5killo Jem'a official Channel
رفتن به کانال در Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
نمایش بیشتر1 159
مشترکین
-124 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
60 ቀናት ሞላ
በዚህ ምሽት ዩኒቨርስቲው ካዘጋጀው የኢፍጣር መድረክ የተገኙ ሒጃቢስቶች "ጥያቄ አለን! መልስ ስጡን!" - በማለት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ማሰማታቸውን ታሪክ በወርቃማ ብዕር ከትቦ አልፏል። ሒጃቢስቷ "ከምግቡ በፊት ነፃነቴ ይቀድማል። ካከበራችሁኝ መብቴን አክብሩ።" - በማለት ተናግራ ነበር። ምሽቱን የነበሩ የግቢው አካላት በማግስቱ ፕሬዚዳንቱ ባሉበት ውይይት ተደርጎ መፍትሔ እንደሚመጣ ቢገልፁም ጁምዓ ሲደረስ ደግሞ ከአዲስ አበባ ከተማ ፀጥታ እና ብልፅግና ቢሮ የመጡ አካላት ቀጠሮው ለሰኞ ይዛወር ብለው መድረክ እንደሚዘጋጅ ቃል ገብተው ነበር።
ሆኖም ይህ ቀን ካለፈ ዛሬ 60 ቀናት ሞላ። ጥያቄያችንን እንመልሳለን ያሉ አካላት ሳይመልሱ፤ ውይይት ይካሄዳል ብለው ቃል የገቡት ቃላቸውን ሳያከብሩ 60 ቀናት ሞላ። በሒጃብ ምክንያት ሰብዓዊ መብቷ ለተገፈፈው እህት ፍትሕ ይሰጥ ዘንድ፤ ችግሮች በውይይት ተፈተው የዩኒቨርስቲው ስም ይመለስ ዘንድ፤ አጥፊዎች ይቀጡ ዘንድ መድረክ ይዘጋጃል ተብሎ ሳይዘጋጅ 60 ቀናት አለፉ።
ቀናት አለፉ ማለት ግን ጥያቄውም አለፈ ማለት አይደለም። ውይይትን ተመራጭ መንገድ አድርጎ መፍትሔን መሻት ፍርሃት ሳይሆን ብስለት ነው። ሆኖም ግን ለውይይት የተጋበዙ እና እንደሚካሄድ ቃል የገቡ አካላት ቃላቸውን ባለማክበራቸው መፍትሔ ሳይመጣ ቀርቷል። ስለሆነም መፍትሔው ይመጣ ዘንድ ጠንከር ብሎ መጠየቅ፤ ጠንከር ብሎ ድምፅን ማሰማት፤ ተቀናጅቶ እና ተናቦ መንቀሳቀስ ግድ ነው። ይህ ይሆናል። ሲሆንም መፍትሔው በቅርቡ ይመጣል። ኢንሻአላህ!
ጥያቄ አለን _ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
©aaumsu
@fivekjemaa
🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋
✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ማክሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ። 6ኪሎ እና 5ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል ቡዙ እናተርፍለን።
⏰ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ
🕌ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ።
https://t.me/durus_at_aqsa
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934
@fivekjemaa
ሒጃቧ - ማንነቷ!
መገለጫዋ ነው
ማንነት ምስጢሩ፥ የተወጠነበት፣
የሴትነት ሀሁ
የተፈጥሮ ሚዛን፥ ጸንቶ የቆመበት።
እሷነት ነው ሒጃብ
ጥንት የተሰጠችው፥ የገጿ ላይ አርማ፣
በወቅት አይደበዝዝ
አረጀብኝ ብላ፥ እትጥለው ከርማ።
እቃዋም አይደለም
ሲያሻት የምትጥለው፥ ደግሞ 'ምታነሳው፥
የመኖር ምሷ ነው
ከራሷ ተገምዶ፥ እሷው የምትለብሰው።
ማንነት ነውና
ነፍስና ስጋዋን፥ ተዋሕዶ ያለ፣
እሷን ከሂጃቧ
የምትነጥልበት፥ ጉልበት ወዴት አለ?
©EHEMSU
Repost from AAU - Muslim Students Union
ጥያቄ አለን ማለት ከጀመርን 624 ቀናት ሞላ። መመሪያው በረቂቅነት ደረጃ ሳለ በመስከረም 15, 2017 ዓ.ል ነበር ጥያቄ አለን በማለት በአምስት ኪሎ ግቢ ድምፃችንን ከፍ አድርገን ያሰማነው። የዚያኔ ለጥያቄያችን ምላሽ ላለመስጠት መድረኩን ረግጠው ቢሄዱም ቢሯቸው ድረስ ተሰብስበን በመሄድ ደጋግመን ጠይቀናቸው ነበር። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ለ20 ወራት እና 19 ቀናት ብንጠይቅም በውይይት አምኖ ለጥያቄያችን ምላሽ ለመስጠት ከጠረጴዛ በአግባቡ የተቀመጠ አካል የለም። ለጥያቄያችን የተነፈገው ትኩረት እና በሂደቱ የተሰጠው ግብረመልስ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያለውን ውይይት ጠል እና ሙስሊም ጠል አካሄዶችን የሚያሳይ ነው። ምንም ቢሆን ምን መብቶቻችንን በመጣሳቸው ፍትሕን ለመጠየቅ የጀመርነው ጉዞ አይቋጭም። በሰላማዊ መንገድ በአስቸኳይ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ዳግም እንጠይቃለን።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
Umar ibn Al-Khattab እንዲህ ብለዋል፦
“እኛ ከሁሉ የተዋረድን ሕዝቦች ነበርን፤ አላህ ግን በእስልምና ከፍ አደረገን። ከእርሷ ውጭ ክብርን ብንፈልግ አላህ ያዋርደናል።”
ብዙ ሰዎች ክብርን በተከታዮች፣ በዝና፣ በግንኙነት ወይም በሰዎች ዘንድ ይፈልጋሉ።
ነገር ግን ለአላህ የሚሰግድ፣የሚታገል ልብ ከዙፋን በላይ ይቆማል።
ሁሉም የተደፋ ራስ፣የተለፋ ልፋት ድካም ብቻ አይደለም፤ክፍያው ጀነት ነውና
وباالله توفيق
©
Alhamdulillah, today at the 5K Muslim Developers Circle (MDC) Meetup, we had a very engaging and beneficial session filled with insightful discussions and interactive conversations 🤍💻 at Ambassodor musalla.
what We discussed in detail:
📚 Structured Learning Paths
💼 Job Preparation & Applications
🌍 Freelancing & Remote Opportunities
📈 Current & Emerging Tech Trends
🎤 Interactive Q&A Sessions
The Q&A session was especially valuable, as audience members had the opportunity to ask important questions and receive insightful answers from our respected guests and speakers.
We would like to sincerely express our heartfelt gratitude to our esteemed guests and speakers:
🤝 Abdulmunim
🤝 Abdulfetah
🤝 Abdulkerim
🤝 Seid
🤝 Mohammed
🤝Anwar
Jazakumullahu Khairan for sharing your experiences, knowledge, and valuable advice with the community. Your contribution truly inspired and benefited many attendees 🌿
In Sha Allah, we will continue organizing more developer meetups and beneficial sessions in the future as we continue building and uplifting the Muslim tech community together 🚀
We would also like to sincerely apologize for the low voice volume experienced during today’s session. We'll conduct a program fully equipped regarding everything after this. In Sha Allah, we will work on improving this in future events that we are planning to prepare. As the saying goes, "Though no one can go back and make a brand new start, anyone can start from now and make a brand new ending." Get ready to give us a second chance!
Lastly, today’s meeting recording will be shared on the MDC channel, In Sha Allah 🎙✨
https://t.me/+-eAKAYVYRdxmYjI0
🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋
✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ። 6ኪሎ እና 5ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል ቡዙ እናተርፍለን።
⏰ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ
🕌ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ።
https://t.me/durus_at_aqsa
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934
@fivekjemaa
🚫 እይታን መስበር!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿فالعينانِ تزنيانِ وزناهما النظرُ﴾
“አይኖች ዝሙት ይፈፅማሉ። ዝሙታቸው ደግሞ የተከለከለን ነገር መመልከታቸው ነው።”
📚 ቡኻሪ (6612) ሙስሊም (2657) ዘግበውታል
ኢብኑልቀዪም (ረሂመሁላህ ) እንዲህ ይላሉ፦
﴿العين مرآة القلب، فإذا غض العبد بصره غض القلب شهوته وإرادته، وإذا أطلق بصره أطلق القلب شهوته﴾
“አይን የልብ መስታዎት ነው። አንድ ባሪያ አይኑን ሲሰብር ልብ አጉል ስሜትና መሻቱን ይሰብራል። አይኑን ሲለቅ ደግሞ ልብ ስሜቱን ይለቃል።”
📚 ረውደቱል ሙሒቢን፡ 92
وَلَا تَهِنُوا(አትድከሙ/አትስነፉ)፦
የሰበሰባችሁት 1,141 ፊርማ በ "X" ሲሰረዝ፣ የተወካዮቻችሁ ድምፅ "አናውቃችሁም" ተብሎ ሲናቅ፣ በሩ ላይ ያሉት ጥበቆች መንገዱን ሲዘጉባችሁ... አትድከሙ! የእናንተ ጥንካሬ የሚለካው በሮች በመከፈታቸው ሳይሆን፣ በሮች ተዘግተውባችሁም ለቆማችሁለት አላማ ባለመደላደላችሁ (resilience) ነው።
وَلَا تَحْزَنُوا(አትዘኑ)፦
ርቦሽ ከካፌ ስትባረሪ፣ ታመሽ ከክሊኒክ ስትገፊ፣ ወይም መምህራን ማርክሽን ቀንሰው ሊያሸማቅቁሽ ሲጥሩ... አትዘኚ! ይህ የአጭር ጊዜ እንግልት ነው። እነሱ 'እየቀጣናችሁ ነው' ብለው ቢያስቡ፣ አላህ ግን በሰማይ ቤቱ ለአንቺ የክብር ማዕድ 🍱 እያዘጋጀ ነው። ውጤትሽን በወረቀት ላይ ቢቀንሱትም፣ በእርሱ ዘንድ ያለሽ ደረጃ ግን ከፍ ያለ ነው።
وَأَنتُمُ الْأَعْلَوْنَ(እናንተ የበላይ ናችሁ)፦
ሀቅ ነው! ኒቃብሽን እንደ "ስጋት" ለሚቆጥሩት፣ ክብራቸውን ለዲግሪ ለሸጡትና የሌላውን ጥላ ለሚከተሉት ሰዎች አትሸማቀቂ። "በጥላ ውስጥ የሚቆይ ሰው ጥላ የለውም!" እንደሚባለው፣ ማንነታቸውን ደብቀውና የሌላውን ቀለም ለብሰው የሚሄዱት እነርሱ እንጂ፣ በፀሐይ ተቃጥለሽም ቢሆን የራስሽን የፅናት ጥላ ይዘሽ የቆምሽው አንቺ የበላይ ነሽ! ዲግሪ ካንቺ በታች ነው፤ ኒቃብሽ ግን የፈጣሪሽ አደራ በመሆኑ ካንቺ ጋር ከፍ ያለ ነው።
ባርነት ወይስ ዕውቀት?
ዛሬ ላይ ባለመማር ሊቀጡሽ የወሰኑ አካላት አንድ ነገር ሊረዱ ይገባል፤ ጥያቄሽ አንድና ግልፅ ነው— "መማር እፈልጋለሁ!" ነገር ግን ስትማሪ ክብርሽን፣ ሞገስሽንና ኒቃብሽን ጠብቀሽ ነው። ያለ ዲንሽ ሕይወት የለሽም፤ ያለ ተቅዋ ትምህርት ትርጉም አይሰጥሽም። የታላቁ ነቢያችን (ሰ.ዐ.ወ) አደራ የሆነውን ዲን አጥፍተሽ የምታመጪው ዲግሪ ለቤትሽም ለሀገርሽም በረካ አይሆንም። አንገትሽን አስደፍተው፣ በራስሽ ማንነት እንድትሸማቀቂ አድርገው የሚሰጡሽ እውቀት እውቀት ሳይሆን 'ባርነት' ነው።
አብሽሪ! አንቺ አትሰበሪም!
ለካፌና ለክሊኒክ ስትከለከዪ፣ በሩ ላይ ስትገፊና ስትገለዪ "ተሰበረች" ብለው ለገመቱ ሁሉ የምንለው፤ ይሄ ጫና የሚጨምረው ጥንካሬሽን እንጂ ድካምሽን አይደለም። ዛሬ በሩን ቢዘጉብሽ፣ ተቅዋን በልብሽ ካኖርሽ..
ረቡና በውብ ንግግሩ እንዲህ ሲል አብሽር ይልሻል፦
وَمَن يَتَّقِ اللَّهَ يَجْعَل لَّهُ مَخْرَجًا ۞ وَيَرْزُقْهُ مِنْ حَيْثُ لَا يَحْتَسِب
...አንቺ ብቻ እኔን ፍሪ እንጂ ላለሽበት ጭንቀት እና ጫና መውጫን አደርግልሻለሁ፤ ምን እሱ ብቻ ባላሰብሽው በኩልም ሪዝቄን እረዝቅሻለሁ ይልሻል። አንገትሽን ሊያስደፉሽ በሞከሩ ሰዎች ፊት፣ በኩራት ቀና ብለሽ የምትሄጂበት ቀን ደግሞ እሩቅ አይደለም። Inshallah ❤️
.... أَلَا إِنَّ نَصْرَ اللَّهِ قَرِيبٌ
(እውቁ! የአላህ እርዳታ ቅርብ ነው) ፦
የእርሱ እርዳታ በቢሮክራሲና በሰው ፍቃድ የታጠረ አይደለም። ለጊዜው ነገራቶችን እያየ ዝም ያለው አንቺ እንድትሰበሪ or ሊቀጣሽ ሳይሆን፣ በፅናትሽ ታሪክ ሰርተሽ ለድል እንድትበቂ ነው።
ሀስቡነላህ ወኒእመል ወኪል!
ሰዎች "ተከታታይ ክስ መስርተንባችኋል፣ አናውቃችሁም፣ ዲግሪ የላችሁም" ብለው ሊያስፈራሯችሁ ሲሞክሩ፣ ቁርአን የሚሰጣችሁ 'ወኔ' ግን ፍፁም የተለየ ነው ፦
الَّذِينَ قَالَ لَهُمُ النَّاسُ إِنَّ النَّاسَ قَدْ جَمَعُوا لَكُمْ فَاخْشَوْهُمْ فَزَادَهُمْ إِيمَانًا وَقَالُوا حَسْبُنَا اللَّهُ وَنِعْمَ الْوَكِيلُ
Look... እነሱ 1,141 ፊርማን ሲንቁ፣ አንቺ ግን "አላህ በቂዬ ነው" ስትይ፣ ሰማይና ምድር ካንቺ ጋር ይቆማሉ። ዲግሪ ወረቀት ነው፤ ኒቃብሽ ግን 'ሞገስ' ነው። ዛሬ አንገትሽን ሊያስደፉሽ የሞከሩ ሁሉ፣ ነገ በፅናትሽ ብርሃን አይናቸው ሲታወር ታያለሽ።
አብሽሪ እህቴ! አንቺ የአላህ እንግዳ እንጂ የካምፓስ ስደተኛ አይደለሽም። ዛሬ በካፌው በር ብትከለከዪም፣ ነገ በጀነት በር 'ያለምንም ሂሳብ' የምትገቢው አንቺ ነሽ!
"ኒቃቧንም ትለብሳለች... ትምህርቷንም ትማራለች!"
❤️🩹ከ ቁርአን አያህ...©ከቁርአን አያህ #AAUMuslimStudents #DignityOverEverything #KeQuranAyah #JusticeForNiqabis #Ethiopia ©aaumsu @fivekjemaa
Repost from 5killo Jem'a official Channel
⚡️ The wait is over… THE REVELATION IS HERE!
✨Aselamu Aleykum Werahmetu'llahi Weberekatuh!✨
Introducing the first-ever 5K MDC Meetup — where Muslim developers, learners, mentors, and graduates come together to connect, learn, and grow. 💻✨
From structured learning and job preparation to freelancing, opportunities, tech trends, and interactive Q&A sessions — this is more than a meetup. It’s the beginning of something bigger.
🗓 Monday, May 11, 2026
📍 Ambassador — after Asr Prayer
One community. Countless possibilities. Infinite reward.
Here's the link to our circle👇👇
https://t.me/+-eAKAYVYRdxmYjI0
©Academic Sector
🌟ዱዓእን አብዝቶ ማድረግ ያለው ትሩፋት!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿من مسلِمٍ يَدعو، ليسَ بإثمٍ ولا بِقطيعةِ رَحِمٍ إلّا أَعطاه إِحدى ثلاثٍ: إمّا أن يُعَجِّلَ لهُ دَعوَتَهُ، وإمّا أن يَدَّخِرَها لهُ في الآخرةِ، وإمّا أن يَدْفَعَ عنهُ من السُّوءِ مِثْلَها قال: إذًا نُكثِرَ، قالَ: اللهُ أَكثَرُ﴾
“አንድ ሙስሊም ዱዓእ በሚያደርግ ግዜ፤ ወንጀል እስካልሆነ ድረስና ወይም ደግሞ ዝምድናን በመቁረጥ እስካልሆነ ድረስ በሶስት መንገድ ምላሽ የሚሰጠው ቢሆን እንጂ። ወይ ዱዓእው ቶሎ ምላሽ ይሰጠዋል። (ተቀባይነት ያገኛል)፣ ወይ ደግሞ ለአኼራው ተቀማጭ ይደረግለታል፣ ወይ ደግሞ እሷን የሚመጥን ክፉ ነገር ይወገድለታል። በዚህ ጊዜ አንድ ሰው እንዲህ አለ፦ ‘ዱዓእ እናብዛ ማለት ነው!’ እንዲህ አሉት፦ አላህ (መልስ በመስጠት) የበለጠ ብዙ ነው።”
📚 ሶሂህ አል‐ዳቡል ሙፍረድ፡ 547
🌟 አብዛኛው ሰው በምን ያህል መከራ እያለፈ እንዳለ ስታውቅ በአስተውሎት በአንኩሮ የምታሰተውለው የታላቁ ነቢይ (ﷺ) ሐዲስ
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿مَنْ أصبَحَ منكمْ آمنًا في سِرْبِهِ، معافًى فِي جَسَدِهِ، عندَهُ، قوتُ يومِهِ، فكأنَّما حِيزَتْ لَهُ الدنيا بحذافِيرِها﴾
“በቤተሰቡ መሀል በሰላም ያደረ፣ ሰውነቱ በሙሉ ጤነኛ ሆኖ ያነጋ፣ የዕለት ጉርሱን ያገኘ፣ ዱንያን በሙሉ እሱ ዘንድ ሰብሰቧታል።”
📚 ሶሂህ አልጃሚ: 6042
🌟በርግጥም የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَقَلِيلٞ مِّنۡ عِبَادِيَ ٱلشَّكُورُ﴾ “ከባሮቼ በጣም አመስጋኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡” (ምዕራፍ ሰበእ: 34‐13)
❗️Venue update❗️
📍Location: Ambassador musala
📅 Date: Monday, May 11th, 2026
⏳ Time: After Asr prayer
Invite your colleagues and let's get together for a great experience sharing that will serve bigger purpose, insha'Allah!
See you there!
©Academic Sector
🌟ሪዝቅህን ሳትጠቀም አትሞትም!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿يا أَيُّها الناسُ إنَّ أحدَكم لن يموتَ حتى يَستكملَ رِزقَه فلا تَستبطِئُوا الرِّزقَ خُذُوا ما حَلَّ ودَعُوا ما حُرِّمَ﴾
“እናንተ ሰዎች ሆይ! አንዳችሁ ሞት አያገኝውም ሪዝቁን ተጠቅሞ ሳይጨርስ። ሪዝቄ ለምን ዘገየ አትበሉ (ከመድረስ ቅሮት የላትምና)። ሃላል (ከተፈቀደ) ነገር ብቻ ደግሞ ያዙ (ተጠቀሙ)። ሃራም (የተከለከለን) ነገር ደሞ ተው (ራቁ)።”
📚 ኢብኑ ማጃህ ዘግበውታል አልባኒ ሶሂህ ብለውታል፡ 2144
🎉ዛሬ ጁምዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ
ሰለዋትን እናብዛ🎉✨✨
💎 { إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا }
✨✨ ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ ✨✨
🌸የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
" የውመል ጁሙአ ቀኑንም ማታውን እኔ ላይ ሰለዋት ማድረግን አብዙ፡ እኔ ላይ አንድን ሰለዋትን ያወረደ አሏህ በሱ ላይ አስር ሰለዋት
ያወርድለታል........
"أكثروا الصلاة علي يوم الجمعة وليلة الجمعة فمن صلى علي صلاة صلى الله عليه عشراً"
ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣
ሰለዋት ጭንቀትን ይቀንሳል፣
ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣
۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦
➊ መታጠብ
➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች)
➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም
➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ
➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት
➏ በጊዜ መስጂድ መግባት
➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ
‣ በመጨረሻው ሰአት (ከአስር በኋላ ) ዱዓ ማድረግ- እስልምናን ለማስከበር ለሚታገሉ እህት/ወንድሞቻችን በዱዓ እናስታውሳቸው!!
اللَّهُمَّ اجعلهم مِنَ الَّذِينَ يَثْبُتُونَ عَلَى صِرَاطِكَ، وَثَبِّتْ قُلُوبَهُمْ عَلَى طَاعَتِكَ، وَانْصُرْهُمْ عَلَى أَنْفُسِهِمْ وَأَعْدَائِهِمْ
🌟 መልካም ጁምአ🌟
@fivekjemaa
⚡️ The wait is over… THE REVELATION IS HERE!
✨Aselamu Aleykum Werahmetu'llahi Weberekatuh!✨
Introducing the first-ever 5K MDC Meetup — where Muslim developers, learners, mentors, and graduates come together to connect, learn, and grow. 💻✨
From structured learning and job preparation to freelancing, opportunities, tech trends, and interactive Q&A sessions — this is more than a meetup. It’s the beginning of something bigger.
🗓 Monday, May 11, 2026
📍 Electrical Floor — after Asr Prayer
One community. Countless possibilities. Infinite reward.
Here's the link to our circle👇👇
https://t.me/+-eAKAYVYRdxmYjI0
©Academic Sector
