fa
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

کانال بسته
1 148
مشترکین
-124 ساعت
-27 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
መስከረም 14፣ 2018 ዓ.ም. በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የመስቀልና የኢሬቻ በዓላት አከባበር ላይ ውይይት ተካሄደ "በእመርታና ማንሰራራት የታጀበ ህዝባዊ ባህላትን በጋራ እናክብር" በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የመስቀልና የኢሬቻ በዓላት አከባበርን አስመልክቶ "በእመርታና ማንሰራራት የታጀበ ህዝባዊ ባህላትን በጋራ እናክብር" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ በዓላቱ ሃይማኖታዊና ባህላዊ እሴቶቻቸውን ጠብቀው መከበር እንዳለባቸው ተገለጸ። የውይይት ሰነዱን ያቀረቡት የአካዳሚክና ስልጠና ዘርፍ ምክትል ዲን የሆኑት አቶ ደመላሽ ተስፋዬ፣ እነዚህ ታላላቅ የአደባባይ በዓላት የኢትዮጵያ የብዝሃነት መገለጫና የህዝብን አንድነት የሚያጠናክሩ እንደመሆናቸው፣ ዋና ማንነታቸውን ሳይለቁ መከበር አለባቸው ብለዋል። በተጨማሪም የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልባር መሀመድ "የመስቀልና የኢሬቻ በዓላት ለዘመናት የቆዩ፣ በውስጣቸው ሰፊ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ትውፊቶችን የያዙ ናቸው፡ እኛ የዚህ ትውልድ ባለአደራዎች እንደመሆናችን እነዚህን እሴቶች ሳንሸረሽር ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ታሪካዊ ኃላፊነት አለብን" ሲሉ በኮሌጁ ለተገኙ ተሳታፊዎች አሳስበዋል። በዓላቱ ለቱሪዝም መስህብነት ያላቸውን ጠቀሜታ የጠቀሱት ዲኑ፣ ይህንንም ተከትሎ የሚመጡ የውጭ ጎብኚዎች የኢትዮጵያን ትክክለኛ ገጽታ የሚረዱት በዓላቱ በባህላዊና ሃይማኖታዊ ይዘታቸው ሲከበሩ መሆኑን አስምረውበታል። አያይዘውም በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የሚያስገኘው ሀገራዊ ፋይዳ እንዲሁም በአሰልጣኞች ምዘና፣ ድልድል እና ዞኒንግ አተገባበር ገለፃ የተደረገ ሲሆን በመጨረሻም በመድረኩ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በኮሌጁ ዲኖች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል። ከኮሚዩኒኬሽን ቡድን

photo content
+7

photo content

photo content

photo content
+4

መስከረም 12/01/2018 ዓ.ም ተፈሪ መኮንን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት የ2018 ዓ.ም ዕቅድን ለኮሌጁ ማህበረሰብ በማቅረብ የጋራ ውይይት አድርጓል። በ2018 በጀት ዓመት የትውልድ ስነ ምግባር ግንባታ፣ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የሚያስችሉ ዋና ዋና ተግባራትና የትኩረት አቅጣጫዎችን ይፋ ባደረጉበት መድረክ ላይ ከኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርጓል። የኮሌጁ ስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ መከታው ሹመት፤ ዳይሬክቶሬቱ በትውልድ ስነ ምግባር ግንበባታና ብልሹ አሰራርን መከላከል ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ አስታውቀዋል። ለኮሌጁ ማህበረሰብ ከስልጠና ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በመነሳት የትውልድ ስነ ምግባር ግንባታ፣መልካም አስተዳደር፣ሙስናና ብልሹ አሰራርን መታገል የሚያስችሉ ስልጠናዎችን ይሰጣል። በተጨማሪም ለሙስናና ብልሹ አሰራር ተጋላጭ የሆኑ አሰራሮችን በጥናት በመለየት የማስተካከያ እርምጃዎችን መውሰድና በየደረጃው ተጠያቂነትን ማስፈን እንደሚገባ በውይይቱ ተመላክቷል። በመጨረሻም የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ለመልካም አስተዳደር መጎደል ምክንያት የሚሆኑ ብልሹ አሰራሮችን እና ሙስናን ለመከላከል የሚያስችል ተቋማዊ አሰራርን ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

photo content
+3

መስከረም 12/01/2018 ዓ.ም የወርቃማ ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ተካሔደ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማ ሰኞ የጋራ ልምድ ልውውጥ መድረክ ለስድስተኛ ቀን ተካሂዷል። በዕለቱ የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ የታላቁን ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ አስመልክቶ "በህብረት ችለናል የህዳሴ ግድብ ታሪካዊ ድል" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ፅሁፍ አቅርበዋል። በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የታየውን የህዝብ ድጋፍ በሌሎች ልማቶች ለመድገም በቅንጅት መስራት እንዳለብን፤ ይህንን ታሪክ ሰሪነታችንን አጠናክረን በማስቀጠል የተሻለ ለውጥ ለማምጣት በህብረት መቆም እንደሚገባን፤ የህዳሴ ግድቡ የሁሉም ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት መሆኑን እና ለሀገር እድገት የጎላ አስተዋፅዖ የሚያበረክት መሆኑን አብራርተዋል።

ባሳለፍነው ሳምንት

photo content

እንኳን ለ2017 ዓ.ም.የሰልጣኞች ምርቃት አደረሳቹ!!!አደረሰን!!! ዛሬ ቅዳሜ የምርቃት በዓል በታላቅ ድምቀት እንዲከበር ትልቅ እገዛ ያደረጋቹ ያስተባበራቹ የአካዳሚክ ኮሚሽን አባላት: የማነጅመንት አባላት: የኮሌጁ ዲኖች: የሬጅስትራል ፅ/ቤት: የስ/ት/ጋ/ካ/ስ/ክፍል አስተባባሪ: የኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪ:ነሙዚቃ ሴክሽን በእለቱ የተሳተፋ አሰልጣኞች: ሰልጣኞች:የጋርመንት ስልጠና ዘርፍ ተጠሪ: የኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፍ ተወካይ: የአይስቲ ስልጠና ዘርፍ ተወካይ: የሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፍ ተወካይ : የኮሌጁ ሰልጣኝ ካውንስል ፕሬዝዳንትና አባላት : የግዢ ዳሬክቶሬትና ባለሙያዎች: የፋይናንስ ዳሬክቶሬትና ባለሙያዎች: የንብረት ዳሬክቶሬትናባለሙያዎች:የኮሌጁ ሹፌሮች;የኮሌጁ ጥበቃ ሰራተኞች እና ሌሎች ልዪ እገዛ ላደረጋቹ በሙሉ በኮሌጁና በግሌ ላቅ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 በትብብር ማሳካት ይቻላል!!!! በድጋሚ እንኳን ደስ አላቹ!!!አለን!!!

photo content
+3

+2

photo content

photo content
+6

photo content
+2

ጠንካራ የስራ ባህልን ያዳበረ ትውልድ መገንባት ያስፈልጋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለአንድ ሀገር እድገትና ብልፅግና እውን መሆን በቴክኒክና ሙያ ጠንካራ የስራ ባህልን ያዳበረ ትውልድ መገንባት ያስፈልጋል አሉ። ከንቲባ አዳነች ይህን ያሉት የከተማ አስተዳደሩ ስራና ክህሎት ቢሮ በመንግስት የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች በመደበኛና በማታ መርሐ ግብር ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ 7 ሺህ 149 ሰልጣኞችን ባስመረቀበት ወቅት ነው። ቢሮው በፍላጎት መር የስልጠና መርሐ ግብር ከደረጃ ሁለት እስከ ደረጃ አምስት ለቢሮው ተጠሪ በሆኑ 14 የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች በ22 የስልጠና ዘርፎች ሰልጥነው ብቁ የሆኑ ሰልጣኞችን አስመርቋል፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚህ ወቅት የዛሬው ትውልድ ለነገው ትውልድ ስንቅ ለማስቀመጥ ከፍተኛ ስራ እንደሚጠበቅ ገልጸው÷ ይህን እውን ለማድረግ ጠንካራ የስራ ባህል ያስፈልጋል ብለዋል። በዚህም የቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎችን ችግር ፈቺ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል። ከተማ አስተዳደሩ አዳዲስ የፈጠራ ስራ ያላቸውን ወጣቶች ለማበረታታት ከፍተኛ በጀት መድቦ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። ኮሪደርን ጨምሮ በከተማ አስተዳደሩ የልማት ስራዎች የቴክኒክና ሙያ የስራ ውጤት የሆኑ ግብዓቶች በከፍተኛ ሁኔታ አገልግሎት ላይ መዋላቸውንም ገልጸዋል። ከትምህርት በተጨማሪ በስራ ዓለም ሙያቸውን በማሳደግ ከሀገር ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን መትጋትና መስራት ይኖርባችኋል ሲሉም ለተመራቂዎች መልዕክት አስተላልፈዋል። ከተማ አስተዳደሩ ጥራትን ለማሳደግና ዘርፉን ይበልጥ ወደፊት ለማሻገር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ስለመሆኑም አንስተዋል።

መስከረም 09/2018ዓ/ም በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፀድቆ በመጣው የአሰልጣኞች የዝዉዉርና ምደባ አፈጻጸም ደንብ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተሰጠ ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሙሉ ፀድቆ የመጣው የአሰልጣኞች የዝዉዉርና ምደባ አፈጻጸም ደንብ ላይ ለኮሌጁ አሰልጣኞች እና ለሚመለከታቸው አካላት በድልድል ኮሚቶው የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጠ። በመድረኩም የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብድልበር መሀመድ እንደተናገሩት በደንቡ ላይ ተጨማሪ ግንዛቤ ለመፍጠር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አስረድተው ከመድረክ ለቀረበው ጥያቄ በደንቡ መሠረት ማብራሪያ ተሰጥቶበታል። ኮሚኒኬሽን ቡድን።