fa
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

رفتن به کانال در Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

نمایش بیشتر
1 162
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+37 روز
+730 روز
آرشیو پست ها
"እኔ ሙስሊም ነኝ፤ ሶላት መስገድ ግዴታዬ ነው። ልጄ ሙስሊማ ነች፤ ሒጃብ መልበስ ጎዴታዋ ነው። ማን ነው የሚከለክለው?!" - አልዩ ሰዒድ (በፌደራል መጅሊስ የትምህርት ክፍል ዳይሬክተር) ሐቅ ነው። ሴኩላር የሚሆነው በክፍል ውስጥ የሚማሩት ትምህርት እንጂ ተማሪው አይደለም። መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZSXQGbk4A/ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት አድርጉ። ወደ ተግባር! ይህ ትንሹ ሀላፊነት ነው!! @aaumsu

#ጣፋጭ #ሀዲስ ረሱል ሰ.ዐ.ወ ከሶሃቦቻቸው ጋር ቁጭ ብለው በዱኒያ ላይ በጣም  ስለሚዎዷቸው ነገሮች አየተጨዋወቱ እያሉ ነብዩ አቡበክርን "ያ አባ በከር አንተ በዱኒያ ላይ በጣም የምትወደው ነገር ምንድነው?" ብለው ጠየቁት። አቡበክርም "3 ነገሮችን እወዳለሁ:- 1.ከአንተ ጋር መቀመጥ፣ 2.አንተን ማየት፣ 3.አንተ ባዘዝካቸው ነገሮች ላይ በሙሉ ገንዘቤን መለገስ" ብሎ መለሰ። ° ዑመርን በተራው ጠየቁት "አንተስ ያዑመር ?" "በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ 1.በድብቅ እንኳን ቢሆን በመልካም ነገር ማዘዝ፣ 2.በግልጽ እንኳን ቢሆን ከመጥፎ ነገር መከልከል፣ 3 መራራ እንኳን ቢሆን እውነትን መናገር።" ብሎ መለሰ። ° ዑስማንን ጠየቁት "አንተስ ያዑስማን? በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ:- 1.ሰዎችን ማብላት፣ 2.ሰላምታን ማብዛት፣ 3.ሰዎች በተኙ ጊዜ ሶላትን ማብዛት፣ ° አልይን በተራው ጠየቁት "አንተስ ያአልይ ?" "በዱኒያ ላይ 3ነገሮችን እወዳለሁ:- 1.እንግዳን ማክበር፣ 2.በሙቀት ወቅት ፆምን መፆም፣ 3.ጠላቴን በሰይፍ መቅላት፣ ° አባ ዘርን በተራው ጠየቁት "አንተስ ያአባ ዘር?" "በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ :- 1.እርሃብን እወዳለሁ፣ 2.በሽታን እወዳለሁ፣ 3.ሞትን እወዳለሁ፣ ነብዩም "ያ አባ ዘር ለምን እነዚህን ወደድክ?" አቡዘር መለሰ "ረሃብን ወደድኩት ቀልቤን ፈሪ ሊያደርግልኝ ዘንድ፣ በሽታን ወደድኩት ወንጀሌን ሊያቀልልኝ ዘንድ፣ ሞትን ወደድኩት ከጌታየ ጋር ሊያገናኜኝ ዘንድ።" ብሎ መለሰ። ° ነብዩ ሰለላሁ አለየሂ ወሰለም🥰 " እኔም በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ:- 1.ሽቶን እወዳለሁ፣ 2.ሚስቶቼን እወዳለሁ፣ 3.የአይኔ ማረፊያ ሶላቴን እወዳለሁ፣ በዚህ መካከል ድንገት ጅብሪል ዱብ አለ ሰላምታ ካወረደ በኋላ እንዲህ አለ "አንቱ የአላህ መልዕክተኛ በዱኒያ ላይ እኔም 3 ነገሮችን እወዳለሁ ነብዩም ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም "ምንድናቸው ያ ጀብሪል?" ብለው ጠየቁት። 1.መልዕክትን ማድረስ፣ 2. አማናን አደራን መጠበቅ፣ 3.ሚስኪኖችን መውደድ፣ ጅብሪል ተመልሶ ወደ ሰማይ ከወጣ በኋላ ረሱልና ሱሃቦቻቸው ከመቀመጫቸው ሳይነሱ ተመልሶ ወደ መሬት ዱብ አለ አሁንም ሰላምታውን አቅርቦ:- "አላህም ሰላም ብሏችኋል ካለ በኋላ አላህም እንዲህ ብሏል:- በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ:- 1.አላህን አውሺ የሆነችን ምላስ፣ 2.አላህን ፈሪ የሆነችን ቀልብ፣ 3.መከራ የበዛበት ታጋሽ የሆነችን ጀሰድ። አላህ ታጋሾች አድርጎ ነብዩና ሱሃቦች የወደዱትን ያስወድደን! ©

🛠️ Thinking of Choosing Biomedical Engineering? The Unfiltered Truth 🇪🇹 💡 3 Ground-Level Realities 👉 It’s no longer just "fixing broken hospital gear": The era of being a glorified repair technician in Addis is over. The local healthcare market has matured. Modern BME in Ethiopia is heavily focused on hospital network architecture, medical IoT data pipelines, telemedicine infrastructure, and the calibration of advanced diagnostic arrays like high-field MRI, CT scanners, and automated molecular labs. 👉 The Tender, Procurement & Regulatory Boom: Ethiopia is aggressively upgrading its healthcare infrastructure. If you want to make an impact here today, you aren't just handling hardware; you are navigating EFDA (Ethiopian Food and Drug Authority) compliance, analyzing multi-million dollar international medical tenders, and designing specialized hospital environments (radiation shielding, clean rooms, isolated power grids) for public and private healthcare giants. 👉 The Global Standard vs. Local Resource Deficit: The local medical tech landscape is bottlenecked by foreign currency shortages and customs delays. This means as an Ethiopian biomedical engineer, you aren't just running manufacturer manuals; you are pushed to safely innovate, reverse-engineer, and maintain life-saving tech under severe resource constraints. Your training must match global safety standards because a miscalibration directly impacts human life. All of the above means the ceiling is incredibly high—but only if you treat healthcare technology as a high-stakes responsibility, not just a major. The Transition: You will move from basic freshman physics and mathematics into intense multi-disciplinary thinking. The real challenge is shifting from "memorizing anatomy" to complex troubleshooting. If you cannot spend six hours diagnosing a ghost signal on an EEG board, tracking down a calibration error, or studying international ISO codes without losing your patience, this field will drain you quickly. 🔗Join our resource sharing group for Biomedical department here: https://t.me/+Syg1aAUjtOZhYzFk ✍Academic Sector

Biomedical Stream.MP312.55 MB

🛠️ Thinking of Choosing Software Engineering? The Unfiltered Truth 🇪🇹 💡 3 Ground-Level Realities 👉 It’s no longer just "writing HTML websites": The era of getting paid well just for building basic WordPress sites or landing pages in Addis is over. The local market has matured. Modern SE in Ethiopia is heavily focused on secure system architecture, cloud DevOps, data pipelines, and building complex integrations for massive platforms like Ethio Telecom’s Telebirr, CBE Birr, and the Commercial Bank of Ethiopia. 👉 The "Fayda" & Fintech Infrastructure Boom: Ethiopia is aggressively building its Digital Public Infrastructure (DPI). If you want to build high-impact software here today, you aren’t coding in a vacuum; you are writing OAuth 2.0 or OpenID Connect integrations to hook into Fayda (the National Digital ID) APIs, or syncing customer account data for banks. The engineering demand is shifting from isolated apps to massive, interconnected national systems. 👉 The Silicon Valley Bridge vs. Local Brain Drain: The local tech landscape is heavily shaped by competitive elite pipelines like A2SV (Africa to Silicon Valley). This means as an Ethiopian software engineering student, you aren't just competing with the person sitting next to you in class; you are being pushed to train at a standard that lands graduates directly at global tech giants like Google, Amazon, and Bloomberg in Europe and the US. All of the above means the ceiling is incredibly high—but only if you treat coding as a competitive sport, not just a major. The Transition: You will move from basic freshman calculus into intense abstract thinking. The real challenge is shifting from "memorizing code" to problem-solving. If you cannot sit in front of a laptop for six hours trying to find a single missing semicolon or broken API endpoint without throwing your computer, this field will drain you quickly. Join our resource sharing group for Software department here: https://t.me/+bUv8Yyj8bvVhMDRk ✍Academic Sector

Software Stream.MP316.60 MB

ሰላሙዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁ!📢 ለመላው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት  አባላት በሙሉ የተላለፈ ጥሪ! ​ዛሬ በሀገራችንም ሆነ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች ከምንጋፈጣቸው ግዙፍ አስተሳሰቦች መካከል የ Secularism ጉዳይ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። ይህ አይዲዮሎጂ ምን እንደሆነ፣ እንዴት እንደሚተገበርና ድንበሩ የት ድረስ እንደሆነ በበቂ መልኩ ግንዛቤ ያልተፈጠረለት መሆኑ ፤ በተለይም የሃይማኖት ነፃነትን ለመጠበቅ ከሚያገለግለው መርህ ውጭ በተሳሳተ መልኩ ሲተረጎም፣ ሙስሊም ተማሪዎች የራሳቸውን እምነታዊ መብቶች እንዳይጠቀሙና በግቢ ውስጥ ከእምነታቸው ጋር ለመኖር እንዳይችሉ የሚያደርጉ ከባድ ተቋማዊና ስነ-ልቦናዊ ጫናዎችን እየፈጠረ ይገኛል። ስለሆነም ተማሪው ይህንን ሐሳብ በሕግና በተቋማዊ አውድ ውስጥ ምን እንደሚመስል አውቆ፣ የራሱን መብትና ግዴታ ተገንዝቦ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ጽኑ አቋም እንዲኖረው ማገዝ የህልውና ያህል አንገብጋቢ ሆኗል። ​የ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች 6 ኪሎ ጀምዓመ ይህንን ክፍተት ለመሙላት በቀጣዩ ሳምንት ስለ ሴኩላሪዝም እጅግ ጥልቅና መሠረታዊ የሆነ ስልጠና በዚሁ ቻናል ላይ ይዞላችሁ የሚቀርብ ሲሆን፤ በተመሳሳይ መልኩ በ6 ኪሎ ጀመዓ ዋና ቻናል ላይ ደግሞ ስለ ፌሚንዝም ሰፊ ስልጠና በቀጣዮቹ ሳምንታት ይካሄዳል። ​ነገር ግን......እነዚህን ግዙፍና ፈታኝ ዘመናዊ አስተሳሰቦች ከመጋፈጣችን በፊት የታጠቅነው መሣሪያ ምንድን ነው? ​እነዚህን ርዕሶች በጥልቀት ለመረዳት፣ መብቶቻችንን ለማስከበርና ግራ መጋባት ውስጥ ሳንገባ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ሚዛናዊ እስላማዊ አቋም ለመያዝ የመጀመሪያውና ዋናው ቁልፍ ሂሳዊ አስተሳሰብ (Critical Thinking) ነው። ያለ ሂሳዊ አስተሳሰብ የሚቀርቡልንን መረጃዎች ማጣራት፣ መተንተንና ሚዛናዊ በሆነው እስላማዊ ዕይታ መመዘን በፍጹም አንችልም። ​ስለሆነም ለሕብረታችንም ሆነ ለጀመዓው ስልጠናዎች እንደ ወርቃማ መክፈቻና እንደ መከላከያ ጋሻ የሚያገለግለውን ነገ ቅዳሜ እና ከነገ በስቲያ እሁድ (ሐምሌ 11 እና 12) ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በ6 ኪሎ ጀመዓ ዋና ቻናል የሚሰጠውን የ"Critical Thinking" ስልጠና መከታተል ለሁላችንም እጅግ ወሳኝ መሠረት ነው! ​በዚህ  ስልጠና ላይ የምንዳስሳቸው ዋና ዋና ንዑስ ርዕሶች የሚከተሉት ናቸው፦ 1. ​ሂሳዊ አስተሳሰብ ለምን ያስፈልገናል? (Why Do We Need Critical Thinking?) 2. ​የሂሳዊ አስተሳሰብ ሕጎች (Rules of Critical Thinking) 3. ​ለአንድ ሐሳብ ለእያንዳንዱ ክፍል የሚነሱ ሂሳዊ ጥያቄዎች (Critical Questions for Each Part of the Idea) 4. ​የቀረቡ ማስረጃዎችን በሂሳዊ ጥያቄዎች መመዘን - ሦስተኛው ሕግ (Directing Critical Questions to the Evidence - The Third Rule) 5. ​ማስረጃዎችን በትክክል መረዳትና በወጥነት ሥራ ላይ ማዋል (Correctly Understanding and Consistently Applying Evidence) ​​ይህን ለቀጣዩ ሳምንታት ስልጠናዎቻችን ትልቅ መነሻ የሚሆነውን ስልጠና የሚሰጥልን ወንድማችን ጋዜጠኛ አብዱረሂም አሚን ነው። ወንድም አብዱረሂም በአሁኑ ወቅት በሀሩን ሚዲያ ላይ በጋዜጠኝነት እያገለገለ የሚገኝ ሲሆን፤ በኢቲቪ  እና በሌሎች የተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ከ6 ዓመታት በላይ የስራ ልምድ ያለው ባለሙያ ነው። በአሁኑ ሰዓት በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ ብዙም ትኩረት ያልተሰጣቸው ነገር ግን በውስጣችን ሰርገው በመግባት ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ ባሉ ዘመናዊ አይዲዮሎጂዎች (Modern Ideologies) ዙሪያ ያሉ ክፍተቶችን ለመሙላትም በርካታ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ ይገኛል። ​የዛሬው በ 6 ኪሎ ጀመዓ የሚካሄደው የ"Critical Thinking" ስልጠና በዚሁ ቻናል ላይ ለሚተላለፈው የሴኩላሪዝም ስልጠና መሰረት በመሆኑ፤ ሁላችሁም ከወዲሁ ጊዜያችሁን አመቻችታችሁ እንድትገኙና ይህንን መልዕክት ለሌሎችም ተማሪዎች በማጋራት እንድታደርሱ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ፕሮግራሙ በቀጥታ የሚተላለፍበት የቴሌግራም ቻናል 👇 https://t.me/AAU6kilojemea

🙏 ለሰላምህ ስትል ሰላምታን አብዛ! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿السلامُ اسمٌ من أسماءِ اللهِ وضَعَهُ اللهُ في الأرضِ، فأفْشُوهُ بينَكمْ، فإنَّ الرجلَ المسلمَ إذا مَرَّ بقومٍ فسلَّمَ عليهم، فردُّوا عليه؛ كان لهُ عليهم فضلُ درجةٍ بتذكيرِهِ إيّاهُمُ السلامَ، فإنْ لمْ يرُدُّوا عليه رَدَّ عليه مَنْ هوَ خيرٌ مِنهمْ وأطْيبُ﴾ “አስ-ሰላም ከአላህ ስሞች ውስጥ አንዱ ስም ነው። አላህ በምድር ላይ (ሰላምታን ትለዋወጡበት ዘንድ) አስቀምጦታል። በመሆኑም በመካከላችሁ (ሰላምታን) አብዙ። አንድ ሙስሊም ሰው በሰዎች አጠገብ ሲያልፍና ቀድሞ ሰላምታ ሲያቀርብላቸው፣ እነሱም መልስ ከሰጡት፤ ሰላምታን በማስታወሱ ብቻ በእነሱ ላይ የአንድ ደረጃ ብልጫ (ተጨማሪ ምንዳ) ያገኛል። እነሱ መልስ ካልሰጡት ግን፣ ከእነሱ የተሻለና ይበልጥ የጠራው የሆነ አካል (መላኢይካ) መልስ ይመልስለታል።” 📚 ሶሂህ አልጃሚ፡ 3697

🛠️ Thinking of Choosing Civil Engineering? Here is what you need to know 🇪🇹 💡 3 Fast Facts 👉With the integration of Building Information Modeling (BIM), structural simulation software, and smart city technologies, modern Civil Engineering in Ethiopia is heavily merging with digital project management, coding, and environmental data. 👉The Backbone of Infrastructure: From the massive expanding highway networks and light rail systems to high-rise skylines in Addis and large-scale water dams, Ethiopia’s physical development runs on the expertise of civil engineers. 👉Highly Versatile: It allows you to pivot into structural design, geotechnical investigation, water resources, transport planning, or construction management. All of the above could be seen as an opportunity if you have the will to grow and discipline to strive. 📈 The Learning Curve (What to Expect) The Transition: You will move from basic freshman math and physics into intense subjects like Strength of Materials, Structural Analysis, Fluid Mechanics, and Soil Mechanics. The Challenge: The curve is steep. You will need to transition from theoretical equations to real-world safety calculations, mastering CAD and structural design software, and understanding complex building codes. Join our resource sharing group for civil department here: https://t.me/+G4bHIHi__v1iYjU0 ✍Academic Sector

Civil Stream.MP36.78 MB

በሀገራዊ ምክክር ላይ የሕዝበ ሙስሊሙን አጀንዳዎች ይዘው ለቀረቡ ተወካዮች ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የተላለፈ መልዕክት፦ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት እና የሀገራችንን እጣፋንታ በውይይት ለማስመር የተጀመረው እና ለ30 ቀናት የሚቆየው ሀገራዊ ምክክር በታሪክ ስለሀገራዊ ችግሮቻችን ውይይት ለማድረግ የመጣ ታሪካዊ እድል፤ በአግባቡ ከተጠቀምንበት ደግሞ ጥያቄዎቻችን በውይይት ምላሽ የሚያገኙበት የድል መድረክ ነው። በተለይም ከ8ቱ የምክክር አጀንዳዎች 4ተኛ እና 5ተኛ የሆኑት የሀይማኖት ጉዳዮችየተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነት እና ሰብዓዊ መብቶች አጀንዳዎች ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከትምህርት ቤቶች ጀምሮ በሴኩላሪዝም እና መሰል የዳቦ ስሞች እየደረሱበት የነበሩትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ተከትሎ ያደረገውን ሰላማዊ ትግል ተከትሎ ወደ መድረክ የመጡ ናቸው። ከምክክሩ ቡሃላ በሀይማኖት ነፃነት እና በሴኩላሪዝም መካከል ያለው ቅርርብ እና ርቀት፤ ትክክለኛው ኢትዮጵያዊ ሴኩላሪዝም፤ የሙስሊም ተማሪዎች የሀይማኖት ነፃነት መብቶቻቸው እንደሚበየኑ እና ፍትሐዊ በሆነ መልኩ ተግባራዊ የሚደረጉበት መንገድ እንደሚቀመጥ እናምናለን።   ስለሆነም በሙስሊሙ ማህበረሰብ ተወክላችሁ ወደ ምክክሩ ለገባችሁ የሚከተሉት መልዕክቶች አሉን፦   ፨ ሀገራችን ሴኩላር ሆና ሙስሊሙ ማህበረሰብ የሐይማኖት ነፃነት መብቱ ተከብሮለት ይኖር፣ ይማር እና ይሰራ ዘንድ በአባቶቻችን የተከፈለው መስዋዕትነት በታሪክ መዝገብ ደምቆ ያለ ነው። ለዚህ ጉዳይ መሳካት የነበረውን መስዋዕትነት፣ መናበብ፣ ቁርጠኝነት እና ህዝባዊ ተሳትፎ እነ ሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ሀቢብ (ረህመቱላሂ ዐለይህ) በየቢሮው እየዞሩ ከሚያስገቡት ደብዳቤ፣ ከሚያቀርቡት ቅሬታ፣ ከሚያደርጉት ክርክር ባሻገር በሚያዚያ 12 / 1966 ሕዝበ ሙስሊሙ መቶ ሺዎችን ሆኖ ሰልፍ በማድረግ ባሰማው ተቃውሞ፤ ይህንንም ተከትሎ የነበሩ ሕዝባዊ ንቅናቄዎችን በሰለጠነ መንገድ ማካሄዳቸው የሚጠቀስ ነው። የነበረው ስኬት የሐይማኖት ነፃነት እና እኩልነት መብቶቻችንን በወረቀት እንዲሰፍሩ ማድረግ ቢችልም እነዚህ መብቶቻችን ግን የትምህርት ተቋማትን አጥር ማለፍ ሳይችሉ፤ ወደ ሕዝብ አደባባዮች እና የመንግስት መስሪያ ቤቶች ሳይሻገሩ፤ ከአየር መንገድም ሳይገቡ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ለተደጋጋሚ ጭቆና እና ትግል እንዲጋለጥ አድርጎታል።    እንደ ሙስሊም ተማሪ ከቅርብ ጊዜያት ጀምሮ በትምህርት ተቋማት ውስጥ እያገረሸ በመጣው ሙስሊምጠልነት ለመሠል የመብት ጥሰቶች እና ጥያቄዎች ተጋላጭ መሆናችንን ተከትሎ መፍትሔ ለመሻት ወደተለያዩ ተቋማት ስናቀና እንድንጠብቅ ከተነገሩን መድረኮች መካከል የሀገራዊ ምክክሩ ዋነኛው ነው። ስለሆነም በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚደርሰው መዋቅራዊ መድሎ እና ጭቆና ታሪክ ሆኖ ያልፍ ዘንድ የተገኘውን ታሪካዊ መድረክ በአግባቡ መጠቀም የሁላችንም ሀላፊነት ነው። እድል ሆኖም ለምክክሩ የታጫችሁ ሰዎች አማና ነውና ሙሉ ትኩረታችሁን ከምክክሩ ላይ አድርጋችሁ፤ ስለሕዝበ ሙስሊሙ ዘርፈብዙ ጥያቄዎች ትሟገቱ፤ መብቶቻችን በዘላቂነት የሚተገበሩበት መንገድ እንዲፀኑ ትሰሩ ዘንድ ሀላፊነታችሁ ነው።    አላህ ያግዛችሁ። መብቶቻችን ተከብረው በነፃነት በእኩልነት እና በፍትሕ የምንኖርባትን ሀገር ይስጠን። @aaumsu

አሰላሙዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁ ! ​የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የ6 ኪሎ ጀመዓ ሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ሴክተር ለመላው የጀመዓችን አባላትና ተማሪዎች እጅግ አንገብጋቢና ወቅታዊ የሆነ ታላቅ የ Online ስልጠና ይዞላችሁ ቀርቧል። በቀጣዮቹ ሳምንታት በጀመዓችን ቻናል ላይ በዘመናችን በተለይም በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ህይወትና ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሰፊ ተጽዕኖ እያሳደሩ ባሉ ሁለት አበይት ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ስልጠናዎችን የምንሰጥ ይሆናል። እነዚህም ታሪካዊ አመጣጡን፣ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች እና እስልምና ስለ ሴት ልጅ ክብርና መብት ያለውን ሚዛናዊ እይታ የምንዳስስበት በ Feminism ርዕስ ዙሪያ ስልጠና እንዲሁም ትርጉሙን፣ በሀገራችንና በዩኒቨርስቲያችን ያለውን ተግባራዊ ተጽዕኖና በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚፈጥረውን ጫና የምንማርበት የ Secularism ስልጠና ናቸው። ​ሆኖም ግን እነዚህን ውስብስብ ዘመናዊ አስተሳሰቦች (Ideologies) በጥልቀት ለመረዳት፣ ትክክለኛውን ከስህተቱ ለመለየት እና ግራ መጋባት ውስጥ ሳንገባ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ሚዛናዊ እስላማዊ አቋም ለመያዝ የመጀመሪያውና ዋናው ቁልፍ "Critical Thinking" (ሂሳዊ አስተሳሰብ) መኖር ነው። ያለ ሂሳዊ አስተሳሰብ የምንሰማቸውን ማናቸውንም መረጃዎች መመዘንና መተንተን አንችልም። ስለሆነም ወደ ዋናዎቹ ርዕሶች ከመግባታችን በፊት በዚህ ሳምንት መጨረሻ ቀናት ልዩ የቅድመ-ዝግጅት ስልጠና በ"Critical Thinking" ርዕስ ዙሪያ አዘጋጅተንላችኋል። ​ይህን እጅግ ወሳኝ ስልጠና የሚሰጠን ከወር በፊት በጀመዓችን ቻናል ላይ ስለ "Content Creation" ድንቅ ስልጠና አቅርቦልን የነበረው ወንድማችን ጋዜጠኛ አብዱረሂም አሚን ነው። ወንድም አብዱረሂም በአሁኑ ወቅት በሀሩን ሚዲያ ላይ በጋዜጠኝነት እያገለገለ የሚገኝ ሲሆን፤ በኢቲቪ  እና በሌሎች የተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ከ6 ዓመታት በላይ የስራ ልምድ ያለው ባለሙያ ነው። በአሁኑ ሰዓት በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ ብዙም ትኩረት ያልተሰጣቸው ነገር ግን በውስጣችን ሰርገው በመግባት ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ ባሉ ዘመናዊ አይዲዮሎጂዎች (Modern Ideologies) ዙሪያ ያሉ ክፍተቶችን ለመሙላትም በርካታ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ ይገኛል። ​ይህ ልዩ ስልጠና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን በዚሁ በ6 ኪሎ ጀመዓ ዋና ቴሌግራም ቻናል ላይ የሚተላለፍ ሲሆን፣ ከዛሬ 3 ቀናት በኋላ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ቅዳሜና እሁድ (ሐምሌ 11 እና 12) በሀገር ውስጥ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ የሚሰጥ ይሆናል። እራሳችንን በዕውቀት የምናንጽበትና ዘመናዊ ፈተናዎችን በንቃት የምንከላከልበት ታላቅ መድረክ በመሆኑ ሁላችሁም ከወዲሁ ዝግጁ እንዲትሆኑና ይህንን መልዕክት ለሌሎችም በማጋራት የበኩላችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።  ፕሮግራሙ በቀጥታ የሚተላለፍበት ቻናል👇 https://t.me/AAU6kilojemea @AAU6kilojemea

🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ ﷺ 🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟 ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት "ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።" ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልባችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው። ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️ اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

Surah_Al_Juma_Tranquility_Omar_Hisham_Al_Arabi_سكينة_سور.m4a3.76 MB

🛠️ Thinking of Choosing Mechanical Engineering? Here is what you need to know 🇪🇹 💡 3 Fast Facts 👉It’s no longer just "grease and gears": With the rapid rise of EV assembly (like Dodai in Addis) and automated factories, modern ME in Ethiopia is heavily merging with electronics, robotics, and coding. 👉The Backbone of Industrialization: Ethiopia's industrial parks and massive energy projects like the GERD run on the expertise of mechanical engineers. 👉Highly Versatile: It allows you to pivot into automotive, aerospace, manufacturing, energy, or construction. All of the above could be seen as an opportunity if you have the will to grow and discipline to strive. 📈 The Learning Curve (What to Expect) The Transition: You will move from basic freshman math and physics into intense subjects like Thermodynamics, Fluid Mechanics, and Machine Design. The Challenge: The curve is steep. You will need to transition from memorizing formulas to visual thinking, using CAD (Computer-Aided Design) software, and doing practical workshop training. It requires patience and strong spatial problem-solving. ✍Academic Sector

Mechanical stream.MP36.94 MB

📢 [ANNOUNCEMENT] New Series: Department Orientation — One Day, One Stream! 📚✨ To help you make an informed, wise, and confident choice, we are launching a brand-new series: One Department, One Day. 🗓️ How It Works: Every day, we will spotlight a different engineering stream. For each department, we will share: 🎙️ A Voice Record Orientation: In-depth insights from seniors and professionals sharing real experiences. 📝 A Quick-Fact Post: A short, precise breakdown of the department's reality in Ethiopia, its learning curve, and actual job opportunities. Make sure to catch up with the upcoming daily posts and share it with your peers! ✍ Academic Sector

በምርቃት ቀናቸው ስለታሰሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኒቃቢስት ተማሪዎች በዝርዝር ተነስቷል፤ በዩኒቨርስቲው ስለበጠለው የመብት ጥሰት፤ በግንቦት 7 ጁምዓ ምሽት መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ውይይት እንደሚደረግ ከተገለፀ ቡሃላ ስለነበሩት ሁኔታዎች ተብራርቷል። በደንብ አድርጋችሁ አዳምጡት። መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድም አሰራጩት። በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSXB5FKa1/ ይከታተሉ። ኮፒሊንክ ሪፖስት ያድርጉ። በYoutube ደግሞ በሱመያዎቹ ፖድካስት https://youtu.be/KzVdHbBx43M?si=R8TD8i0y4kJM52c1 ይከታተሉ። ጥያቄ አለን ... ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu