1 149
مشترکین
-124 ساعت
-47 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
1 149
ለተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ባልደረቦች፣ በተለይም ለቴክኖሎጂስቶች፣ ለኳስ ተጫዋቾች እና ለቮሊቦል ቡድን ሻምፒዮናዎች፡-
የ16ኛው ክልላዊ የቴክኒክና ሙያ (TVET) ሳምንት በታላቅ ስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ ይህ ስኬት እውን እንዲሆን ላደረጋችሁት ሁሉ ላቅ ያለ ምስጋና እናቀርባለን። ይህ ድል የቴክኒክ ብቃታችንን እና የአሸናፊነት መንፈሳችንን ለአለም ያሳየበት አጋጣሚ ነው።
🏆 ለሻምፒዮናዎቻችን (የእግር ኳስ እና የቮሊቦል ቡድኖች)
በሜዳው ላይ ያሳያችሁት ብቃት እና ያመጣችሁት ድል ለኮሌጃችን ኩራት ሆኖናል።
ለእግር ኳስ ቡድናችን፦ ስለ ነበረችሁ የቡድን ስራ፣ ጽናት እና ኮሌጃችንን በክብር ስላስጠራችሁ እናመሰግናለን።
ለቮሊቦል ቡድናችን፦ ላሳያችሁት ቅልጥፍና እና "ተሸናፊነትን ላለመቀበል" የነበራችሁ ቁርጠኝነት ለሁላችንም አርአያ ሆኗል።
ውጤቱ፦ ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የፈጠራ ሰዎች ብቻ ሳይሆን የአሸናፊ ስፖርተኞችም መፍለቂያ መሆኑን ለክልሉ አስመስክራችኋል።
🛠️ ለቴክኖሎጂስቶች እና ለመላው ሰራተኞች
አትሌቶቻችን በሜዳ ላይ ድል ሲቀዳጁ፣ እናንተ ደግሞ ከበስተጀርባ ለሳምንቱ ስኬት ሞተር ሆናችሁ አገልግላችኋል።
የቴክኒክ ብቃት፦ በኤግዚቢሽኑ ወቅት የኮሌጃችንን የፈጠራ ስራዎች በሚገባ በማቅረብ እና በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያለንን አቅም በማሳየታችሁ ትልቅ ክብር ይገባችኋል።
የድጋፍ ስራዎች፦ መደበኛ ስራችሁን ከአሰልጣኝነት እና ከቡድን ድጋፍ ስራ ጋር አስተባብራችሁ በመስራት ለተገኘው ውጤት መሰረት ሆናችኋል።
ማጠቃለያ
16ኛው የክልል የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ለኮሌጃችን የታሪክ ምዕራፍ ሆኖ ይኖራል። በቮሊቦል እና እግር ኳስ ጨዋታ ሜዳው ላይ ካሳያችሁት ድንቅ እንቅስቃሴ ጀምሮ በቴክኒክ አውደ-ርዕዩ ላይ እስከቀረቡት የፈጠራ ስራዎች ድረስ፣ ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በክህሎትም ሆነ በስፖርታዊ መንፈስ ቀዳሚ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጣችኋል።
እንኳን ደስ አላችሁ! ለሁላችሁም ምስጋና ይግባችሁ!
"አንድ ላይ መሆን ጅምር ነው፤ አብሮ መቀጠል እድገት ነው፤ አብሮ መስራት ግን ስኬት ነው።" — ኤድዋርድ ኤቨረት ሄል
1 149
የ16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንትን ምክንያት በማድረግ የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የፈጠራ ጥበብ በፋሽን መድረክ ደመቀ ።
🇪🇹27/08/2018 ዓ.ም🇪🇹
በኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ስም ያለው ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ16ኛውን የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እያከበረ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል የኮሌጁን ሰልጣኞች ክህሎትና የፈጠራ አቅም ለታዳሚው ያሳየውና በጋርመንትና ቴክስታይል ዘርፍ የተዘጋጀው የፋሽን ሾው የዕለቱ ልዩ ትኩረት ሆኖ ውሏል።
በዚሁ የፋሽን ትይንት ላይ የቀረቡት አልባሳት በሙሉ በጋርመንትና ቴክስታይል የስልጠና ዘርፍ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች ጥምረት የተሰሩ ሲሆኑ፣ የወቅቱን የፋሽን አዝማሚያ ከሀገር በቀል ጥበብ ጋር ያዋሃዱ ስራዎች ለዕይታ ቀርበዋል። ሰልጣኞቹ በክፍል ውስጥ የቀሰሙትን የንድፍ እና የልብስ ስፌት ጥበብ በተግባር በማሳየት፣ የዘርፉን የወደፊት ተስፋ ለታዳሚው አስመስክረዋል።
በሙያው ሰልጣኞች የቀረበው የፋሽን ሾው በኮሌጁ ማህበረሰብና በክብር እንግዶች ፊት በታላቅ ድምቀት የቀረበ ሲሆን፣ አልባሳቱን የዘርፉ ሰልጣኞች ራሳቸው በመድረክ ላይ ተላብሰዋቸው ትይንቱን አቅርበዋል። ይህም ሰልጣኞቹ ልብሶቹን ከመስፋት ባለፈ፣ ለገበያ እንዴት ማቅረብና ማስተዋወቅ እንደሚችሉ ያላቸውን በራስ መተማመን ያሳዩበት መድረክ ሆኗል።
ይህ የፋሽን ሾው ኮሌጁ በጋርመንትና ቴክስታይል ዘርፍ የሚያሰለጥናቸው ወጣቶች የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መመለስ የሚችሉ፣ የፈጠራ ባለቤትና ተወዳዳሪ መሆናቸውን ያረጋገጠ ነው። የቴክኒክና ሙያ ሳምንቱ በኮሌጁ ውስጥ የሚከናወኑ የፈጠራ ስራዎችና የቴክኖሎጂ ሽግግሮች ለህዝብ እይታ የሚቀርቡበት ሲሆን፣ የፋሽን ትይንቱም የዚሁ ትልቅ ዓላማ አካል ነው።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በአራዳ ፓርክ ዛሬ በድምቀት የ16ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዓውደ-ርዕይ ተከፍቷል።
🇪🇹26/08/2018 ዓ.ም🇪🇹
“የቴክኖሎጂ ልህቀት ለሀገር ብልጽግና!” የሚል መሪ ቃል የተካሄደው ዓውደ-ርዕይ ለተከታታይ ሦስት ቀናት ይቆያል።
ዓውደ-ርዕዩ እንደተገለፀው ከተማዊ የቴክኒክና ሙያ ክህሎትን በተግባር የሚያሳይ መድረክ ሲሆን፣ በተለይም የሚሰሩ እጆችና የሚፈጥሩ አዕምሮዎች በሀገር ግንባታ ያላቸውን ሚና ጎልቶ አሳይቷል። በመድረኩ ላይ የተቀረቡ ስራዎች በቴክኖሎጂ ፈጠራ፣ በምርት ተኪ ልማት እና በአገር ውስጥ አምራችነት ላይ እየተመዘገቡ ያሉ እድገቶችን አብራርተዋል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመክፈቻ ሥነ-ስርዓቱ ተገኝተው እንደገለፁት፣ በከተማዋ ፈጣን እድገት ውስጥ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ሲሆን፣ ተቋማቱ በቀጣይም ውጤታቸውን እንዲያሰፉ ጥሪ አቅርበዋል። እንዲሁም የተሻለ የሥራ ባህል ማስፈንጠር፣ ፈጠራን ማጠናከር እና የሀገሪቱን የልማት ፍላጎት የሚመጥኑ ባለሙያዎችን ማፍራት ላይ እንዲጠናከር አሳስበዋል።
በተጨማሪም ከተማ አስተዳደሩ ለቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደማያቋርጥ አረጋግጧል። በዓውደ-ርዕዩ ላይ በተለያዩ ኮሌጆች የተዘጋጁ ፈጠራ ስራዎች ቀርበው እየታዩ ሲሆን፣ ተፈሪ መኮንን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኮሌጁ ማህበረሰብ የተሰሩ ልዩ ልዩ ስራዎችን በመቅረብ ተሳትፎ አድርጓል።
በመጨረሻም ዓውደ-ርዕዩን በቅንጅት ለዘጋጁ የሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች፣ አሰልጣኞች፣ ሰራተኞችና ሰልጣኞች ከፍተኛ ምስጋና ተገልጿል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
👋ሰላም የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ፣ አስተባባሪዎች እና የስራ ክፍል ዳይሬክቶሬቶች👋
❗️ ሰኞ በአዲሱ አራዳ ፓርክ በሚጀመረው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ላይ እንድንገኝ የስራ እና ክህሎት ቢሮ ትዕዛዝ አስተላልፏል❗️
በመሆኑም:-
👉 በስልጠና ዘርፎች ስር የሚገኙ ሁሉንም አሰልጣኞች እና በየዘርፋችሁ ስር የሚገኙ ሰልጣኞችን በማስተባበር ወደተዘጋጀው መኪና በጠዋት እንድታስገቡ ይሁን።
👉 ዳይሬክቶሬቶች በስራችሁ የሚገኙትን ሰራተኞች በሙሉ በማስተባበር ወደተዘጋጀው መኪና እንድታስገቡ ይሁን።
ማሳሰቢያ!
የመክፈቻ መርሀ ግብሩ የሚጀመረው በጠዋት 2:30 ስለሆነ ከዛ ቀድመን ኮሌጁ ግቢ እንድንገናኝ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን።
1 149
+4
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የደጃቻ ዉቤ አቻዉን በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ተሻገረ
መያዚያ 24/2018 ዓ.ም
ዛሬ በተካሄደው የእግር ኳስ የጥሎ ማለፍ ውድድር የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የእግር ኳስ ቡድን የደጃቻ ዉቤ አቻውን በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፉን አረጋግጧል።
በሁለቱ ቡድኖች መካከል የተደረገው ጨዋታ በከፍተኛ ፉክክር የታጀበና በስፖርታዊ ጨዋነት የተሞላ ነበር።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስፖርተኞች ከመጀመሪያው ደቂቃ ጀምሮ ባሳዩት ብልጫና የተቀናጀ የቡድን ስራ ተቀናቃኛቸውን በማሸነፍ አመርቂ ውጤት ሊያስመዘግቡ ችለዋል።
ቡድኑ ያስመዘገበው ይህ ድል ወደ ቀጣዩ ዙር እንዲሸጋገር ከማድረጉም ባለፈ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ትልቅ ደስታን የፈጠረ ሆኖ አልፏል።
በቀጣይ ለሚደረጉት ወሳኝ ግጥሚያዎችም ቡድኑ ዝግጅቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ይህ ውጤት ኮሌጁ በትምህርትና ስልጠናው ዘርፍ ከሚያስመዘግባቸው ስኬቶች ጎን ለጎን በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችም ውጤታማነቱን እያሳየ መሆኑን ማሳያ ነው ተብሏል።
1 149
Repost from N/a
የኢንዱስትሪ አብዮትና የሰው ልጅ ወደ ማሽንነት የተቀየረበት ጥቁር ዘመን።
ከ140 ዓመታት በፊት የተከሰተው የኢንዱስትሪ አብዮት ለዓለም አዲስ የቴክኖሎጂ ብርሃን ይዞ የመጣ ቢመስልም፣ በስተጀርባው ግን በታሪክ የማይረሳ ሰብዓዊ ስቃይን አዝሎ ነበር።
በወቅቱ የነበረው የካፒታሊዝም ሥርዓት ሰራተኛውን እንደ ሰው ሳይሆን እንደ አንዱ የፋብሪካ ማሽን ይቆጥረው ነበር። ሠራተኞች ከማለዳው 11 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 4 ሰዓት ድረስ ለ16 ሰዓታት ያለ እረፍት እንዲሠሩ ይገደዱ ነበር።
በተለይም ሕፃናት በትምህርት ገበታ ፋንታ በፋብሪካ ጭስ ውስጥ እንዲታፈኑ መደረጋቸውና እናቶች ያለምንም የወሊድ ፈቃድ በቆሙበት እንዲወልዱ መገደዳቸው የዘመኑን እጅግ አሰቃቂ ገጽታ ያሳያል። ይህ "ጥቁር ህልም" የሰው ልጅ ሰብዓዊነት ክብር የወደቀበትና ጉልበት በግፍ የሚበዘበዝበት ወቅት ነበር።
የቺካጎው ትግልና የመብት ማስከበር መስዋዕትነት
ይህ መጠነ ሰፊ ግፍና በደል የወለደው መራራ ትግል በ1886 (እ.ኤ.አ) በቺካጎ ከተማ ፈነዳ። ሠራተኞች "እኛ ማሽን አይደለንም፣ ሰው ነን!" በሚል ጽኑ ድምፅ አደባባይ ወጡ። "8 ሰዓት ለሥራ፣ 8 ሰዓት ለዕረፍት፣ 8 ሰዓት ለእንቅልፍ" የሚለው ታሪካዊ ጥያቄ የዛሬው ዓለም አቀፍ የሥራ መመሪያ መሠረት ነው። ይሁን እንጂ ይህ ጥያቄ በቀላሉ አልተመለሰም፤ የሠራተኞች ደም ፈሷል፣ በጠመንጃ ጥይት ተቆልተዋል፣ ብዙዎችም በአደባባይ ተሰቅለዋል።
ዛሬ የምናገኘው የሳምንት ዕረፍት፣ የወሊድ ፈቃድ፣ የትርፍ ሰዓት ክፍያና የሥራ ቦታ ደህንነት መብቶች በሙሉ በነዚያ ጀግኖች ደምና አጥንት የተገነቡ እንጂ በነፃ የተገኙ ስጦታዎች አይደሉም።
የስራና ክህሎት ቢሮ ተልዕኮ፦ ሰብዓዊነትን የተላበሰ የስራ አካባቢ
በኢትዮጵያም ሆነ በከተማችን አዲስ አበባ፣ የሥራና ክህሎት ቢሮ የተቋቋመው እነዚህን በደም የመጡ የሠራተኛ መብቶችን ለማስከበርና ለዜጎች ምቹ የሥራ ሁኔታን ለመፍጠር ነው።
የቢሮው ተልዕኮ ዜጎች በክህሎት የበለፀጉና በሥራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ማብቃት ብቻ ሳይሆን፣ የሠራተኛውና የአሠሪው ግንኙነት በሕግና በሥርዓት እንዲመራ ማድረግ ነው። ቢሮው የሥራ ቦታ ደህንነትን በማረጋገጥ፣ ተገቢውን የሥራ ሰዓትና ክፍያ በመከታተል፣ እንዲሁም የኢንዱስትሪ ሰላምን በማስፈን የሠራተኛውን ሰብዓዊ ክብር የመጠበቅ ታሪካዊ አደራ አለበት። ይህም ትላንት በቺካጎ የተጀመረውን የፍትህ ትግል በዘመናዊና በተቋማዊ መንገድ የማስቀጠል ሥራ ነው።
የክህሎት ልማት ለተሟላ የሠራተኛ ክብር
በዛሬው ዘመን የሠራተኛው ቀን ሲከበር ከመብት ጥያቄ ባሻገር "ክህሎትን" ማሳደግ የክብር መገለጫ ሆኗል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ዜጎችን በቴክኒክና ሙያ በማሰልጠንና ብቁ በማድረግ፣ ሠራተኛው በጉልበቱ ብቻ ሳይሆን በዕውቀቱና በቴክኖሎጂ ታግዞ ራሱንና ሀገሩን እንዲለውጥ እየሠራ ይገኛል።
ሚያዝያ 23 ስናከብር፣ በትላንትናው መስዋዕትነት የተገኘውን መብት እያከበርን፣ በዛሬው የክህሎት ልማት ደግሞ የሠራተኛውን ተወዳዳሪነትና ምርታማነት ለማረጋገጥ ቃል የምንገባበት ቀን ነው። የሠራተኛው ክብር የሚጠበቀው መብቱ ሲከበርና ለሥራው የሚመጥን ዕውቀትና ጥበብ ሲታጠቅ ብቻ በመሆኑ፣ ቢሮው ይህንን የተቀደሰ ዓላማ ከግብ ለማድረስ ሌት ተቀን ይተጋል።
ለሀገር ሰራተኞች በሙሉ ክብር ይገባችኋል!
መልካም የሰራተኞች ቀን!
🇪🇹 ሚያዝያ 23/2018 ዓ.ም 🇪🇹
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://aabols.gov.et/qr.html
1 149
👋ሰላም የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ፣ አስተባባሪዎች እና የስራ ክፍል ዳይሬክቶሬቶች👋
❗️ ሰኞ በአዲሱ አራዳ ፓርክ በሚጀመረው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ላይ እንድንገኝ የስራ እና ክህሎት ቢሮ ትዕዛዝ አስተላልፏል❗️
በመሆኑም:-
👉 በስልጠና ዘርፎች ስር የሚገኙ ሁሉንም አሰልጣኞች እና በየዘርፋችሁ ስር የሚገኙ ሰልጣኞችን በማስተባበር ወደተዘጋጀው መኪና በጠዋት እንድታስገቡ ይሁን።
👉 ዳይሬክቶሬቶች በስራችሁ የሚገኙትን ሰራተኞች በሙሉ በማስተባበር ወደተዘጋጀው መኪና እንድታስገቡ ይሁን።
ማሳሰቢያ!
የመክፈቻ መርሀ ግብሩ የሚጀመረው በጠዋት 2:30 ስለሆነ ከዛ ቀድመን ኮሌጁ ግቢ እንድንገናኝ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን።
1 149
Repost from Addis Admass
+1
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ የ100 ዓመት
ክብሩን በአለም አቀፍ እውቅና አደመቀ
ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ትምህርት ፋና ወጊ የሆነውና "የአፍሪካው ሃርቫርድ" በመባል የሚታወቀው ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ "መቶ ዓመት ታሪክ፣ መቶ ዓመት ክብር!" በሚል መሪ ቃል የመቶኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በታላቅ ድምቀት አጠናቋል። ለዘመናት "እንጦጦ" በሚል ስያሜ ተቀይሮ የቆየውን ታሪካዊ ማንነቱን በይፋ ያስመለሰው ተቋሙ፣ የቀድሞ ተማሪዎች፣ የመንግስት ባለስልጣናትና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት በኪነ-ጥበብና በቴክኖሎጂ ኤግዚቢሽን የታጀበ ደማቅ መርሃ-ግብር አከናውኗል።
ይህ ታሪካዊ በዓል የክብር ብቻ ሳይሆን የጥራት ሽግግር የታየበት ነበር፤ ኮሌጁ የትምህርት አሰጣጡን ደረጃውን የጠበቀ በማድረጉ የ ISO 21001:2018 ዓለም አቀፍ የምስክር ወረቀት በይፋ ተረክቧል። የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ እንደገለጹት፣ ተቋሙ ካለበት ታላቅ ታሪክ ተነስቶ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የልህቀት ማዕከል (Center of Excellence) ለመሆን አዲስ የቴክኖሎጂና የብልጽግና ምዕራፍ መጀመሩን አብስረዋል።
ተፈሪ መኮንን ባለፉት መቶ ዓመታት እንደነ ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ፣ ጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተ-ወልድ፣ ክቡር ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ እና ሎሬት አፈወርቅ ተክሌ ያሉ የአገሪቱን የፖለቲካ፣ የጥበብና የሳይንስ ምሰሶዎችን ያፈራ አንጋፋ ተቋም ነው። ይህ የመቶኛ ዓመት በዓል፣ ተቋሙ የተነጠቀውን ስምና ዝና በማስመለስ ለቀጣዩ መቶ ክፍለ ዘመን አዲስ ጉዞ የጀመረበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሆኖ ተመዝግቧል።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
