3 661
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
+2330 روز
آرشیو پست ها
ተማሪዎች ፈተና ወረቀት ለመውሰድ ሲመጡ ክሊራንስና መታወቂያ እንዲይዙ፣ እንዲሁም ዩኒፎርም እንዲለብሱ እናሳስባለን ።
ለባሸዋም 2ኛ ደረጃ ተማሪዎች በሙሉ :- የሁለተኛ ሰሚስተር አራተኛ ተርም ማጠቃለያ ፈተና ወረቀት የሚመለሰው ነገ ረቡዕ ሰኔ 17/ 2018 ከ 2:30-6:00 ባለው ጊዜ ብቻ መሆኑን እየገለፅን ሁሉም ተማሪ በተጠቀሰው ጊዜና ሰአት በመማሪያ ክፍሉ በመገኘት የፈተና ወረቀቱን እንዲወስድና ከ100% ያለውን ውጤት እንዲያረጋግጥ በጥብቅ እናሳስባለን ።
ማሳሰቢያ:- ለ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች - ነገ ረቡዕ ሰኔ 17/2018 ከ2:30 ጀምሮ የሙከራ ፈተና ስለሚሰጥ በፈተና መስጫ IT ክፍል እንድትገኙ እናሳስባለን ። (አድሚሽን ካርድ እንዳትረሱ)
Repost from Addis ketema Education 2018
+1
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበት የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆነ።ሰኔ 13/2018ዓ.ም የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞች በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል። ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል። ዝርዝሩን ከሚከተለው ሠንጠረዥ ይመልከቱ። የፈተና ስርቆትንና ኩረጃን በጋራ እንከላከል! #ምንጭ: የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
NOTICE TO GRADE 11 STUDENTS
Dear Students,
This is to inform you that there will be final examinations taking place on Monday, Sené 15, 2018 E.C.
Subjects and Schedule:
• Natural Science: Biology and Agriculture
• Social Science: Economics and Marketing
Please ensure that you are well-prepared for these exams. Review your notes, study materials, and any past papers to help you succeed.
Wishing you all the best in your preparations!
Sincerely
NOTICE TO ALL GRADE 10 STUDENTS
Date: 11/10/2018 E.C
Dear Students,
This is to inform you that the Geography exam will be replaced and readministered. All Grade 10 students are required to prepare for the upcoming Geography exam, which will now take place on Monday, Sene 15, 2018 E.C.
Please ensure that you review all relevant materials thoroughly in preparation for this exam. If you have any questions or need further clarification, do not hesitate to reach out.
Best of luck in your studies!
ACADEMIC OFFICE
Repost from Bashewam Primary & Junior School 1-8
ተማሪ ቤካ ወ/ኪዳን በትናትናው እለት በቀን 04/10/2018 ዓ. ም እጅግ አሳዛኝ በሆነ ክስተት በሞት ተለይቶናል።
ተማሪው በዚህ ዓመት የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልቀቂያ ፈተና (ሚንስትሪ) ለመፈተን ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቆ👉 Orientation ለመዉሰድ በቀጠሮ የተለያየን ቢሆንም በጋጠመዉ ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ህይወቱ አልፋል። ተማሪው በትምህርት ቤት በነበረው ባህሪ ተወዳጅ እና ምስጉን የነበረ ሲሆን በሀገር ደረጃም ተሰፋ የተጣለበት ጎብዝ ብስክሌተኛ ነበር።
የባሽዋም ት/ቤት ማህበረሰብ በዉዱ ተማሪያችን በቤካ ወ/ኪዳን እጅግ አስደንጋጭ እና ድንገተኛ ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ የሃዘን ስሜት እየገለፅን👉 ቸሩ እግዚአብሔር ነብሱን በአፀደ ገነት እድያኖርልንና ለመላው ቤተሰቡ እና ጕደኞቹ መፅናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን።
የመኪና አደጋ ሕይወቱን የቀማው ታዳጊ ብስክሌተኛ!😭
#maleda: በአዲስ አበባ ከተማ የብስክሌት ስፖርት ውስጥ ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት የነበረው ታዳጊው ቤካ ወ/ኪዳን በደረሰበት አሳዛኝ የመኪና አደጋ ሕይወቱ አለፈ።
ታዳጊው ቤካ ወ/ኪዳን ትናንት ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በብስክሌት ላይ እያለ በደረሰበት ከባድ የትራፊክ አደጋ ነው ሕይወቱ ሊያልፍ የቻለው።
የአባቱን ፈለግ በመከተል ወደ ብስክሌት ስፖርት የገባው ቤካ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደረጃ በሚዘጋጁ ልዩ ልዩ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ውጤታማ መሆን የቻለ ስፖርተኛ ነበር።
በዚሁ ዓመት በአዳማ ከተማ በተካሄደው ሀገር አቀፍ የታዳጊዎች የምዘና ውድድር ላይም የከተማ አስተዳደሩን ወክሎ በመሳተፍ ደማቅ አፈጻጸም አሳይቶ ነበር። ይህን ባለ ብዙ ህልም ታዳጊ ብስክሌት እየነዳ ሳለ የትራፊክ አደጋ ገጭቶት ህልሙን እስከወዲያኛው ቀማው ። ልብ ይሰብራል።
ዛሬ ቤካን የቀማን አደጋ ነገ ሌላ ህይወት እንዳይቀማ፣ አሽከርካሪዎች ሆይ በመንገድ ላይ ለባለብስክሌቶችና ለእግረኞች ያለንን አክብሮትና ጥንቃቄ እናሳድግ። በሕይወት ውስጥ ሁለተኛ ዕድል የለምና።የማለዳ ቤተሰቦች በቤካ ድንገተኛ ህልፈት እጅግ አዝነናል።
ለቤተሰቦቹ፣ ለስፖርቱ ማኅበረሰብ እና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛለን።ቤካ ፤ነፍስህን ይማር፣ እግዚአብሔር በገነት ያኑርህ!🙏💔
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
