት ምትደሰቱ ፣ የሰውን ችግር በማቅለል ከጌታችሁ ምንዳን የምትከጅሉ ተወዳጅ ባሮች አሏህ ያርጋችሁ!!!
አሏህን "በሰጠሁት ሰደቃ ይሁንብህ" ብላችሁ ለምኑት ፣ የለመናችሁትን ካሰባችሁት በላይ አሳምሮ ይስጣችሁ!
🤲🤲አሚንንንንንን🤲🤲
እንዲህ ለኸይር ስራ ስትጠሩ ለምላሽ የምትቸኩሉ የእናንተ አይነቱን ያብዛልን !!
በዱዓ ሁላችንም እናስባቸው !!
✨የተቀረነውስ? ምን እንጠብቃለን? ለሊቱ እየተጋመሰ ነው ሸባብ!✨
አካውንት፡ 1000626274718
(Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.)
ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !
