fa
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

رفتن به کانال در Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

نمایش بیشتر
1 159
مشترکین
-124 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
የወሎ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ከጁምዓ ቡሃላ "ፍትሕ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች!" - በማለት አስተጋብተዋል። ሒጃብ ማንነት ነው። ማንነት ሊከለከል አይገባም! መብቶቻችንን የነጠቁ
+1
የወሎ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ከጁምዓ ቡሃላ "ፍትሕ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች!" - በማለት አስተጋብተዋል። ሒጃብ ማንነት ነው። ማንነት ሊከለከል አይገባም! መብቶቻችንን የነጠቁ አካላት በሕግ ይጠየቁ! ጥያቄው የእኛም ነው! ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው! ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ! ይህ ጅማሮው ነው _ ይቀጥላል 🔥 ©aaumsu @fivekjemaa

photo content

💎የውመል ጁሙአ(ተወዳጁ ቀን)💎 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
💎የውመል ጁሙአ(ተወዳጁ ቀን)💎 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ }    ✨✨   ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ  ✨✨ 🌸የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- " የውመል ጁሙአ ቀኑንም ማታውን እኔ ላይ ሰለዋት ማድረግን አብዙ፡ እኔ ላይ አንድን ሰለዋትን ያወረደ አሏህ በሱ ላይ አስር ሰለዋት ያወርድለታል........ "أكثروا الصلاة علي يوم الجمعة وليلة الجمعة فمن صلى علي صلاة صلى الله عليه عشراً" ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣ ሰለዋት  ጭንቀትን ይቀንሳል፣ ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣ ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ ‣ በመጨረሻው ሰአት (ከአስር በኋላ ) ዱዓ ማድረግ - ለዲናቸው ሲሉ ብዙ ውጣ ወረድ እያዩ ላሉ እህት/ ወንድሞች እንዲሁም በሕይወት ላሉም ላጣናቸውም ወላጆቻችን ዱዓ እናድርግ اللهم اجعلنا بررة أتقياء، وصالحين مصلحين. واغفر لنا ولوالدينا وللمسلمين أجمعين. وأعنا على ذكرك وشكرك وحسن عبادتك. رب ارحمهما كما ربياني صغيرا 🤲 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

ይህንን ቪድዮ እናሰራጭ። የተፈፀመውን ሁሉም ያውቅ ዘንድ። ማብራሪያ መስጠት ያለበት ማብራሪያ ይሰጥ ዘንድ። መጠየቅ ያለበትም ይጠየቅ ዘንድ። ሊንኩ https://vt.tiktok.com/ZS9PMXMfg/ ነው። ግቡና ሪፖስት አድርጉ። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ! @aaumsu

ተለቋል! እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች እየደረሰብን ያለውን የመብት ጥሰት በመታገል ረገድ አሁናዊ ሁኔታን በደንብ የሚገልፀው ፖድካስት ተለቋል። ሊንክ https://youtu.be/OL
ተለቋል! እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች እየደረሰብን ያለውን የመብት ጥሰት በመታገል ረገድ አሁናዊ ሁኔታን በደንብ የሚገልፀው ፖድካስት ተለቋል። ሊንክ https://youtu.be/OLd-8QipP2k?si=JhpcMx-4MoqCpmnE ነው። ለሌሎችም ያድርሱ። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ©aaumsu @fivekjemaa

📣 Join the Muslim Developers Circle Mentorship Program! 💻✨ Assalamu Alaikum wa Rahmatullahi wa Barakatuh 🌙 Are you interested in building real tech skills and growing with a purpose-driven community? The Muslim Developers Circle is excited to open applications for our Mentorship Program! 🚀 🔹 Available Tracks: • Mobile App Development 📱 • Frontend Development 🎨 • Backend Development ⚙️ • UI/UX Design 🧩 👩🏽‍💻 Whether you're a beginner or have some experience, this is your chance to: ✔️ Learn from experienced mentors ✔️ Work on practical projects ✔️ Collaborate with like-minded Muslim students ✔️ Grow both technically and professionally 📝 Apply now through the form below: 👉 https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScmyfWGJBQA_jKFtIa2yLop478IAa9Cp8491eBJ1EXcwfv2DA/viewform?usp=publish-editorSpots are limited — don’t miss out! Those who have previously registered and haven't started classes yet are also advised to fill out the form since we are reorganizing the previous circles too. Let’s build skills, strengthen our ummah, and create impactful solutions together, inshaAllah! The official channel of Muslim Developers Circle: https://t.me/+-eAKAYVYRdxmYjI0

Here’s a polished and engaging Telegram post you can use to promote the form: 📣 Join the Muslim Developers Circle Mentorship Program! 💻✨ Assalamu Alaikum wa Rahmatullahi wa Barakatuh 🌙 Are you interested in building real tech skills and growing with a purpose-driven community? The Muslim Developers Circle is excited to open applications for our Mentorship Program! 🚀 🔹 Available Tracks: • Mobile App Development 📱 • Frontend Development 🎨 • Backend Development ⚙️ • UI/UX Design 🧩 👩🏽‍💻 Whether you're a beginner or have some experience, this is your chance to: ✔️ Learn from experienced mentors ✔️ Work on practical projects ✔️ Collaborate with like-minded Muslim students ✔️ Grow both technically and professionally 📝 Apply now through the form below: 👉 https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScmyfWGJBQA_jKFtIa2yLop478IAa9Cp8491eBJ1EXcwfv2DA/viewform?usp=publish-editorSpots are limited — don’t miss out! Those who have previously registered and haven't started classes yet are also advised to fill out the form since we are reorganizing the previous circles too. Let’s build skills, strengthen our ummah, and create impactful solutions together, inshaAllah! The official channel of Muslim Developers Circle: https://t.me/+-eAKAYVYRdxmYjI0

As-salamu alaykum, There is a sirah kitab (Ar-Rahiq al-Makhtum) dars at Aqsa, and we are in an amazing part the Battle of Badr. We learn a lot about the bravery of the Sahabah, even though they were few in number. As many of us are facing challenges in our din, including the niqab case, we can take strong lessons from this dars in patience, courage, and trust in Allah. Don’t miss it, in sha’ Allah?

⭕️Urgent Update ⭕️ ዛሬ ከአስር በኋላ ሊካሄድ የነበረው የንፅፅር መዝጊያ ፕሮግራም ከፕሮግራሞች ብዛት እና ካለን የሰዓት እጥረት አንፃር ማካሄድ ስላልተቻለ (ከመጝሪብ በኋላም የሲራ ደርስ ስላለ) ወደ ነገ ጁሙዓ ከዝሁር በኋላ  ተሸጋግሯል ለተፈጠረው መራዛም ዓፍውታ እየጠየቅን ❔በነገው ፕሮግራም በንፅፅር ዙርያ ያላችሁን ማንኛውም ጥያቄ ይዛችሁ መምጣታችሁን አትርሱ። የፕሮግራማችን እንግዶች 3ቱም ኡስታዞች ማለትም ✪Èmɾɑղ apologetics ✪ibrahim islamic Apologetics ✪ÀBÙBEĶEŔ ابوبکر ይገኛሉ በነገው ፕሮግራም ❀ ስለ ኤቲዝም እንማራለን ❀ የኡስታዞች ማጠቃለያ ሀሳብ ❀ ልዩ የሆነ የኮርስ የመዝጊያ ፕሮግራም ❀ ጥያቄና መልስ፤(ከሙስሊሞች+ከnon ሙስሊሞች ጋር) ❀ ኮርሱን ላጠናቀቁ የመጽሃፍ ሽልማት ከኡስታዞቹ እንቀበላለን ❀ ከኡስታዞቻችን ጠቃሚ ምክሮች እንቀበላለን ©AAU6kilojemea @fivekjemaa

Education in Islam is deeply valued 📚; it shapes both the individual and the المجتمع (community) 🌍. But with that value comes pressure; expectations, competition, and fear of failure . This is where Tawakul becomes essential ✨. “اعقلها وتوكل” (Tie your camel, then trust in Allah 🤲.) This principle reflects a sophisticated understanding 💡: Knowledge requires effort. Effort does not guarantee outcomes. Outcomes do not define your worth. 💎 In academic life, Tawakul allows students to: Stay committed without becoming overwhelmed. Reflect without self-judgment. Continue forward with clarity and patience. In this way, education is no longer just about results 📉 but about building discipline, resilience, and trust . ©Academic Sector

📍የአላህ ሸቀጥ ውድ ናት! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿مَنْ خَافَ أَدْلَجَ ، وَمَنْ أَدْلَجَ بَلَغَ الْمَنْزِلَ، أَلَا إِنَّ سِلْعَةَ اللَّهِ غَالِيَةٌ، أَلَا إِنَّ سِلْعَةَ اللَّهِ الْجَنَّةُ﴾ “የፈራ ይማልዳል (በጠዋት ተነስቶ ይወጣል)። በጠዋት የተንቀሳቀሰ ደግሞ ያሰበበት ይደርሳል። አዋጅ! የአላህ እቃ (ሸቀጥ) ውድ ናት። አዋጅ! የአላህ ሸቀጥ ደግሞ ጀነት ነች።” 📚 ቲርሚዚ ሶሂህ ብለውታል፡ 2450

የወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ባወጣው መግለጫ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች አጋርነቱን ያሳየ ሲሆን ለሚመለከታቸው አካላትም መልዕክቱን አስተላልፏል። በመግለጫው፦ እስከመጨረ
+1
የወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ባወጣው መግለጫ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች አጋርነቱን ያሳየ ሲሆን ለሚመለከታቸው አካላትም መልዕክቱን አስተላልፏል። በመግለጫው፦    እስከመጨረሻው ሰዓት ድረስ የሚጠበቅባቸውን በማድረግ ከተማሪዎቹ ጎን እንደሚቆሙ የገለፁ ሲሆን የፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ ከ9 ቀናት በፊት ለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ መፍትሔ ለማምጣት ቁርጠኝነታቸውን ከገለፁ ቡሃላ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ተወካዮች ጋር ይሰሩ ዘንድ የተቀመጡ አራት ነጥቦች ወደ ተግባር አለመለወጣቸው አስጊ እንደሆነ በመግለፅ ወደ ተግባር በቁርጠኝነት ይገባ ዘንድ ጠይቀዋል። ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል! ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! ©aaumsu @fivekjemaa

የመቱ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት ያወገዘ ሲሆን የሚከተሉትን መልዕክቶችንም
+1
የመቱ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት ያወገዘ ሲሆን የሚከተሉትን መልዕክቶችንም አስተላልፏል። ለAAU ሙስሊም ተማሪዎች፦ እየጠየቃችሁ ያላችሁት የእኛን፣ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን የጋራ ጥያቄ ነው። ሙስሊም እንደ አንድ አካል ነውና ወንድሞቻችሁ ባስፈለጉበት ጊዜ እና ቦታ ሁሉ ከጎናችሁ መሆናቸውን እወቁ።"  ለፌደራል መጅሊስ፦ ከ9 ቀናት በፊት የፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም የዩኒቨርስቲውን ፕሬዚዳንት ጨምሮ የሚመለከታቸውን አካላት አናግረው መፍትሔ ለማምጣት እንደተስማሙ ቢገልፁም እስካሁን ድረስ መፍትሔ የሚሆን ነገር አላየንም። ስለሆነም መጅሊሱ ሀላፊነቱ እንደሆነ በቁርጠኝነት ወስዶ አስቸኳይ እና ፍትሐዊ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ እንዲሰራ ጥሪያችን ነው። ለመንግስት፦ ሙስሊም ተማሪዎች በሰላማዊ መንገድ ለጠየቁት ጥያቄ ውይይትን መሠረት ያደረገ፤ ሕግ እና ስርዓትን የተከተለ እንዲሁም አጥፊዎችን ተጠያቂ የሚያደርግ መፍትሔ እንዲመጣ ይሰራ ዘንድ ጥሪያችን ነው። ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል። ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው ! ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ©aaumsu @fivekjemaa

ምሽት ላይ በሙባረክ ፖድካስት ይጠብቁ ! @aaumsu

لسَّلَامُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللّٰـهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋 💥 የደርስ ማስታወሻ:::::::::::::::::: ✅ ኢንሻአላህ የኡምደቱል አህካም ደርስ የሚኖረን ይሆናል።ከመጝሪብ እስከ ኢሻ ባለው ስአት በ4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ እንገናኝ። 🕌 «በሱ ውስጥ እውቀትን ለመፈለግ ብሎ መንገድን የጀመረ ሰው አላህ በሱ የጀነትን መንገድ ያገራለታል» ነብዩ ﷺ✨ @aau4kilomsj

🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋 ✅ኢንሻአላህ ዛሬ (እሮብ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ።  5ኪሎ እና 6ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል  ቡዙ እናተርፍለን። "مَنْ سَلَكَ طَرِيقًا يَلْتَمِسُ فِيهِ عِلْمًا، سَهَّلَ اللَّهُ لَهُ بِهِ طَرِيقًا إِلَى الْجَنَّةِ" «በሱ ውስጥ እውቀትን ለመፈለግ ብሎ መንገድ የጀመረ  ሰው አላህ የጀነትን መንገድ ያገራለታል» ነብዩ ﷺ ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ ቦታ፡ አቅሳ መስጅድ 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/durus_at_aqsa ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934 @fivekjemaa

#ስለመንገዱ 🫧ከ ባለፈው ሳምንት የ እህቶች ውይይት ፕሮግራም የተወሰደ ጽሑፍ🫧 🍂ይህንን ፅሁፍ ስፅፍ ፊት ለፊቴ አንድ ሗላው በሰማይ ያሸበረቀ ያማረና የተዋበ ረጅም ዛፍ አለ።ቅጠሎቹ ይወዛወዛሉ ግን አልረገፉምም አልወደቁምም!! የሀሳብ አለም ውስጥ ከተምኩ! በምናቤ አንዲት ውብ፣ኢትዮጵያዊት፣ሙስሊም፣ወጣት እና ትምህርት ወዳድ ሴት መጣች።መስታውቷ ፊት ቆማ ለመውጣት ሂጃቦቿን ትመርጣለች። "ይህ ስስ ነው አይሆንም፤ኡ...ይህማ አጭር ነው አይይ፤ ይህ ደግሞ ከአባያዬ ጋር አይሄድም..." እያለች በመጨረሻም አንዱን መርጣ ለብሳ በነፃነትና በሰላም ለመውጣት ዝግጁ ናት። ድንገት የሆነ ማዕበል እንደወረደበት ሰው ደርቃ ቀረች! ቀስ እያሉ አይኖቿ እንባ ማፍሰስ ጀመሩ። ምን መሰላችሁ: ብዙዎቻችን የዘነጋነው ዛሬ ላይ የእምነት፣ውበትና ክብራችን መገለጫ የሆነው ሂጃብን ከመልበስ ጀርባ ያለው መራራ እውነት እና ደም ትዝዝ ብሏት ነው!! ለመሆኑ ከዚህ ሂጃባችን ጀርባ ያለውን ነገር አስተውለን እናውቃለን ?! ኧረ ምን በወጣን! እንዲህ በደከምንበት ሁኔታማ አደለም አርቆ አቅርቦ ማሰብም ተስኖናል! ወላሂ ነው የምላችሁ እህቶችዬ ወደድንም ጠላንም ከዚህ ሂጃባችን ጀርባ የደመቀ እና የበዛ የመስዋዕትነት ደም አለ! ምናልባትም ሩጫ ውስጥ ሆኖ ከዲኔ አይበልጥም ብሎ ሁሉን ትቶ ለኛ ሂጃብ ተሰውቶ ልጆቹን የቲም አድርጎ የሞተ አባት !! ምናልባትም ደግሞ ሙስሊም ልጄ ላይ ዛሬም ወደፊትም እንባን ማየት አያስችለኝም ብላ ህይወቷን ረስታ በጭቆና የተሰዋች እናት!!  ምናልባትም ሙስሊም መምህራን ፣ ምናልባትም ደግሞ ብዙ ቤተሰብ ልጄ ተመርቆ ሊመጣልኝ ነው እያሉ ሚጠብቁት እሱ ግን ኢስላም ሳይከበር እህቶቼ ተባረው የኔ ትምህርት ደም ደም ይለኛል ብሎ በትግል ህይወት ውስጥ የነበረ ፣ ወይ ብዙውን ወይ ራሱን ያጣ ሙስሊም ወንድም!! እና ብዙ የዚያን ጊዜ የትግል ባለ ታሪክ የሆኑ እህቶች .. እንዲህ እንደቀልድ በነፃነት ለብሰን ስንወጣ እና በየቀኑ በጣም ከለመድነው ሂጃብ ጀርባ ያለው እዉነታ ይህ ነው:: ሰላም የሚነሳ፣ ያልተቋረጠ ፣ ውዶችን ያሳጣን የደመቀ የመሰዋትነት ደም!!! ስለዚህ ነቅትን እንደ ግለሰብ ሳይሆን እንደ ጀመዓ ፣ ነገሩን ለጥቂት እህቶች ብቻ ሳይሆን እያንዳንዳችን በጋራ ለመፍታት ቁርጠኛ እንሁን ። አለበለዚያ ብቸኛ ምርጫችን ድል አድርጎ የሂጃብ ጉዞን በመሙላት ኒቃብ በነፃነት እንዲለበስ፣ እንድንማር : አባቶቻችን እንዲሁ ብዙ ስቃይ እንግልትን አልፈው ይህንን ዉብ እስልምና እዚህ ያደረሱልን ዉዱ ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) እና ተከታዮቻቸውን ሚያስታውሰን በጥቂቱም ቢሆን በዲን መታገል ምን ያህል ሰላም እንደሆነ አዉቆ በሰላም መኖር ሳይሆን ••• በልፋት የመጣው ሀገራችን ዉስጥ ያለው እስላማዊ ነፃነታችን በእሳት ሲቃጠል ቆመን እናያለን•• ወይ ደግሞ ጥቂት እህት ወንድሞቻችን ነገሩን ታግለውት ተሳክቶላቸው የስኬት አካል ባለመሆናችን ደም ስናለቅስ •• አልያም ጥቂት ሆነው ሲታገሉ ንፋሱም አወዛዉዞ ሊጥላቸው ሲሞክር: እንደ ቅጠሎቹ በዝተን በጋራ እንዳንወድቅ ማድረግን እንረሳና እነሱ ለዲናቸው ብለው የደረሰባቸውን ግፍና ጭቆና እያየን የኛ ትምህርት ያለ እነሱ ደም ደም እያለን ህይወታችን ሰላም አጥቶ እንኖራለን... ••ስለዚህ መቋጫው 1 ነው!!•• እህቶቼ የሰው ልጅ ጊዜው ራሱ የአላህ ነውና አላህ ከሰጠው ጊዜው በሱ መንገድ ላይ መኖር ካቃተው :ለተፈጠረለት አላማ እንዲኖር ሚያመቹ መንገዶችን ጌታው ሲያገራለት ደግሞ መገራት ከተሳነው •• ሰላም የሌለው, ከመሞት ያላነሰ, ያለበት ማይዋጥለት, ሚያየው ማይስበው, ሚኖረው ማይገባው የሆነ የሸይጣን መጫወቻ ሚመስል ሂወት እንዲኖር ይገደዳልና.. ንቅት ብለን, ከአላማ ጋር: አላህ ባበጀልን መንገድ ላይ በዱዐ እየታገዝን በዚህ ውብ የትግል መንገድ ላይ ከጉዞ ፋናዎቻችን 1ዱ አሻራና ፋና የኛ ይሆን ዘንድ ሰበብን በግራ:  ዱዐ, ተወኩልን ደግሞ በቀኙ እጃችን አጥብቀን ይዘን እየተራመድንንን......... #ስለመንገዱ @aaumsu

ጃዕፈር ቢን ሙሐመድ (رحمه الله) ለሱፍያን አስሰውሪ እንዲህ አሉት፦ አንተ ሱፍያን ሆይ! ﴿إذا جاءك ما تُحب؛ فأكثر من (الحمد لله)، وإذا جاءك ما تَكره؛ فأكثر من (لا حول ولا قوة إلا بالله)، وإذا استبطأت الرّزق؛ فأكثر من(الاستغفار). قال سفيان، رحمه الله: فانتفعت بهذه الموعظة﴾ “የምትወደው ነገር ከመጣልህ ‘አልሐምዱሊላህ’ ማለትን አብዛ። የምትጠላው ነገር ከመጣብህ ‘ላሓውላ ወላቁወተ ኢልላቢላህ’ ማለትን አብዛ። ሲሳይ ከቆየብህ ‘እስቲግፋር’ ማድረግ አብዛ።” ሱፍያን (رحمه الله) እንዲህ ይል ነበር፦ “በዚህ ምክር ተጠቅሚያለሁ።” 📚ሒሊየቱል አውሊያ ለአቢ ነዒይም፡ 2/475

🔥ከ ሙተነቂቦች መንደር~5🔥
🍂ከዛው ከሙተነቂቦች መንደር ያለሁ አህታችሁ ነኝ እስቲ ከሕይዎቴ ገጠመኝ 1ዱን ላጋራችሁ
የሰው ልጅ በጠዋት ተነስቶ ቀኑን እንዴት እንደሚውል ያስባል። ዛሬስ ምን አስበን ይሁን የተነሳነው...እንዳሰብነውስ እየዋልን ይሆን ?? ••ያው ሰው ግን ቁርሱን በልቶ ምሳ መድረሱን አላህ ብቻ ሚያውቅለት ደካማ ፍጡር ነው። በአላህ ፍቃድ ስር ያሉ እና ከማንጠብቃቸው አጋጣሚዎች ውስጥ አንዱ ህመም ነው። 1 ቀን እንደማንኛውም ተማሪ ለጠዋት class ለመድረስ እየተዘጋጀሁ ሳለ, قدر ሆነና የህመም ስሜት ተሰማኝ እንደምንም class እንዳልሄድ እንኩዋን አቅም አጣሁ፣ ህመሙም ባሰብኝ °° ግቢ ከባድ ነው ቤት ቢሆን ህመም ሲፈጠርር ያለውን የውድድ ቤተሰብ ጭንቀት እና እንክብካቤ እያሰብኩ፣ እያመመኝ፣ እየከፋኝ ብቻዬን እዛው ግቢ ያለው clinic ለመታከም አስቤ ከዶርም ወጣሁ። ያው ሰበቡን ላድርስና በቶሎ ወደ ጤናዬ እና ትምህርቴም ልመለስ እያልኩ ይህንንን እያሰብኩ ከclinicኡ በርር ደረስኩ •• ወደ ውስጥ ገባ ስል ህመም ላይ ህመም ሚጨምርር የፊት expression ጠበቀኝ። አይይይይ ይህ ይሁን ዶክተሩሩ ?? አልኩኝ በውስጤ ብቻ ማነሽ ?!! ሲል ጠየቀኝ እኔም ነገረ ስራውን ignore አርጌ ለራሴም ሕክምና ብቻ ይስጠኝ እንጂ ይህ ሚያስጠላ ማስተናገዱን ዋጥጥ ላርግ ብዬ ስሜን ነገርኩት ጉድድድ እኮ ነው ከዛ ምንሽን አሞሽ ነዉ ?! እንደ ማለት ምን ፈልገሽ ነዉ? ሲለኝ ህመሜ ላይ ንዴቴ ሲጨመር  ተሰማኝ ዋጥ አድርጌ 🤐 የሱን ኮስታራ ፊት እና ሚገፋ አወራር እንደምንም እየቻልኩ ህመሜ ይብሳል ብዬ አሞኛል እና ልታከም ነዉ የመጣሁት አልኩት :: ከዛ በዛው በተለመደው ደባሪ አወራሩ "ቁጭ በይ..Id አምጪ" አለኝ!!ሰጠሁት። በቃ ትክክለኛውን ጥያቄ አሁን መጠየቅ ጀመረ አልሃምዱሊላህ•• በመጨረሻም ምንሽን አሞሽ ነዉ?? አለኝ ሁኔታውም ስላልተመቸኝ ህመሙም እረፍት ስለነሳኝ ቶሎ ታክሞ መውጣት ነበር የፈለኩት ምን አንደሆንኩ ነገርኩት ሕክምና ይጀምራል ብዬ ሲጠብቅ በጣምም ውስጤን ሚያቃጥል ፣ ሕመሜን ሚያስረሳ፣ ከዚህ በላይ መታገሥ እንደሌለብኝ ውስጤ እንዲነግረኝ ሚያደርግ ነገር ገጠመኝ clinicun በንዴት ውስጥ ሆኝ ጥዬ ወጣሁ!!! በቃሽሽሽ አዎ በቃሽ አልኩት ለራሴ •• ምን ገጥሞኝ ወጣሁ መሰላችሁ ?? እንደ ሀኪም ቶሎ ሊደርስልኝ ሕመሜን ሊረዳኝ ሲገባ•• በዛ መንገድ ስያዋራኝ አልበቃ አለው!! አረረረረ እሱን ተዉት ተማሪ መሆኔ እኮ ግልፅ ነዉ መቼስ id ቢኖረኝ ነዉ ግቢ ራሱ የገባሁት (ለዛውም ሙተነቂብ እንዴት እንደሚገባ ታቁታላችሁ 😒)። ተማሪ ብሆን ነዉ ዶርም አድሬ በዛ ጠዋት clinic የሄድኩት!! እሺ ይሁን ብዬ ላለመከራከር እና ቶሎ ለመታከምም ነበር id የሰጠሁት ግን ምን አንደገጠመኝ ታቃላችሁ .. Id አይቶ ሕመሜን ጠይቆ ከጨረሰ ቡሃላ ስራውን ይሰራል ብዬ ስጠብቅ "ፊትሽን ክፈች" አለኝ ግንፍል ብዬ ለምንንን ?!! አልኩት አይገርማችሁም id አይቶ ተማሪ መሆኔን ካረጋገጠ ቡሃላ "ፊትሽን ካላየው ተማሪ መሆንሽን በምን አውቃለው" አለኝ ያኔ አልቻልኩም ተናድጄ ጥዬ ወጣሁ በቃ!! ከዚህ ምንረዳው ብዬ ወሬ አላብዛባችሁ እኔ ታሪኬን አጋራሁ እናንተ አህት ወንድሞቼ ፍረዱም!!ተረዱም!! ©aaumsu @fivekjemaa