የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን Addis Ababa City Administration Environmental protection Authority(official)
رفتن به کانال در Telegram
Addis Ababa City Administration Environmental protection Authority የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ በለስልጣን
نمایش بیشتر773
مشترکین
+124 ساعت
+27 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ ሰይፈ ደርቤ ''የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ'' በተሰኘው ሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ እንዳቀረቡት የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከምስረታው ባልተናነሰ የለውጡ መንግሥት በዘረፉና በተቋሙ ባደረገው ሪፎርም ምክንያት ዳግም ተወልዷል ማለት እንደሚቻል ገልጸዋል።
የተከናወነው የእሳቤ፣ የህግና አደረጃጀት እንዲሁም የአሰራር ሪፎርም፤ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን በአፍሪካ አስተማማኝና ተጽዕኖ ፈጣሪ የዜና ምንጭ በመሆን ብሄራዊ ጥቅምን ማስጠበቅና ብሄራዊ መግባባት መፍጠር የሚያስችል አቅም እንዲላበስ አስችሎታል። ተቋሙ ተደራሽነቱን በማስፋት፣ በቴክኖሎጂ ተደራጅቶ፣ ከኢትዮጵያ ተሻግሮ የአፍሪካ ድምጽ በመሆን የወል ትርክትን እየገነባ ይገኛል።
#PMOEthiopia
አሁን በመካሄድ ላይ!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት "የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ" በሚል መሪ ቃል ሀገራዊ የምክክር መድረክ መካሄድ ጀምሯል።
ኢትዮጵያ ካስመዘገበቻቸው የለውጥ ድሎች አንዱ ተቋማት ጠንካራና ትክክለኛ የዴሞክራሲ ስርዓት መገለጫ እንዲሆኑ ማድረግ ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል የመገናኛ ብዙሃን ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ናቸው።
#PMOEthiopia
የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉብኝት በአዲስ አበባ
የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ የሚያደርጉትን ጉብኝት ጀምረዋል።
የአፍሪካን እውነተኛ ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅና የዲጂታል ትርክቱን በባለቤትነት ለመምራት ያለመው የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS 2026) በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ዛሬ እና ነገ ይካሄዳል።
በጉባኤው ለመታደም ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 321 ሚሊዮን በላይ የማህበራዊ ሚዲያ ተከታዮች ያሏቸው 61 ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በአዲስ አበባ ከትመዋል።
በተጨማሪም 150 ሚሊዮን ተከታዮች ያላቸው 120 ኢትዮጵያውያን የይዘት ፈጣሪዎች በጋራ በመሰባሰብ፣ የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ አዲስ የዲጂታል ታሪክ ለመጻፍ ተዘጋጅተዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የጉባኤው አካል የሆነውን ጉብኝት የጀመሩ ሲሆን፤ አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲናነቷን የሚያጎሉ ድምቀቶቿን ታስጎበኛለች።
አፍሪካውያን የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ፈጣሪዎች በአዲስ አበባ
አፍሪካውያን የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ፈጣሪዎች የአህጉሪቷን ትክክለኛ ገጽታ ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ እንደ አምባሳደር እያገለገሉ ይገኛሉ።
የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ በፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ትብብር በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ነገ እና ከነገ በስቲያ ይካሄዳል።
"ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ" በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ የአህጉሪቱ የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ፈጣሪዎች አዲስ አበባ ገብተዋል።
የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ዳያስፖራዎችና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች የረጅም ጊዜ ትብብር የሚፈጥሩበት ይህ መድረክ የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ትክክለኛ ትርክት ለዓለም ለማስተዋወቅ ወሳኝ ነው።
ታዋቂው የአፍሪካዊ ዲጂታል ታሪክ ተራኪ ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) ጨምሮ የአህጉሪቷ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ መግባት ጀምረዋል።
ጋናዊው በርትሆልድ ኮቢ ዊንክለር አክኮን (ዎዴ ማያ) እንዳለው፤ የአፍሪካን የይዘት ፈጠራ ባለሙያዎች በአንድ መድረክ በተለይም በአዲስ አበባ ማግኘት እጅግ የሚያስደስት ነው፡፡
የይዘት ፈጣሪዎቹ በአንድ አዳራሽ ተገኝተው የአፍሪካን አጀንዳ ለቀሪው ዓለም ለማድረስ የሚያደርጉት ምክክር ትልቅ ፋይዳ እንዳለው መግለጹን ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ዘግቧል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት፡-
ከኔዘርላንድስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮብ ጄተን ጋር ውጤታማ የሥልክ ውይይት አድርገናል።
በውይይታችን የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ የመከርን ሲሆን፣ በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚያስችሉ መንገዶች ላይ ሃሳብ ተለዋውጠዋል።
"ጥበብ ሀገርን ትሰራለች፤ሀገርም ጠቢብን ታስታውሳለች"
አዲስ አበባ ለሕፃናት ተመራጭ መዲና ለመሆን የጀመረችው ጉዞ ስኬት እያሳየ መምጣቱ ተገለፀ።
********************************
አዲስ አበባን ለሕፃናት እድገትና አስተዳደግ ምቹና ተመራጭ የአፍሪካ ከተማ ለማድረግ የተወጠነው “የቀዳማይ ልጅነት ዕድገት ፕሮግራም” አስገራሚ ውጤቶችን እያስመዘገበ መሆኑ ተገለጸ።
ከተማዋ የነገ አገር ተረካቢ ትውልድን ለመቅረጽ የጀመረችው ይህ ታላቅ ፕሮጀክት፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተለይም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎችን ማዕከል በማድረግ 1.3 ሚሊዮን ሕፃናትን እና 330 ሺህ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ወላጆችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ አምስት ዋና ዋና የንቅናቄ ዘርፎችን (Initiatives) ተግባራዊ እያደረገች ትገኛለች።
በፕሮግራሙ መጀመሪያ ላይ በከተማዋ የነበሩት የሕፃናት መጫወቻ ስፍራዎች 11 ብቻ የነበሩ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ሰፊ የንቅናቄ ስራ ተሰርቶ ቁጥራቸው ወደ 4,429 ከፍ እንዲል ተደርጓል ተብሏል። ይህም ሕፃናት በየሰፈራቸው በቂ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚያደርጉባቸውና የሚጫወቱባቸው ስፍራዎች እንዲኖሩ በማድረግ ረገድ ትልቅ ለውጥ ያመጣ መሆኑ ተመልክቷል።
ፕሮግራሙን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ከማድረግ በተጨማሪ ዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር የሕፃናትን የአእምሮና የአካል ዕድገት በሚያፋጥን መልኩ ደረጃቸውን የጠበቁ ማዕከላት እንዲስፋፉ እየተደረገ ነዉ።
ይህ ስራ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የነገ አገር ተረካቢ ዜጎችን በአእምሮና በአካል ብቁ አድርጎ ለማሳደግ የሚደረግ ትልቅ የትውልድ ግንባታ ኢንቨስትመንት መሆኑን የከተማዋ አስተዳደሩ በተደጋጋሚ ሲገልፅ ይስተዋላል፡፡
በአጠቃላይ አዲስ አበባ ለሕፃናት ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየች ሲሆን፣ ፕሮግራሙ በተያዘለት ፍጥነት ከተቀጠለ መዲናዋ በቅርቡ በአፍሪካ ለሕፃናት ምቹ የሆኑ ከተሞች ተርታ ቀዳሚዋ እንደምትሆን የሚደረጉ ጥረቶች ያሳያሉ።
በመዲናዋ ለ5 ቀናት ሲካሄድ የቆየው የልማት ስራዎች የፎቶ አውደ-ርዕይ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተጠናቋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ አዘጋጅነት "የእርጅና ገፅታን የገፈፈ ፤የውበት ፀዳል ያላበሰ" በሚል መሪ ቃል ባለፉት አምስት አመታት በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ለህዝብ ሲያስተዋውቅ የቆየው የፎቶ አውደ-ርዕይ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
ከመጋቢት 23 ቀን ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት ክፍት ሆኖ የቆየው ይህ አውደ-ርዕይ የከተማዋን ሁለገብ ለውጥ የሚያሳዩ በርካታ ምስሎች ለአንባቢያንና ለተመልካች እንዲቀርቡ የተደረገበት ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሃፍታይ ገብረእግዚአብሔር እንደገለፁት አውደ ርዕዬ ከለውጡ ወዲህ ባሉት አምስት ዓመታት መንግስት ለህዝብ የገባውን ቃል በተግባር መፈጸሙን፣የተመዘገቡ የልማት ውጤቶችንና የከተማዋን ጉዞ በተጨባጭ ለማሳየት ያለመ እንደነበር ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ በመንግስትና በህዝብ መካከል ጠንካራ የኮሙኒኬሽን ሥርዓት በመዘርጋት በቂ መረጃ ያለውና በልማት ስራዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርግ ማህበረሰብ ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝም አቶ ሃፍታይ ገብረእግዚአብሔር አክለዉ ገልፀዋል።
አውደ ርዕዩ በመዲናዋ የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ ሲሆን ጎብኚዎች በመዲናዋ የታዩትን የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ፣ የሰው ተኮር ስራዎችንና የከተማ ውበት ስራዎችን በፎቶ አውደ-ርዕይ ሲመለከቱ መሰንበታቸው ተገልፃል።
በማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸዉ አዲስ አበባ እውነትም በየጊዜው አዲስ ለውጥ እና ፈጣን እድገት የሚታይባት ከተማ እየሆነች መምጣቷን ተናግረዋል።
በተለይም ልማቱ የከተማዋን ገፅታ ከማሳመር ባለፈ ነዋሪውን ማዕከል ያደረገ ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጠ መሆኑን የፎቶ አውደ-ርዕዬ ተሳታፊዎች ጠቁመዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ የቆሙ የአንጋፋ የኪነጥበብ ባለሙያዎችን የመታሰቢያ እና የክብር ሀውልቶችን መረቁ፡፡
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
