fa
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

کانال بسته
1 148
مشترکین
-124 ساعت
-27 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
photo content
+7

photo content

26/01/2018 ዓ/ም የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሸራተን አዲስ ባለ 5 ኮከብ ሆቴል ለ15 የፍሮንት ኦፊስ(front office) ተመራቂዎች የስራ ቅጥር አመቻቸ ። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የፍሮንት ኦፊስ(front office) ተመራቂዎች ከሸራተን አዲስ ባለ 5 ኮከብ ሆቴል 19 ስልጣኞችን ቃለ-መጠየቅ  በማድረግ 15 በላይ ሰልጣኞችን ቅጥር ያገኙ ሲሆን የሆቴሉ የሰው ሀብት ማናጀር  አቶ ክፍሌ እና ም/ሀላፊ አቶ መስፍን  ከኮሌጃችን የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ም/ዲን አቶ ወንድምሲያረኝ አሰልጣኝ እሱእንዳለው:የስራ ትስስር አስተባባሪ ሙሉጌታ ጋር በመሆን ከቅጥር በዘለለ ቀጣይ ከኮሌጁ ጋር አብረን እንደምንሰራ መግባባት ተችሏል። በተጨማሪም የሆቴሉ አመራሮች በሆቴል ስልጠና ዘርፍ አብሮ ለመስራት የሆቴል የማሰልጠኛ ወርክ ሾፕ ለመጎብኝት እንደሚመጡ የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+7

photo content

photo content

አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ
አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ

photo content

ነገ ዓርብ ከቀኑ 6:00 ጀምሮ መንገዶች ይዘጋሉ። ከኢሬቻ በዓል ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆነዋል። የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ/ም በአዲስ አበባ ይከበራል፡፡ በመሆኑም የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል ተከብሮ እስከሚጠናቀቅ ፦ - ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ሜክሲኮ፣ - ከወሎ ሠፈር መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ፣ - ከቄራ ሜክሲኮ የሚወስደው መንገድ ቡልጋሪያ፣ - ከመርካቶ በአቡነ ተ/ኃይማኖት ወደ ጥቁር አንበሳ የሚወስደው መንገድ አቡነ ተ/ኃይማኖት ቤ/ክ፣ - ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣ - ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣ - ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣ - ከአጎና  ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣ - ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣ - ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣ - ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣ - ከሐራምቤ  መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ  መብራት፣ - ከአዲሱ ገበያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባንኮዲሮማ፣ - ከብሔራዊ ቤተ መንግስት  ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ  ብሔራዊ  ቤተ መንግስት አጠገብ፣ - ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ ሼል አጠገብ፣ - ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወስደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከመስከረም 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡ በዓሉ በሚከበርበት ዙሪያ እና በአካባቢው በግራና በቀኝ ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ እንደሆነ ፖሊስ አሳስቧል። ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት ፦ - በ011-1-26-43-59 ፣ - በ011-5-52-63-02/03፣ - በ011-5-52-40-77፣ - በ011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች ጥቆማ እንዲሰጥና አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል። Teteri Mekonnen

photo content

መስከረም 19/2018 ዓ/ም የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሰባተኛ ቀን ተካሄደ።በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት አቶ ኤፍሬም ሀብታሙ የተወለዱት አዲስ አበባ ልዩ ቦታው ቤላ እንደሆነና አንደኛ ደረጃ ትምህርት በህብረት ፍሬ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃ በከፍተኛ 12 ወይም ካራማራ እንደጨረሱና ድግሪያቸውን  በማኑፋክቸሪንግ  ቴክኖሎጂ ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ ሁለተኛ ድግሪያቸውን ከኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩንቨርስቲ አግኝተዋል።የስራ ልምዳቸውን በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅተው በመስራት፣ አዋሽ ኮንስትራክሽን በበያጅነት ፣ ኮተቤ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በሲ እና በቢ ደረጃ አሰልጣኝነት ፣ ልደታ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ምክትል ስራ መሪ ሆነው እንዲሰሩና በአሁኑ ሰአት በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  የኤ ደረጃ አሰልጣኝ እንደሆኑ  ገልጸዋል ። የሰው ልጅ ለውጥን እንዴት ይመለከታል በሚል መሪ ቃል ለኮሌጁ ህብረተሰብ ግንዛቤ የፈጠሩ ሲሆን የኮሌጁን ህብረተሰብ አንተ የትኛው ነህ ??? በጥንካሬ ወይስ በድክመት በማለት ቆም ብሎ እራሱን እንዲያይ አድርገዋል ። ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+6

መስከረም 19/2018 ዓ/ም የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሰባተኛ ቀን ተካሄደ።በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት አቶ ኤፍሬም ሀብታሙ የተወለዱት አዲስ አበባ ልዩ ቦታው ቤላ እንደሆነና አንደኛ ደረጃ ትምህርት በህብረት ፍሬ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃ በከፍተኛ 12 ወይም ካራማራ እንደጨረሱና ድግሪያቸውን  በማኑፋክቸሪንግ  ቴክኖሎጂ ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ ሁለተኛ ድግሪያቸውን ከኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩንቨርስቲ አግኝተዋል።የስራ ልምዳቸውን በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅተው በመስራት፣ አዋሽ ኮንስትራክሽን በበያጅነት ፣ ኮተቤ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በሲ እና በቢ ደረጃ አሰልጣኝነት ፣ ልደታ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ምክትል ስራ መሪ ሆነው እንዲሰሩና በአሁኑ ሰአት በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  የኤ ደረጃ አሰልጣኝ እንደሆኑ  ገልጸዋል ። የሰው ልጅ ለውጥን እንዴት ይመለከታል በሚል መሪ ቃል ለኮሌጁ ህብረተሰብ ግንዛቤ የፈጠሩ ሲሆን የኮሌጁን ህብረተሰብ አንተ የትኛው ነህ ??? በጥንካሬ ወይስ በድክመት በማለት ቆም ብሎ እራሱን እንዲያይ አድርገዋል ። ከኮሚኒኬሽን ቡድን

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ

photo content

ነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ ከሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ጋር በተያያዘ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች - ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣ - ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣ - ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣ - ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣ - ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣ - ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣ - ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣ - ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣ - ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣ - ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣ - ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ መንገድ ይዘጋል። በተገለፁት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አሳስቧል። አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል። ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ተላልፏል። T M S

photo content