AACPPPDS
رفتن به کانال در Telegram
308
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
مه '24
مه '240
در 0 کانالها
آوریل '24
+48
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '24
+9
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+29
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+21
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+291
در 0 کانالها
پستهای کانال
| 2 | بدون متن... | 0 |
| 3 | የሠራተኞች የደምብ ልብስ ጨረታ የመክፈት ሥነስርዓት | 0 |
| 4 | የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የስድስት ወር ዕቅድ አፈፃፀሙን ከባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ
አገልግሎቱ ሀሙስ ታህሳስ 2016 በአዜማን ሆቴል ባከናወነዉ የእቅድ አፈፃፀም መድረክ ላይ በርካታ ተሳታፊዎች የታደሙ ሲሆን ከፋይናንስ ቢሮ ፣ ከአቅራቢዎች፣ ከክፍለ ከተሞች፣ ከምክር ቤት እና ከሴክተር መስሪያ ቤቶች እንዲሁም መሰል ተቋማት የተወከሉ አካላት ተገኝተዋል ፡፡
መድረኩ በተቋሙ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ አጥናፉ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የተከፈተ ሲሆን በአገልግሎቱ በመጀመሪያ ስድስት ወራት ዉስጥ የተከናወኑ የግዥ እና የማስወገድ እንዲሁም ጥራትን የተመለከቱ ተግባራት ሪፖረት ለተሳታፊ ቀርቧል ፡፡
የግዥ እና የማስወገድን በተመለከተ ሪፖርቱን ያቀረቡት የአገልግሎቱ እቅድ እና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ወርቅነህ በሪፖርቱ ከተፈፀሙ የግዥ እና የማስወገድ አፈፃፀሞች በተጨማሪ በመልካም አስተዳደር ፣ በቅሬታ አፈታት ፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ እና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ለተሳታፊ አቅርበዋል ፡፡
በመድረኩ ላይ በጥራት ማረጋገጥ እና ግንዛቤ ማስጨበጥ ቡድን በተከናወኑ የጥራት ማስጠበቅ ስራዎች እና በስራ ክፍሉ እንዲቋቋም አስገዳጅ ምክንያቶች ዙሪያ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በአጠቃላይ በቀረቡት ሰነዶች ዙሪያ ሰፊ ዉይይት ተከናዉኗል ፡፡
በመጨረሻም በዋነኝነት በተነሱ አቅርቦት እና ጥራትን በተመለከቱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ በሆኑት አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን እና በአገልግሎቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ አጥናፉ ሰፊ ማብራሪያ እና ምላሽ በመስጠት እንዲሁም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መድረኩ ያለመዉን በማሳካት እና ዉጤታማ በመሆን ተጠነቋል ፡፡ | 0 |
| 5 | بدون متن... | 0 |
| 6 | በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ።
የኤሌክትሮኒክ የመንግስት ግዥ ሥርአትን ለማስፋፋት በሚደረገው ጥረት እና በአጠቃላይ በ ኢ.ጂ.ፒ ምንነት እንዲሁም በውል እና በአስተዳደራዊ ዉል ዙሪያ የግንዛቤ ማሥጨበጫ ስልጠና ተከናወነ | 0 |
| 7 | بدون متن... | 0 |
| 8 | አገልግሎቱ በቅንጅታዊ አሰራር የትስስር ስምምነትን አስመልክቶ ከሴክተር ተቋማት ጋር የአፈፃፀም ግምገማ አከናወነ ።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ የተሠጠውን ተልዕኮ ለማሳካት እና ውጤታማ ለመሆን በየደረጃው ከሚገኙና የሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ትስስር ፈጥሮ በተቀናጀ ሁኔታ የድርሻቸውን እንዲወጡ በማስቻል የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል ።
በመሆኑም አገልግሎቱ በ 2016 በጀት ዓመት እስካሁን በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ጋር ያከናወናቸውን ተግባራት ባስቀመጠው ቅንጅታዊ አሠራር እና አቅጣጫ መሠረት ሪፖርቱን በማቅረብ አፈፃፀሙን ገምግሟል ።
በሪፖርቱም የተገኙ ውጤቶችን አስመልክቶ እንደተገለፀው በግዥና ንብረት ማስወገድ የሱፐርቪዥን ስራ መሠራቱ ፣ የጥራት ማሻሻያ መደረጉ ፣ የ 40/60 ድልድል በወቅቱ መከናወኑ ፣ ለቀረቡ ቅሬታዎች በወቅቱ ምላሽ መሠጠት መቻሉ ፣ የሚወገዱ ንብረቶችን በስፋት መለየት መቻሉ ተጠቃሽ ናቸው ።
መድረኩ በተስተዋሉ ተግዳሮቶች እና በገጠሙ ችግሮች ዙሪያ ውይይት የተከናወነ ሲሆን ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችንም በማስቀመጥ ተጠናቋል ። | 0 |
| 9 | በአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ 56/2010 ዙሪያ ለዓመራሩና ባለሙያው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተከናወነ።
ስልጠናው የተቋሙ ሠራተኞች በአዋጅ የተሠጣቸውን የአሠራር ሁኔታ እንዲሁም መብት እና ግዴታቸውን እንዲገነዘቡ ማስቻልን ዓላማ ያደረገ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በተጨማሪም በዕውቀት ላይ የተመረኮዘ ኃላፊነትን የመወጣት አቅምን በማዳበር የአገልግሎቱን ተልዕኮ ለማሣካት ምቹ መደላድል መፍጠር መሆኑም ተጠቅሷል ።
ስልጠናው በስራ አፈፃፀም ፣ በደረጃ እድገት ፣ በዝዉዉር ፣ የአሠሪ መሥሪያ ቤት ኃላፊነት ።፣ የሠራተኛ ግዴታ ፣ የሥራ ውል ማቋረጥ እና ማራዘም እንዲሁም የሥራ ዲስፕሊን እና መሠል ጉዳዮች ዙሪያ ትኩረት ያደረገ ነበርም ተብሏል ። | 0 |
| 10 | بدون متن... | 0 |
| 11 | በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ለዓመራሩና ባለሙያው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሠጠ።
ስልጠናው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የተከናወነ ሲሆን በኦዲት አሰራር እና የዉስጥ ቁጥጥር ፤ደምብና መመሪያን የተከተለ የግዥ ስርዓት ፤እንዲሁም በግዥ አፈፃፀም ዙሪያ እና በአጠቃላይ በስራ ወቅት ሊኖሩ ስለሚገቡ ሙያዊ ስነምግባሮች ላይ ትኩረት ያደረገ እንደሆነም ተገልጿል ። | 0 |
| 12 | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የተለያዩ መ/ቤቶችና ተቋማት ንብረቶች የተለያዩ ያገለገሉ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች፣ (የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ ባትሪዎች፣ ከነመዳሪዎች፣ ቸርኬዎች፤ ፍላፖች፣ በርሜሎች፣ የተሸከርካሪ መለዋወጫዎች፣ ያገለገሉ የህክምና ዕቃዎች፣ ያገለገሉ የኤሌክትሪክ መብራት ዕቃዎች፣ አዳዲስ የተሸከርካሪ መለዋወጫ) እና የአገልግሎት ዘመናቸውን የጨረሱ ወይም ተጠግነው አገልግሎት መስጠት የማይችሉ ኮምፒውተርና ተያያዥነት ያላቸው የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ሌሎችም በሽያጭ በግልፅ ጨረታ ለማስወገድ ማስታወቂያ ታህሳስ 4 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቷል፡፡
በዚሁ መሰረት መጫረት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከታህሳስ 4 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 18 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ሜክሲኮ ሰንጋ ተራ ዮቤክ የንግድ ማዕከል 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 606 በመገኘት የጨረታ ሰነድ በመግዛት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ጨረታው ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 4፡15 ላይ ይከፈታል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-557-86-71 ይደውሉ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሰት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት | 0 |
| 13 | بدون متن... | 0 |
| 14 | በወቅታዊ የገበያ ዋጋ መረጃ ዙርያ ነጋዴው ማህበረሰብ ትክከለኛ መረጃ መስጠት እንዲችል የግንዛቤ ማስጨበጥ እንቅስቃሴ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የገበያ ጥናት ዳይሬክቶሬት በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ መ/ቤቶች ክ/ከተሞች እንዲሁም ለሌሎች ባለበጀት መ/ቤቶች የተለያዩ የአገልግሎት የዕቃዎችን እና አገልግሎቶችን የገበያ ዋጋ ጥናት፤ የገበያ ዋጋ መረጃ ትንተና እና የዋጋ ማስተካከያ በመስራት አገልግሎቱ በጥናት የተደገፈ ውሳኔ እንዲወስን የገበያ ዋጋ ጥናት በማከናወን የበኩሉን ሚና እንደሚጫወት ይታወቃል፡፡
በገበያ ጥናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ በላይነሽ ደረጄ እንደሚያስረዱት ወቅታዊ የገበያ ዋጋ በሚጠናበት ወቅት የነጋዴው ማህበረሰብ ስለወቅታዊ የገበያ ዋጋ ምንነትና አላማ የግንዛቤ ክፍተት ስላለ ጥናቱን ከጊዜ ወደ ጊዜ ለዉሳኔ አዳጋች እና ጊዜ የሚፈጅ የመሆን ተግዳሮቶች እየተስተዋሉበት በመሆኑ ለነጋዴው ማህበረሰብ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ማከናወን ይደር የማይባል ነዉ ይላሉ፡፡
በመሆኑም የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዉ በሙሉ አቅም ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የተከናወነ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ በላይነሽ ደረጄ በዚህም ለ 113 (መቶ አስራ ሶስት ) የንግድ ድርጅቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ የተሰራ ሲሆን በዚህም ለፈርኒቸር ድርጅቶች፤ለፅህፈት መሳሪያ አቅራቢዎች፤ለፅዳት እቃ አቅራቢዎች ፤ለተሸከርካሪ እና ጎማ አቅራቢዎች፤ለደንብ ልብስ፤ለኤሌክትሮኒክስ እቃ አቅራቢዎች እና መሰል ድርጅቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ መስጠት ስራ ተከናዉኗል ብለዋል ፡፡
ከግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዉ በፊት የነበሩ የነጋዴው ማህበረሰብ አመለካከትን አስመልክቶ ያብራሩት የገበያ ጥናት ዳይሬክተሯ መረጃዉን የሚሰጠዉ ነጋዴ የገበያ ዋጋ ጥናት መሙላታችን ለኛ የሚሰጠን ምንም ጥቅም የለም ፣ለፕሮፎርማ ከሆነ ብቻ በትከክል ዋጋ የመሙላት እና መሰል የግንዛቤ ክፈተቶች እንደነበሩ ጠቅሰዉ ከግንዛቤ ማስጨበጥ ተግባሩ በኀላ ግን በየወቅቱ የገበያ ዋጋ መረጃ መስጠት ማለት ትልልቅ ሃገራዊ ውሳኔዎች ላይ ተሳትፎ ማድረግ ማለት በመሆኑ ትብብር ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን፤እና መረጃ መስጠት ዘመናዊነት ነው፤መረጃ መደበቅ በራስ አለመተማመን በመሆኑ መረጃ ለመስጠት ተነሳሽነታቸዉ መጨመሩን ጠቅሰዉ ፡፡
የሚያደርሰውን የተዛባ ውሳኔ በመረዳትም በተቀመጠው ስፔስፊኬሽን መሰረት ብቻ የእቃዎችን እና የአገልግሎቶችን ወቅታዊ ዋጋ በመሙላት ትብብራቸውን በቅንነት ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል ብለዋል ፡፡ | 0 |
| 15 | بدون متن... | 0 |
| 16 | بدون متن... | 0 |
| 17 | በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ከተቋቋመበት እና በአዋጅ ከተሠጠው ተልዕኮ ባሻገር በተለያዩ ሀገራዊ እና ማህበራዊ ኀላፊነቶች ላይ በንቃት ሲሳተፍ እና የበኩሉን ሚና ሲጫወት መቆየቱ ይታወቃል ።
ተቋሙ ይህንን ኀላፊነቱን በማሥቀጠልም ከ 13 በላይ የተለያዮ ይዘት ያላቸውን ለትምህርት አገልግሎት የሚውሉ በርካታ መፅሐፍትን ግዥ በመፈፀም ለ ሻውልደማ ትምህርት ቤት ድጋፍ አከናውኗል ።
የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ መንግስቱ አጥናፉ ድጋፉን አስመልክቶ እንደገለፁት << የተደረገው የመፃህፍት ድጋፍ የከተማ አስተዳደሩ እየተገበረው ላለው ትምህርት ቤቶችን የማጠናከር እና የማሻሻል እንቅስቃሴ የበኩሉን ሚና ይጫወታል >> ብለዋል ። | 0 |
| 18 | بدون متن... | 0 |
| 19 | ‹‹የማህበረሰብ መሪነት ለላቀ የኤች.አይ.ቪ መከላከል›› በሚል መሪ ቃል የዘንድሮዉ የዓለም የፀረ-ኤድስ ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ
የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰራተኞች እና ዓመራች የዓለም የፀረ-ኤድስ ቀንን በደማቅ ሁኔታ ያከበሩ ሲሆን በዓሉ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ 35ኛ ጊዜ ‹‹የማህበረሰብ መሪነት ለላቀ የኤች.አይ.ቪ መከላከል ›› (let communities lead) በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ዉሏል ፡፡ ዓለም አቀፉ የፀረ-ኤድስ ቀን በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች ኤች.አይ.ቪ በደማቸዉ ለሚገኝባቸዉና በቫይረሱ ጉዳት ለደረሰባቸዉ ወገኖች ድጋፋቸዉን ለማሳየት እንዲሁም በኤድስ ህይወታቸዉን ያጡትን ወገኖች ለማስታወስ በየዓመቱ ህዳር 22 (ዲሴምበር 1) እንደሚከበር የሚታወቅ ነዉ ነዉ ያሉት በዕለቱ የፀረ-ኤድስ ቀን ላይ ዕለቱን አስመልክቶ የዉይይት መነሻ ሰነድ ያቀረቡት የኮሚኒዩኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ይመር እንደገለፁት የኤችአይቪ/ኤድስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በመንግሰት በህዝብ ና በአጋሮች በተደረጉ ጥረቶች በአገራችን አበረታች ዉጤቶች በየደረጃዉ የተመዘገቡ መሆኑን ገልፀዉ የአለም አቀፉ የፀረ ኤድስ ቀን መከበር ጠቀሜታን አስመልክተዉም መንግስታት እና ውሳኔ ሰጭዎች ለኤች አይ ቪ/ኤድስ የሚሰጡትን ትኩረት እንዲያጠናክሩ ያግዛል፣ ህዝቦች ስለ ኤች አይ ቪ/ኤድስ ያላቸውን ግንዛቤ ይበልጥ እንዲያሳድጉ እና በወረርሽኙ ዙርያ ሁሌም ንቁ ሆነው አንዲሳተፉ ይረዳል፣ ኤች አይ ቪ/ኤድስ የደረሰበትን አጠቃላይ ደረጃ እና እየተሰጡ ያሉ ምላሾችን በጋራ እንድንገመግም እድል ይሰጣል፣ ከኤች አይ ቪ/ኤድስ ጋር ተያይዞ የሚሰጡ አገልግሎቶችን እንድናጠናክር ያበረታታል፣በአዲስ መንፈስ እና በአዲስ አቅም እንድንነሳሳ ያደርጋል ብለዋል፡፡
በመድረኩ በርካታ ጥያቄዎች እና ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን በተነሱት ላይም ሰፊ ዉይይት ተደርጎ እና የጋራ መግባባት ላይ ተደርሶ ተጠናቋል፡፡ | 0 |
| 20 | የጨረታ መለያ ቁጥር፡ AAPPPDS/FA/NCB/PG/47/03/2016
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለበጀት መስሪያ ቤቶች በማዕቀፍ ውል ስምምነት ግዥ የተለያዩ የተለያዩ የሰራተኞች ደንብ ልብሶች (Different types of Clothes for Employees) ዕቃዎች ግዥ ሀገር አቀፍ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መፈጸም ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም፡
• በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተወዳዳሪዎች ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ከህዳር 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ ከጧቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ድረስ ባሉት 20 ተከታታይ ቀናት ሰንጋ ተራ በሚገኘው ዩቤክ ኮሜርሻል ሴንተር ህንፃ ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት 6ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 606 በአካል በመቅረብ የማይመለስ 700 /ሰባት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
• ጨረታው ታህሳስ 12/2016 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዛው ዕለት ከረፋዱ 5፡30 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት 9ኛ ፎቅ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
• አገልግሎቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር +251- 11-557-31-70/40 በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ | 0 |
