1 148
مشترکین
-124 ساعت
-27 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
1 148
29/01/18 ዓ/ም
የአለም ባንክ እና የስራና ክህሎት ሚኒስቴር የልኡካን ቡድን በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ease project የስራ ሂደትን ገምግሟል።
ጉብኝቱ የጀመረው በጊቢው የኢዝ /EASE ፕሮጀክት ቢሮ እና የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ቢሮ ከጎበኙ በኋላ ሲሆን ቡድኑ በኮንፈረንስ አዳራሽ በነበረው ቆይታም በእንኳን ደህና መጣችሁ ውይይቱን የጀመሩት የኮሌጅ ዲን አቶ አብዱልበር መሀመድ በመቀጠልም በቴክኒክና ሙያ ትምህርት አሰጣጥ ከ100 ዓመታት በላይ ልምድ ያለው የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ወጣቶችን፣ ሴቶችን እና አካል ጉዳተኞችን ባሳተፈና በገበያ ተኮር ስልጠናዎችን በማብቃት ወሳኝ ሚና መጫወቱን ቀጥሏል በማለት አንስተው ኮሌጁ ከሀገር አቀፍ እና ከአለምአቀፍ አጋሮች ጋር በቅርበት በመተባበር የኢንዱስትሪ ትስስርን ለማጠናከር፣የስራ እድልን ለማሻሻል እና በ EASE ፕሮጀክት ስር ፈጠራን ለማስተዋወቅ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጦ እንደሚቀጥል ጠቅሰው ፕሮጀክቱ ለኮሌጁ ያመጣውን አዎንታዊ ተፅእኖ ስኬቶችን፣ ተግዳሮቶችን እና የወደፊት እቅዶችን በማሳየት ገለፃ አድርገዋል በመቀጠልም በኮሌጁ የ EASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ወ/ሪት ቤተልሄም አሰፋ ስለ ፕሮጀክቱ የባለፈው አንድ አመት ጉዞ ለቡድኑ ካብራሩ በኋላ ቡድኑ አይሲቲ እና ኤስቴቲክ ዲፓርትመንቶች ተዘዋውረዋል ።
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 148
28/01/2018 ዓ.ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስልጠና አካዳሚክ ጉዳዮች ስራ ክፍል የ1 ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ከስልጠና ዘርፎች እና ከስራ ክፍሎች ጋር ግምገማ ተካሄደ!!!
በቀጣይም 2018 አዲስ ሰልጣኝ ቅበላ አስመልክቶ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንዲደረግና ሁሉም አዲስ ሰልጣኝ የE-Lmis ምዝገበ አድርጎ የPsychometric test
ተመዝነው ሲያጠናቅቁ ብቻ ምዝገባ እንዲደረግና ቀጣይ የስራ አቅጣጫ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል!!!
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 148
መስከረም 26/2018 ዓ/ም
የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሰባተኛ ቀን ተካሄደ።በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት አቶ አላዬ ውጭዬ በየነ እድል ስለተሰጣቸው አመስግነው የተወለዱት አዲስ አበባ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ሀያ ሶስት ቀበሌ እንደሆነና አንደኛ ደረጃ ትምህርት በቁስቋም ጣይቱ ቡጡል አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃ የካቲት12 ት/ቤት እንደጨረሱና ድግሪያቸውን በሂሳብ መዝገብ አያያዝ ከተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣ የመጀመሪያ ድግሪ ከሬፍት ቫሊ ዩንቨርስቲ ኮሌጅ አግኝተዋል።የስራ ልምዳቸውን በንግድ ሰራ ፣ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 በአስተዳደር ወጣቶችና እስፖርት ጸ/ቤት ሀላፊ፣ብሎም ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚነት ፣የጥቃቅንና አነስተኛ ጸ/ቤት ሀላፊ ፣ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 በኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ በመሆን በአጠቃላይ 8 አመት በአስተዳደር ነት ያገለገሉ መሆናቸውን ገልፀው በመሀል የነበሩ ብዙ ተግዳሮቶች እንደተወጡ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ተሞክሮአቸውን አካፍለዋል።በአሁኑ ሰአት በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የህንፃ አስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊ እንደሆኑ እና በኮሚቴነት ብዙ ዘርፎች ላይ እንደሰሩና በአብይነት በቢፒአር ኮሚቴ ገልጸዋል ። መውጣትና መውረድ በህይወት ውስጥ በሚል ርእሰ ጉዳይ ላይ የራቸውን የሂወት ተሞክሮ አካፍለዋል ከመድረክ ለመጣላቸው አስተያየት ማብራሪያ ሰጥተዋል ።
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 148
መስከረም 26/2018 ዓ/ም
የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሰባተኛ ቀን ተካሄደ።በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት አቶ አላዬ ውጭዬ በየነ እድል ስለተሰጣቸው አመስግነው የተወለዱት አዲስ አበባ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ሀያ ሶስት ቀበሌ እንደሆነና አንደኛ ደረጃ ትምህርት በቁስቋም ጣይቱ ቡጡል አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃ የካቲት12 ት/ቤት እንደጨረሱና ድግሪያቸውን በሂሳብ መዝገብ አያያዝ ከተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣ የመጀመሪያ ድግሪ ከሬፍት ቫሊ ዩንቨርስቲ ኮሌጅ አግኝተዋል።የስራ ልምዳቸውን በንግድ ሰራ ፣ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 በአስተዳደር ወጣቶችና እስፖርት ጸ/ቤት ሀላፊ፣ብሎም ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚነት ፣የጥቃቅንና አነስተኛ ጸ/ቤት ሀላፊ ፣ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 በኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ በመሆን በአጠቃላይ 8 አመት በአስተዳደር ነት ያገለገሉ መሆናቸውን ገልፀው በመሀል የነበሩ ብዙ ተግዳሮቶች እንደተወጡ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ተሞክሮአቸውን አካፍለዋል።በአሁኑ ሰአት በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የህንፃ አስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊ እንደሆኑ እና በኮሚቴነት ብዙ ዘርፎች ላይ እንደሰሩና በአብይነት በቢፒአር ኮሚቴ ገልጸዋል ። መውጣትና መውረድ በህይወት ውስጥ በሚል ርእሰ ጉዳይ ላይ የራቸውን የሂወት ተሞክሮ አካፍለዋል ከመድረክ ለመጣላቸው አስተያየት ማብራሪያ ሰጥተዋል ።
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
