የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
رفتن به کانال در Telegram
#ሪስቶሬሽን ማለት ማፍረስ ማለት አይደለም ፤ ይልቁን የፈረሰውን መገንባት፣ መልሶ ማቆም ማለት ነው። MEKETE DEBAY TADESSE
نمایش بیشتر862
مشترکین
+224 ساعت
+147 روز
+3530 روز
آرشیو پست ها
በጎችና ፍየሎች
ጻድቃን በበግ ኃጥአን በፍየል ለምን ይመሰላሉ፡፡ ጻድቃን በበግ ኃጥአን በፍየል ለምን ተመሰሉ ቢባል የበጎች ተፈጥሮ ከጻድቃን ሥራ ጋር የፍየል ተፈጥሮ (ግብር) ከኃጥአን ጋራ ስለሚመሳሰል ነው፡፡ በጎች በደጋ እንጂ በቆላ አይኖሩም፡፡ ተስማሚያቸው ደጋ ነው ጻድቃን በመከራ ሥጋ እንጂ በተድላ ደስታ ለመኖር ሲሉ ኃይማኖታቸውን ክደው በምግባር ብልሹነት አይገኙም፡፡ ፍየሎች በቆላ እንጂ በደጋ አይኖሩም፤ ኃጥአንም በተድላ ደስታ ለመኖር ሲሉ ኃይማኖታቸውን በወርቅ በብር ይለውጣሉና፡፡
በጎች እረኛቸው ባሰማራቸው ሥፍራ ጸንተው ይኖራሉ፡፡ ጻድቃንም እረኛቸው ክርስቶስ ባሰማራቸው በአንዲት ኃይማኖት (እምነት) ጸንተው ይኖራሉ፡፡ ፍየሎች እረኛቸው ባሰማራቸው ቦታ ጸንተው እንደማይኖሩ ኃጥአንም እንዲሁ በኃይማኖት ጸንተው መኖር አይቻላቸውምና፡፡ በጎች ጥቂት ሳር ካገኙ ተፋቅረው አብረው ይበላሉ ጻድቃንም ያለቻቸውን ተካፍለው ይኖራሉና፡፡ ፍየሎች ግን ሣር ቅጠሉ ሞልቶ ለሁላቸው ሲበቃ ሳለ ይጣላሉ፡፡ ኃጥአንም ሀብት ንብረት ተትረፍርፎላቸው ለወገናቸው አያካፍሉም፡፡ ለገንዘብ ብለው እርስ በእርሳቸው ይጣላሉ ዘለው የሌላውን ሀብት ንብረት ለማግኘት ሲሉ የማይገባ ሥራ ይሠራሉና፡፡
የበጎች ላታቸው የተከደነ ሐፍረተ ሥጋቸው የተሸፈነ ነው፡፡ የጻድቃንም ኃጢአታቸው በሰው ዘንድ የተጋለጠ አይደለም፡፡ ኃጢአት ቢሰሩ ሌላ ሰው ሳይሰናከልባቸው ንስሐ ይገባሉ፡፡ የፍየሎች ላታቸው የተሰቀለ ሐፍረተ ሥጋቸው የተጋለጠ ነው፡፡ የኃጢአተኞችም ሥራ በሰው ዘንድ የተጋለጠ ለሚሰሩት እኩይ ሥራ የማያፍሩ በየአደባባዩ ኃጢአትን የሚፈጽሙ ናቸውና፡፡ በጎች አቀርቅረው እንጂ አሻቅበው አያዩም ጻድቃንም ሁልጊዜ ዕለተ ሞታቸውን በማሰብ ወደ አፈር እንደሚመለሱ እያሰቡ በትህትና ሕይወታቸውን ይመራሉ፡፡ ሀብት’ ንብረት’ ዕውቀት እያላቸው ራሳቸውን ዝቅ ያደርጋሉ፡፡ ፍየሎች አሻቅበው ነው የሚያዩት አንገታቸውን ያንጠራራሉ ኃጥአንም ደካማ ሆነው ሳሉ ብርቱ ነን ይላሉ ባገኙበት ሀብት ዕውቀት ይመካሉ ትዕቢተኞች ናቸው፡፡ ትሕትና በእነርሱ ዘንድ የበታችነት ምልክት ነው፡፡
ከበጎች ውስጥ አንዲቱ ተኩላ ቢነጥቃት ሁለተኛ ወደዚያ ቦታ ተመልሰው አይመጡም፡፡ ጻድቃንም እኩይ ሞት ከእነርሱ አንዱን ከወሰደ ነገም የእነርሱ ተራ እንደሆነ ተረድተው ከኃጢአት ሥራቸው በንስሐ ይመለሳሉ ወደ እግዚአብሔር ይቀርባሉ፡፡ ፍየሎች ግን ከመካከላቸው ነብር አንዲቱን ቢወስድ ለጊዜው ደንብረው ይሄዳሉ፡፡ ኋላ ግን ተመልሰው እዚያው ቦታ ይመጣሉ ኃጥአንም ከመካከላቸው አንዱ ሳያስቡት በሞት ቢወሰድ ለጊዜው ደንግጠው ከኃጥአት ሥራቸው ይታቀባሉ በኋላ ግን የሞተው ሰው ከህሊናቸው ሲጠፋና የዓለም ሁኔታ ሲማርካቸው ወደ ኃጢአት ግብራቸው ይመለሳሉና፡፡
የመጨረሻው ፍርድ።
ሁሉም እንደየሠራው የሚያገኝበት የመጨረሻው ቀን ፍርድ አለ፡፡ ይህም ከጌታችን ምጽአትና ያንቀላፉት ሁሉ ከተነሱ በኋላ ይከናወናል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹የሚጥለኝ ቃሌንም የማይቀበለው እርሱ የሚፈርድበት አለው፤ እኔ የተናገርሁት ቃል እርሱ በመጨረሻው ቀን ይፈርድበታል›› (ዮሐ 12፡48) በማለት ሰው በመጨረሻው ቀን የሰማው የእግዚአብሔር ቃል እንደሚፈርድበት ተናግሯል፡፡ እንዲሁም ‹‹እኔ እላችኋለሁ፥ ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል›› (ማቴ 12፡36) ብሎ ዛሬ ለምንናገራቸው ከንቱ ነገሮች ሁሉ በዚያ በፍርድ ቀን መልስ የምንሰጥበት ይሆናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ ስለመጨረሻው ቀን ፍርድ ሲናገር ‹‹ሌላ መጽሐፍም ተከፈተ እርሱም የሕይወት መጽሐፍ ነው፤ ሙታንም በመጻሕፍት ተጽፎ እንደ ነበረ እንደ ሥራቸው መጠን ተከፈሉ›› (ራዕ 20፡11-15) በማለት ሁሉም እንደ ሥራው የሚከፈልበት ፍርድ መሆኑን መስክሯል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ሰለዚህ ቀን ‹‹መልካም ቢሆን ወይም ክፉ እንዳደረገ፥ እያንዳንዱ በሥጋው የተሠራውን በብድራት ይቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ በፍርድ ወንበር ፊት ልንገለጥ ይገባናልና›› (2ኛ ቆሮ 5፡10) ብሏል፡፡ እንዲሁም ለአቴና ሰዎች ‹‹ቀን ቀጥሮአልና፥ በዚያም ቀን ባዘጋጀው ሰው እጅ በዓለሙ ላይ በጽድቅ ሊፈርድ አለው፤ ስለዚህም እርሱን ከሙታን በማስነሣቱ ሁሉን አረጋግጦአል›› (ሐዋ 17፡31) በማለት እውነትን መስክሮላቸዋል፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞንም ስለዚች ቀን ‹‹እግዚአብሔር ሥራን ሁሉ የተሰወረውንም ነገር ሁሉ፥ መልካምም ቢሆን ክፉም ቢሆን፥ ወደ ፍርድ ያመጣዋልና›› (መክ 12፡14) ብሏል፡፡ ገነትና ሲኦል ጊዜያዊ የነፍሳት መቆያ ናቸው፡፡
ዘላለማዊ ትንሣኤ
መድኃኔዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቀደመው ለአባታችን ለአዳም በገባው ቃልኪዳን መሠረት፤ በአይሁድ እጅ መከራ መስቀልን ከተቀበለ በኋላ ነፍሱን በራሱ ስልጣን አሳልፎ ሰጠ፡፡ ከዚያም በኋላ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ መስፍኑ ጲላጦስን አስፈቅደው ከመስቀል አውርደው ዮሴፍ ራሱ ባሰራው መቃብር በንጹህ በፍታt ገንዘው ቀበሩት፡፡ ሲሄዱም ጸሐፍት ፈሪሳውያንና መስፍኑ በመቃብሩ ላይ ማኅተማቸውንና ጠባቂዎችን አኖሩ (ማቴ 27÷57-66 ማር 15÷42 ሉቃ 23÷50 ዮሐ 19÷38-42) ፡፡ ጌታቸን በሦስተኛው ቀን እሁድ በእኩለ ሌሊት መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በታላቅ ኃይል ሞትንና መቃብርን አጥፍቶ ተነሣ፡፡ ይጠብቁ የነበሩ ጠባቂዎችም ደንግጠው ተበታተኑ በመቃብሩ ዙሪያ ቅዱሳን መላዕክት ታዩ (ማቴ 28÷1-15 ማር 16÷11-15 ሉቃ 24÷1-43 ዮሐ 20÷1-25 1ኛ ቆሮ 15-1 ሮሜ 6÷9-15)፡፡ ለሰው ልጆች ዘላለማዊ ትንሣኤ በኩር የሆነው የክርስቶስ ትንሣኤ ነው፡፡ በመጨረሻው ቀን ሁላችን የምንነሳው ትንሣኤ እንዲሁ ዳግመኛ ሞት የሌለበት ዘላለማዊ ትንሣኤ ነው፡፡
ፊተኛው ትንሣኤ:- በዚኛው ትንሣኤ የሚነሡት ጻድቃን የሚወርሱት መንግሥተ ሰማያትን ነው፡፡ ሲነሡም ብርሃን ለብሰው ብርሃን ተጎናጽፈው እንደ ፀሐይ እያበሩ ነው፡፡ (ራዕ 21÷1-5 ፤ 2ተኛ መቃ 13÷8-14)፡፡ ከዳግም ምጽዓት በኋላ የማይቆጠር እድሜ እንኖራለን ማለት ነው፡፡
ኋለኛው ትንሣኤ:- ይህን ትንሣኤ የሚነሡት ሰዎች በዚህች ምድር ሳሉ እግዚአብሔርን ሲበድሉ በክህደት በምንፍቅና የሚኖሩ የትንሣኤ ልቡና ያላገኙ እና ባጠቃላይ በወንጌል ያላመኑ ሰዎች የሚነሱት ትንሣኤ ነው፡፡ የኋለኛውን ትንሣኤ የሚነሱት ኃጥአን የግብር አባታቸውን ሰይጣንን መስለው ለዘላለም በማይጠፋበት በገሃነመ እሳት ውስጥ ይኖራሉ፡፡ (ማቴ 13÷42፣50፤ 22÷13፤025÷30)
የሙታን አነሳስ፡- “የሞትህ ተነሥ” የሚል አዋጅ በመላእክት አለቃ በቅዱስ መልአክ ይታወጃል፡፡ ጌታ ራሱ በትዕዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምጽ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና (1ና ተሰ 4÷16)፡፡ በምድር ላይ ስንኖር እንዳለው በሚበሰብስ ሥጋ ሳይሆን ዘላለማዊ በሆነው ሥጋ በክርስቶስ ያመንን ሁላችን እንነሳለን፡፡
መድኃኔዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቀደመው ለአባታችን ለአዳም በገባው ቃልኪዳን መሠረት፤ በአይሁድ እጅ መከራ መስቀልን ከተቀበለ በኋላ ነፍሱን በራሱ ስልጣን አሳልፎ ሰጠ፡፡ ከዚያም በኋላ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ መስፍኑ ጲላጦስን አስፈቅደው ከመስቀል አውርደው ዮሴፍ ራሱ ባሰራው መቃብር በንጹህ በፍታ ገንዘው ቀበሩት፡፡ ሲሄዱም ጸሐፍት ፈሪሳውያንና መስፍኑ በመቃብሩ ላይ ማኅተማቸውንና ጠባቂዎችን አኖሩ (ማቴ 27÷57-66 ማር 15÷42 ሉቃ 23÷50 ዮሐ 19÷38-42) ፡፡ ጌታቸን በሦስተኛው ቀን እሁድ በእኩለ ሌሊት መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በታላቅ ኃይል ሞትንና መቃብርን አጥፍቶ ተነሣ፡፡ ይጠብቁ የነበሩ ጠባቂዎችም ደንግጠው ተበታተኑ በመቃብሩ ዙሪያ ቅዱሳን መላዕክት ታዩ (ማቴ 28÷1-15 ማር 16÷11-15 ሉቃ 24÷1-43 ዮሐ 20÷1-25 1ኛ ቆሮ 15-1 ሮሜ 6÷9-15)፡፡ ለሰው ልጆች ዘላለማዊ ትንሣኤ በኩር የሆነው የክርስቶስ ትንሣኤ ነው፡፡ በመጨረሻው ቀን ሁላችን የምንነሳው ትንሣኤ እንዲሁ ዳግመኛ ሞት የሌለበት ዘላለማዊ ትንሣኤ ነው፡፡
ፊተኛው ትንሣኤ:- በዚኛው ትንሣኤ የሚነሡት ጻድቃን የሚወርሱት መንግሥተ ሰማያትን ነው፡፡ ሲነሡም ብርሃን ለብሰው ብርሃን ተጎናጽፈው እንደ ፀሐይ እያበሩ ነው፡፡ (ራዕ 21÷1-5 ፤ 2ተኛ መቃ 13÷8-14)፡፡ ከዳግም ምጽዓት በኋላ የማይቆጠር እድሜ እንኖራለን ማለት ነው፡፡
ኋለኛው ትንሣኤ:- ይህን ትንሣኤ የሚነሡት ሰዎች በዚህች ምድር ሳሉ እግዚአብሔርን ሲበድሉ በክህደት በምንፍቅና የሚኖሩ የትንሣኤ ልቡና ያላገኙ እና ባጠቃላይ በወንጌል ያላመኑ ሰዎች የሚነሱት ትንሣኤ ነው፡፡ የኋለኛውን ትንሣኤ የሚነሱት ኃጥአን የግብር አባታቸውን ሰይጣንን መስለው ለዘላለም በማይጠፋበት በገሃነመ እሳት ውስጥ ይኖራሉ፡፡ (ማቴ 13÷42፣50፤ 22÷13፤025÷30)
የሙታን አነሳስ፡- “የሞትህ ተነሥ” የሚል አዋጅ በመላእክት አለቃ በቅዱስ መልአክ ይታወጃል፡፡ ጌታ ራሱ በትዕዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምጽ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና (1ና ተሰ 4÷16)፡፡ በምድር ላይ ስንኖር እንዳለው በሚበሰብስ ሥጋ ሳይሆን ዘላለማዊ በሆነው ሥጋ በክርስቶስ ያመንን ሁላችን እንነሳለን፡፡
ሰላም እንዴት ናችሁ ?
የግንቦት ወር የወንጌል ስርጭት ወር ነው ይሄ ማለት ግን በሌላው ወር ወንጌል አይሰራም ማለት አይደለም ግን በዋናነት በዚህ ወር ወንጌል የሚሰበክበት ነው እናም ወንጌል በስራ ቦታችሁ እንድትሰብኩ ከዛም ባለፈ ደግሞም በሕይወታችሁ የክርስቶስ መልክ እንድትገልፁ የወንድምናት ምክር ነው ።
ከመጽሐፍ ቅዱስ
“እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።”
— ማቴዎስ 28፥19-20
An essay is a focused piece of writing that develops an argument or explores an idea using evidence, analysis, and interpretation. It typically consists of three main parts: an introduction with a clear thesis statement, body paragraphs for support, and a conclusion that ties everything together. [1, 2]
The Writing Process
Preparation: Research your topic, define your argument, and create an outline.
Drafting: Write the introduction, body, and conclusion based on your outline.
Revision: Edit for flow, clarity, grammar, and ensure all evidence supports your thesis. [1]
Standard Essay Structure
Introduction: Introduces the topic, provides background, and states your main argument (thesis).
Body Paragraphs: Each paragraph discusses one main idea and supports it with examples, quotes, or evidence.
Conclusion: Summarizes the main points, restates the thesis in a new way, and provides a final thought or resolution without introducing new evidence. [1, 2, 3, 4]
Common Essay Types
Argumentative: Persuades the reader to agree with your point of view using evidence.
Expository: Explains or informs the reader about a specific topic.
Narrative/Reflective: Tells a story or explores a topic based on personal experience.
Descriptive: Paints a picture of a person, place, or thing through detailed sensory language.
ታሪካዊ ሥረ መሠረት
በክፍል ሦሥት ----(3)
ዮናስ የኖረው በዳግማዊ ኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት ነው (782-753 ዓ.ዓ.)። ኢዮርብዓም እግዚአብሔርን የማያመልክ ክፉና ኃጢአተኛ ቢሆንም፥ ኃይለኛ ንጉሥ እንደነበር የሚታወስ ነው። የእስራኤልን ድንበር በዳዊትና በሰሎሞን ዘመነ መንግሥት ወደነበረበት ስፍራ ሊመልስ ችሎ ነበር። ይህ የሆነበት አንዱ ምክንያት በዚያ ዘመን ከነዓንን የሚቆጣጠር ኃያል መንግሥት አለመኖር ነው። ወደ ሰሜን ምሥራቅ ርቃ ትገኝ የነበረችውና ሶርያን ያሸነፈችው አሦርም ደካማ ነበረች። ይህም ለእስራኤል ሕዝብ ታላቅ ሰላምንና ብልጥግናን አስገኝቶ ነበር። እስራኤል ታላቅ አገር በሆነች ጊዜ በብርታትዋ ትታበይ ጀመር። ኃይሏንና ብልጥግናዋን ያገኘችው የእግዚአብሔር ምርጥ በመሆኗ መሰላት፡፡ በውስጧ የነበረውን የጣዖት አምልኮ እያወቀች ካለማስወገዷም ንስሐ ለመግባት አልፈለገችም።
እስራኤላውያን የእግዚአብሔር ሕዝብ ስለሆኑ እግዚአብሔር ለሌሎች አሕዛብ፥ በተለይም በጭካኔያቸው አንድ ጊዜ ለታውቁ ሕዝቦች ግድ የለውም የሚል እምነት ነበራቸው። አሦር ኃያል አገር እንደሆነችና በማንኛውም ጊዜ የእነርሱ ጠላት ልትሆን እንደምትችል እስራኤላውያን ያውቁ ነበር። ነቢዩ አሞጽ በኋላም ሆሴዕ በኃጢአታቸው ምክንያት እግዚአብሔር ከደማስቆ ባሻገር (አሞጽ 5፡27) ትገኝ ወደነበረችው ወደ አሦር (ሆሴዕ 9፡3) እንደሚያስማርካቸው ለእስራኤል ሕዝብ መናገር ጀምረው ነበር፡፡ እግዚአብሔር የእስራኤልን ሕዝብ የሚቀጣው በአሦር አማካይነት እንደሆነ ዮናስ ያውቅ እንደነበረ መገመት ይቻላል።
አሦራውያን ለጠላቶቻቸው ከፍ ያለ ጭካኔን በማሳየት ቀድሞውኑ እውቅናን ያተረፉ ነበሩ። አንዳንድ ጊዜ ጠላቶቻቸውን ከነሕይወታቸው ይቀብሩ፥ ቆዳቸውን ይገፍፉና ምላሳቸውን ጎልጉለው በማውጣት ይቆርጡ ነበር። ዮናስ ወደ ነነዌ ሰዎች ሄዶ ለመስበክ ያልፈለገባቸው ምክንያቶች እነዚህ ነበሩ።
እግዚአብሔር በዮናስ በኩል ለሚያመጣው መልእክት አሦራውያንን አዘጋጅቶአቸው ነበር ማለት ይቻላል። በ765ና በ759 ዓ.ዓ. አሦርን የመቱ ሁለት ከባድ መቅሠፍቶች ወርደው ነበር። በ763 ዓ.ዓ. ደግሞ የጥንት ሰዎች ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔር ፍርድ ምልክት ነው ብለው የሚያምኑት የፀሐይ ግርዶሽ ተከስቶ ነበር። አንዳንዶች ደግሞ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይፈጸም አልቀረም ይላሉ። ዮናስ ራሱ ያልተለመደ ምልክት ነበር ማለት ይቻላል። ዮናስ በዓሣ ነባሪ ሆድ ውስጥ ለሦስት ቀናት ስለቆየ፥ የዓሣ ነባሪው የጨጓራ አሲድ ፀጉሩንና ቆዳውን ወደ ነጭነት ቀይሮት ይሆናል። አሦራውያን ዮናስ ላመጣው መልእክት ፈጣን ምላሽ የሰጡት በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች ሳይሆን አይቀርም።
የትንቢተ ዮናስ አስተዋጽኦ
1. ዮናስ ለአሦራውያን እንዲሰብክ ከተሰጠው ተልእኮ ሸሸ (ዮናስ 1-2)፤
2. ዮናስ ለአሦራውያን እንዲሰብክ የተሰጠውን ተልእኮ ፈጸመ (ዮናስ 3-4)፤
ሀ. የሕዝቡ በንስሐ መመለስ (ዮናስ 3)፥
ለ. ለእግዚአብሔር ምሕረት ዮናስ የሰጠው ምላሽ (ዮናስ 4)፥
የመጨረሻ ክፍል
እግዚአብሔር ይባርካችሁ
የትንቢተ ዮናስ መጽሐፍ
በክፍል ሁለት -----(2)
የትንቢተ ዮናስ መጽሐፍ
የትንቢተ ዮናስ ታሪክ እውነተኛነት በብዙ ምሁራን ዘንድ አጠያያቂ ሆኖአል። ዮናስ በዓሣ ነባሪ ሆድ ውስጥ ለሦስት ቀናት እንዴት በሕይወት ሊቆይ ይችላል? ጥላ የሆነችው ቅል እንዴት በፍጥነት ልታድግ ቻለች? ይህ ሊሆን የሚችል ነገር አይደለም በማለት ምሁራን መጽሐፉን በተለያዩ መንገዶች ይተረጉማሉ።
1. ተምሳሌታዊ አተረጓጐም፡- የመጽሐፉ ታሪክ እያንዳንዱ ክፍል አንድን እውነት የሚወክል ነው። ታሪኩንም ሆነ ለታሪኩ የሚሰጠውን ትርጉም በቁሙ (በቀጥታ) ልንረዳው አይገባም።
2. ምሳሌያዊ አተረጓጐም፡- አንዳንዶች ደግሞ ይህ ታሪክ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ከተናገራቸው ምሳሌዎች ጋር ተመሳሳይ ነው ይላሉ። (ለምሳሌ፡- የመልካሙ ሳምራዊ ታሪክ)። ይህ ታሪክ እውነተኛ አይደለም። ነገር ግን የሥነ-ምግባር ትምህርት ለማስተማር የተዘጋጀ የፈጠራ ታሪክ ነው ይላሉ። የዚህ ዓይነቱ ታሪክ ልጆች እውነትን በሚገባ እንዲረዱ ለማድረግ የሚነገር እውነተኛ ያልሆነ ታሪክ የሚመስል ነው)።
3. እውነትን ለማስተማር ተጋንኖ የቀረበ ታሪክ፡- አንዳንዶች የዚህ ታሪክ የተወሰነ ክፍል እውነተኛ ነው ይላሉ። ወደ ነነዌ የሄደ ዮናስ የሚባል ሰው ነበር። ይሁን እንጂ በታሪኩ ውስጥ የተጠቀሱት ዝርዝር ጉዳዮች ታሪኩን የበለጠ ልብ የሚነካ ለማድረግ ተጋንነው የቀረቡ ናቸው። ይህም የተመለከትነውን አደጋ ለመግለጥ ወይም የሠራነውን ታላቅ ሥራ ለማስረዳት በማጋነን እንደምንናገራቸው ነገሮች ያለ ነው። የተመሠረተው በእውነተኛ ታሪክ ላይ ቢሆንም፥ ይበልጥ ሕይወት እንዲኖረው ለማድረግ በዝርዝር ጉዳዮች ላይ ተጨማሪ ነገሮችን እናክላለን።
4. በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተጻፈው በቀጥታ በዮናስ ሕይወት የተፈጸም ታሪክ ነው። መጽሐፉን የምንረዳበት ከሁሉም የተሻለው መንገድ ተአምራቱን ጨምሮ የተጻፈው ሁሉ እንዳለ የተፈጸመ እውነተኛ ታሪክ መሆኑን ማመን ነው። ኢየሱስ በዚህ ታሪክ እንዳመነና ዮናስ በዓሣ ነባሪ ሆድ ውስጥ ለሦስት ቀንና ሌሊት የቆየበትን ታሪክ የሞቱና የትንሣኤው መግለጫ አድርጎ እንደተጠቀመባት ግልጽ ነው (ማቴዎስ 12፡40-41)። በዓሣ ነባሪ ሆድ ውስጥ በርካታ ቀናት የቆዩና ዓሣ ነባሪው ተይዞ ከውስጡ ሲወጡ በሕይወት የተገኙ የሌሎች ሰዎች ታሪኮች አሉ።
ታሪካዊ ሥረ መሠረት
በክፍል ሦሥት ----(3)
ይቀጥላል
✍አገልጋይ መከተ ደባይ
ክፍል አንድ ----(1)
የትንቢተ ዮናስ ጸሐፊ
ከታናናሽ ነቢያት ሁሉ ላቅ ብሉ የታወቀው ዮናስ ነው። ታሪኩን ሁላችንም የምናውቀው ነው። ትንቢተ ዮናስ ከታናናሽ ነቢያት የሚመደብ ቢሆንም፥ ከሌሉች የትንቢት መጻሕፍት ሁሉ ፍጹም የተለየ ነው። የትንቢት መጻሕፍት በሙሉ ነቢያት ለሕዝቡ የተናገሯቸው መልእክቶች የተጻፉባቸው ናቸው። ትንቢተ ዮናስ ግን ነነዌ በጥቂት ቀናት ውስጥ እንደምትጠፋ የሚገልጽ መልእክት ከመያዙ ሌላ ምንም ዓይነት ትንቢት አልያዘም። ይልቁንም መጽሐፉ ከነቢያት አንዱ የሆነውን የዮናስን ታሪክ የያዘ ነው።
ትንቢተ ዮናስ የተሰየመው የመጽሐፉ ዋና ባለታሪክ በሆነው በዮናስ ስም ነው። መጽሐፉን ዮናስ እንደጻፈው የሚገልጽ አሳብ በመጽሐፉ ውስጥ ስለሌለና የተጻፈው በሦስተኛ ሰው ስለሆነ፥ ማን እንደጻፈው ማረጋገጥ አንችልም። በግምት ግን የዚህ መጽሐፍ ጸሐፊ ዮናስ ሳይሆን አይቀርም። እንዲሁም የዮናስን ታሪክ በሚያውቅ በሌላ ሰውም ተጽፎ ሊሆን ይችላል።
እንደ አብዛኛዎቹ ታናናሽ ነቢያት፥ ስለ ዮናስ የምናውቀው ነገር በጣም ጥቂት ነው። ዮናስ ነቢይ እንደሆነ በ2ኛ ነገሥት 14፡25 ተጠቅሷል። በእስራኤል ይኖር የነበረና በዳግማዊ ኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት የነበረ ነቢይ ነው። ለእስራኤል ሕዝብ ለማስተላለፍ የፈለገው መልእክት ምን እንደ ነበረ አናውቅም። ስለ እርሱ የምናውቀው ነገር ቢኖር፥ እግዚአብሔር የአሦር ዋና ከተማ ወደነበረችው ወደ ነነዌ የፍርድ መልእክት እንዲያደርስ በላከው ጊዜ ከእግዚአብሔር ጋር የነበረውን ግንኙነት ብቻ ነው።
በትንቢተ ዮናስ ከተመዘገበው ታሪክ ቀጥሎ ምን እንደተፈጸመ የምናውቀው ነገር የለም። ዮናስ ከኃጢአቱ በንስሐ ተመልሶ ይሆን?
ካሳለፈው የሕይወት ልምድ ተምሮ ይሆን? ወደ እስራኤል የተመለሰው በንስሐ በተለወጠ ልብ ካልሆነ በቀር መጽሐፉን አይጽፍም ነበር የሚል እምነት ስላለን፥ ለእነዚህ ጥያቄዎች ልንሰጥ የምንችለው ምላሽ ቢኖር አዎንታዊ ግምት ብቻ ነው።
የትንቢተ ዮናስ መጽሐፍ
በክፍል ሁለት -----(2)
ይቀጥላል
መዝሙር 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²³ እግዚአብሔርን የምትፈሩ፥ አመስግኑት፤ የያዕቆብ ዘር ሁላችሁ፥ አክብሩት፥ የእስራኤልም ዘር ሁላችሁ፥ ፍሩት።
²⁴ የችግረኛን ችግር አልናቀምና፥ ቸልም አላለምና፤ ፊቱንም ከእኔ አልሰወረምና፥ ነገር ግን ወደ እርሱ በጮኽሁ ጊዜ ሰማኝ።
²⁵ በታላቅ ጉባኤ ምስጋናዬ ከአንተ ዘንድ ነው፤ እርሱን በሚፈሩት ፊት ስእለቴን እሰጣለሁ።
²⁶ ችግረኞች ይበላሉ፥ ይጠግቡማል፤ እግዚአብሔርንም የሚሹት ያመሰግኑታል፤ ልባቸውም ለዘላለም ሕያው ይሆናል።
²⁷ የምድር ዳርቻዎች ሁሉ ያስቡ፥ ወደ እግዚአብሔርም ይመለሱ፤ የአሕዛብ ነገዶች ሁሉ በፊቱ ይሰግዳሉ።
²⁸ መንግሥት ለእግዚአብሔር ነውና፥ እርሱም አሕዛብን ይገዛል።
Repost from የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
መጽሐፍ ቅዱስ በማን፣ መቼ፣ የትና ለማን ተጻፈ፣ ይዘቱስ?
ክፍል ሁለት ......(2)
ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶበእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን፡፡” ዮሐንስ 1፡14 ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ዘላለማዊ ቃል በመሆኑ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ነው፤ ስለዚህ እግዚአብሔርን ሙሉ በሙሉ መግለጥ ይችላል፡፡ እርሱ የእግዚአብሔር የመጨረሻው ታላቅ መገለጥ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ቦታዎች ላይ ይናገራል (ቆላስይስ 2፡9 ጢሞቴዎስ 3:16 ቆላስይስ 1፡15-16 ዮሐንስ 14፡7-10)
ከመሲሁ ስሞች መካከል አንዱ “አማኑኤል” የሚል ሲሆን ትርጓሜውም “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር” ማለት ነው፡፡ ይህንን በተመለከተ ኢየሱስ ከመወለዱ ከ700 ዓመታት በፊት ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ የሚል ትንቢት ተናግሮ ነበር፡-
“ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።” ኢሳይያስ 7፡14
ክርስትና እግዚአብሔር ከንግግር ባለፈ መንገድ ራሱን ለሰው ልጆች እንደገለጠ ያስተምራል፡፡ ይህም አንድያ ልጁን ወደ ምድር በመላክ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ዘላለማዊ ቃል የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በማይለካ ፍቅር፣ በማይለካ ፅድቅ፣ በማይለካ ቅድስና፣ በማይለካ እውነተኛነትና በማይለካ ይቅር ባይነት የእግዚአብሔርን ማንነት በትክክል አሳይቶናል፡፡ በእርሱም በኩል እግዚአብሔርን አይተነዋል፡፡ በስሙ የሚያምኑ ሰዎች የእርሱን ማንነት በሕይወታቸው ውስጥ እውን ሆኖ ያገኙታል፡፡ የክርስትና አስደናቂና አስደሳቹ ገጽታም ይህ ነው፡፡
https://t.me/Nn4F7fF
Repost from የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
መጽሐፍ ቅዱስ በማን፣ መቼ፣ የትና ለማን ተጻፈ፣ ይዘቱስ?
ክፍል አንድ ...(1)
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው የጻፉት መጽሐፍ እንደሆነ ክርስቲያኖች ያምናሉ፡፡ እነዚህ ጸሐፊያን በተለያዩ ቦታዎችና ዘመናት የኖሩ ሰዎች ነበሩ፡፡ እድሜያቸው፣ ዕውቀታቸው፣ሥራቸው እንዲሁም በማሕብረሰባቸው ውስጥ የነበራቸው ደረጃ የተለያየ ነበር፡፡ ከጸሐፍቱ መካከል አብዛኞቹ ስሞቻቸው ከጻፏቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ጋር ተያይዘው ተጠቅሰዋል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ተጽፎ ለመጠናቀቅ 1,500 ዓመታት ያህል ፈጅቷል፡፡ የመጀመርያው ጽሑፍ የተከተበው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ1400 ዓ.ዓ. አካባቢ እንደሆነና የመጨረሻው ክፍል ደግሞ ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ90ዓ.ም. አካባቢ እንደተጻፈ በአብዛኞቹ ምሑራን ዘንድ ይታመናል፡፡
የዚህ እድሜ ጠገብ መጽሐፍ ልዩ ልዩ ክፍሎች በተለያዩ ሦስት አህጉራት፣ ማለትም በኢስያ፣ አውሮፓና አፍሪካ ውስጥ ተጽፈዋል፡፡
የመጽሐፍ ቅዱስ ይዘት:-
ይህ ታላቅ መጽሐፍ ተጽፎ ለመጠናቀቅ 1500 ዓመታትን የፈጀ፣ ከ40 በላይ ጸሐፊያንን ያሳተፈና በተለያዩ ብዙ ቦታዎች የተጻፈ ቢሆንም በሚያስደንቅ ሁኔታ ማዕከላዊ መልዕክቱ አንድ ነው፤ እርሱም እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ያዘጋጀው የዘለዓለም ሕይወት ነው፡፡ ብሉይ ኪዳን ለእግዚአብሔር ልጅ ለኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር መምጣት ቅድመ ዝግጅት ሲሆን አዲስ ኪዳን ደግሞ የእርሱን መምጣት እውን መሆን የሚያበስር ነው፡፡
ብሉይ ኪዳን የፍጥረትን አጀማመርና የጥፋትን ውሃ ከተረከ በኋላ እግዚአብሔር አብርሃም የተሰኘ የመስጴጦምያ (Mesopotamia) ሰው ስለመጥራቱና ከዚህም ሰው እስራኤል የተባለ ሕዝብ ስለመገኘቱ ይተርክልናል፡፡ የአብርሃም መጠራት መሲሁ ኢየሱስ ወደ ምድር ይመጣ ዘንድ የመጀመርያው ዝግጅት ነበር፡፡ በዘፍጥረት 26፡4 ላይ እግዚአብሔር “የምድርም አህዛብ ሁሉ በዘርህ ይባረካሉ” የሚል ቃል ኪዳን ለአብርሃም ገብቶለት ነበር፡፡ ይህ ቃል ኪዳን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እንደተፈጸመ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ተናግሯል (ገላትያ 3፡16)፡፡ የተቀረው የብሉይ ኪዳን ክፍል በአብዛኛውየሚያተኩረው እግዚአብሔር ከሕዝበ እስራኤል ጋር በነበረው ግንኙነት እንዲሁም ስለመሲሁ መምጣትና ስለ አሕዛብ ወደ እግዚአብሔር መመለስና ስለሌሎች ብዙ ጉዳዮች በተተነበዩ የነቢያት ትንቢቶች ላይ ነው፡፡
አዲስ ኪዳን በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት፣ በትምህርቶቹ እንዲሁም ከእርገቱ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ባደረጓቸው ነገሮችና ባስተማሯቸው ትምህርቶች ላይ ያተኩራል፡፡ ጠቅለል ባለ ሁኔታ የአዲስ ኪዳን መልዕክት ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማይ የመጣ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ማስተማሩን፣ ማንነቱን የሚያረጋግጡ ብዙ ተዓምራትን ማድረጉን፣ መከራን መቀበሉን፣ ስለ ሰው ልጆች ኃጢዓት ሲል በመስቀል ላይ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን መነሳቱን፣ ለደቀ መዛሙርቱ መታየቱን፣ ወደ ሰማይማረጉን፣ ለሁሉም እንደ የሥራው ሊከፍል ወደ ምድር ተመልሶ እንደሚመጣ፣ ደቀ መዛሙርቱ ደግሞ ለእነዚህ ነገሮች ምስክሮች መሆናቸውንና የዘለዓለም ሕይወት የሚገኘው በእርሱ በማመን ብቻ መሆኑን የሚናገር ነው፡፡መጽሐፍ ቅዱስ አንድ ዓይነት የሥነ ጽሑፍ ስልት የተከተለ መጽሐፍ አይደለም፡፡ ሕግ፣ ትረካ፣ ቅኔ፣ትንቢት፣ መልዕክት፣ አቡ ቀለም ሲስ፣ ወዘተ. የመሳሰሉ ዘርፈ ብዙ የሥነ ጽሑፍ ዓይነቶች በውስጡ ይገኛሉ፡፡
የመገለጥ ትርጉም፡-
የተለያዩ ኃይማኖቶች ስለመገለጥ የየራሳቸው የሆነ አመለካከት አላቸው፡፡ ለምሳሌ ያህል ሙስሊሞች ቅዱስ ቁርአን “የተገለጠበትን” ሁኔታ ተንዚል ወይም ናዚል በማለት ይጠሩታል፡፡ ተንዚል ማለት “ከላይ የወረደ መገለጥ” ማለት ነው፡፡ ከጥንት ጀምሮ የነበረው ክርስቲያናዊ አመለካከት መጽሐፍ ቅዱስ ከላይ የወረደ መገለጥ ነው የሚል ሳይሆን የእግዚአብሔር ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ በመነዳት (በመመራት) የጻፉት ቃል ነው የሚል ነው፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሰዎቹ የነበራቸውን እውቀት፣ባህልና ቋንቋ እንዲጠቀሙ መንፈስ ቅዱስ ፈቅዷል፡፡
ክርስቲያኖች የሚያምኑት ከላይ የወረደው የእግዚአብሔር መገለጥ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ መሆኑን ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን በሰው ልጆች ባህል፣ ቋንቋና ታሪክ የተገለጠ በጽሑፍ የቀረበ ግልጠተ-መለኮት ነው፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ንግግር ብቻ ሳይሆን የሰው ልጆች ለእግዚአብሔር ሐሳብ የሰጡትንም ምላሽ በውስጡ አካቷል፡፡ ይህም ማለት መጽሐፍ ቅዱስ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት በውስጡ የያዘ መጽሐፍ ነው ማለት ነው፡፡ ለዚህ ነው በተለያዩ ዘመናት የተደረጉየሰው ልጆች ታሪኮች በውስጡ የሚገኙት፡፡
በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶስ “የእግዚአብሔር ቃል” (ሎጎስ) ተብሎ ተጠርቷል፡፡ ይህም እግዚአብሔር በሙላት ራሱን የገለጠው በእርሱ በኩል መሆኑን ያሳያል፡፡ “በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ። ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም ዮሐንስ 1፡1-3፡፡ እግዚአብሔር ዓለማትን የፈጠረበት ሕያውና ዘላለማዊ ቃሉ ሰው ሆኖ በመምጣት ከሰው ልጆች ጋር በምድርላይ ኖረ፤ የእግዚአብሔርንም ማንነት በሙላት ገለጠ፡፡ ይህ መገለጥ ተሠግዎ (Incarnation) በመባል ይታወቃል፡፡ ተሠግዎ ማለት “ሥጋ መሆን” ማለት ነው፡፡
ክፍል ሁለት ....(2)
ይቀጥላል .........
✍አገልጋይ መከተ ደባይ
https://t.me/Nn4F7fF
Repost from የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች
አንድ መጽሐፍ ብዙ ተከታዮች ስላሉት ወይንም ደግሞ በውስጡ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን የሚናገር ሐሳብ ስለ ተጻፈ ብቻ የእግዚአብሔር ቃል ሊሆን አይችልም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ነው ካልን ይህንን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ሊኖሩን ይገባል፡፡ እነዚህ ማስረጃዎች ደግሞ ሊነሱ የሚችሉ መስቀለኛ ጥያቄዎችን በሙሉ የማለፍ አቅም ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ካልሆነ ግን አንድ ሐሳብ እንደ ማስረጃ መጠቀሱ በራሱ የሚፈጥረው ልዩነት አይኖርም፡፡ የእግዚአብሔር ቃል መሆናቸውን የሚናገሩ እና ብዙ አማንያንን የሚያስከትሉ ኁልቈ መሣፍርት የሌላቸው መጻሕፍት በዓለማችን ላይ ይገኛሉ፡፡ በመካከላቸው ካለው ያለመጣጣም የተነሳ ከእነርሱ መካከል ሁለቱ እንኳ በአንድ ጊዜ እውነት ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ከእነዚህ ሁሉ መካከል ትክክለኛ ቃለ እግዚአብሔር ሊሆን የሚችለው አንዱ መጽሐፍ ብቻ ነው፡፡ ይህንን መጽሐፍ ለይተን እናውቅ ዘንድ የሚያስችሉን የማያሻሙ፣ ግልፅ የሆኑ እና አብዛኞቹ ሰዎች ሊገነዘቧቸው የሚችሏቸው ማስረጃዎች ሊኖሩን ያስፈልጋል፡፡
አንዳንድ ኃይማኖቶች ቅዱሳት መጽሐፍታቸው እውነተኛ የእግዚአብሔር ቃል መሆናቸውን ለማሳየት አሻሚ የሆኑና በግላዊ ስሜትና መረዳት ላይ የተመሰረቱ (Subjective) መስፈርቶችን ይጠቀማሉ፡፡ ለምሳሌ ያህል የሞርሞን እምነት ተከታዮች አንድ ሰው በቅዱስ መጽሐፋቸው ላይ እጆቹን አድርጎ ቢፀልይ ልቡ አካባቢ የማቃጠል ስሜት እንደሚሰማውና በዚህ መፈተኛ ተጠቅሞ እውነተኛነቱን ማረጋገጥ እንደሚችል ይናገራሉ፡፡ ሙስሊሞች ደግሞ ቁርኣን ከሁሉም መጽሐፍት የላቀ ሥነ ጽሑፋዊ ውበት ስላለው ይህ የፈጣሪ ቃል መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ይናገራሉ፡፡ ክርስቲያኖች ግን መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ለማረጋገጥ መሰል “ማስረጃዎችን” አይጠቅሱም፡፡ ከነዚህ ይልቅ ጠንካራ የሆኑ እና በግል ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ (Objective) ማስረጃዎችአሉን፡፡ እነዚህ ማስረጃዎች ምንድናቸው? ሊጠቀሱ ከሚችሉት መካከል የተወሰኑትን በሚከተሉት ክፍሎች እንመለከታችኋለን፡፡
Repost from የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሚነሱ ተቃውሞዎችና ምላሾቻቸው
በመግቢያችን ላይ እንዳልነው በዚህች ዓለም ላይ እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ተቃውሞዎችንና ትችቶችን ያስተናገደ መጽሐፍ የለም ብንል ማጋነን አይሆንም፡፡ በተለይም ደግሞ ከዘመነ አብርሆት (Enlightenment) በኋላ የተነሱ ብዙ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን በማጣጣልና በመተቸት ብዙ ጽሑፎችን ጽፈዋል፤ ብዙ ንግግሮችንም አድርገዋል፡፡ በዚያን ዘመን ብቅ ያለው የለዘብተኛ ሥነ መለኮት አስተምሕሮ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለሚገኙ አንኳር አስተምህሮዎች የራሱን አማራጭ ትንታኔዎች በማዘጋጀት የክርስትናን መሠረት ለማናጋት በከፍተኛ ትጋት ሲሠራ ቆይቷል፡፡ በዘመናችን የሚገኙ አምላክ የለሾችና የሌሎች ኃይማኖታዊ ቡድኖች ምሑራን የለዘብተኛ ሥነመለኮት አቀንቃኞችን ትምህርቶች በመቀበል ያስተጋባሉ፡፡
ዛሬ በተለያዩ መጽሐፍቶችና የኤሌክትሮኒክስ የመገናኛ አውታሮች ተሰራጭተው የምናያቸው የተለያዩ የመሟገቻ ሐሳቦች ቅርፃቸው ቢለዋወጥ እንጂ ከጥንት ጀምሮ የነበሩና በቤተ ክርስቲያን አባቶች ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት ምላሽ የተሰጠባቸው ናቸው፡፡ ክርስቲያኖች እንደ መሆናችን ሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያላቸውን ጥያቄ በነፃነት መጠየቃቸው ያስደስተናል፡፡ ጥያቄዎችንም በፍቅርና በአክብሮት መመለስ ኃላፊነታችን መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ አሳዛኙ ነገር ግን እነዚህን ጥያቄዎች ከሚጠይቁ ወገኖቻችን መካከል አብዛኞቹ ፍላጎታቸው መልስ ማግኘት ሳይሆን ክርክር መሆኑ ነው፡፡ ለዚህ ነው እልፍ ጊዜ የተመለሰን ጥያቄ በሌላ ጊዜ ምንም ማሻሻያ ሳያደርጉለት መልሰው የሚጠይቁት፡፡ ከእነዚህ ወገኖች ጋር የሚደረገው ውይይት ፍሬ አልባና አድካሚ ቢመስልም ነገር ግን መልስ ለመስጠት አንታክትም፡፡ ይህንን የምናደርግበት ምክንያቱ እውነትን በቅን ልብ የሚፈልጉ ሰዎች በእነዚህ የተሳሳቱ መረጃዎች እንዳይታለሉ ለመርዳት ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዟልን?
በመጽሐፍ ቅዱስ ተኣማኒነት ላይ የሚነሳው የተለመደ ተቃውሞ መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዟል የሚል መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ይህንን ስሞታ በተደጋጋሚ የሚያሰሙት ደግሞ ሙስሊም ወገኖቻችን ናቸው፡፡ ከቁርአን አስተምህሮና ከቀደሙት ሙስሊሞች እምነት ጋር የማይስማማ ቢሆንም አብዛኞቹ የዘመናችን ሙስሊሞች ስለ ነቢዩ መሐመድ የተተነበዩትን ትንቢቶች ለማስወገድና ለማድበስበስ አይሁድና ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስን በርዘውታል የሚል አቋም አላቸው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሚነሱ “ግጭቶች” እና “ሳይንሳዊ ስህተቶችን ”የመሳሰሉ ውንጀላዎች በሙሉ የዚህኛው ውንጀላ ንዑሳን ክፍሎች ናቸው፡፡ ዓላማቸውም መጽሐፍ ቅዱስ “መበረዙን” ማረጋገጥ ነው፡፡
https://t.me/Nn4F7fF
Repost from የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች
አንድ መጽሐፍ ብዙ ተከታዮች ስላሉት ወይንም ደግሞ በውስጡ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን የሚናገር ሐሳብ ስለ ተጻፈ ብቻ የእግዚአብሔር ቃል ሊሆን አይችልም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ነው ካልን ይህንን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ሊኖሩን ይገባል፡፡ እነዚህ ማስረጃዎች ደግሞ ሊነሱ የሚችሉ መስቀለኛ ጥያቄዎችን በሙሉ የማለፍ አቅም ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ካልሆነ ግን አንድ ሐሳብ እንደ ማስረጃ መጠቀሱ በራሱ የሚፈጥረው ልዩነት አይኖርም፡፡ የእግዚአብሔር ቃል መሆናቸውን የሚናገሩ እና ብዙ አማንያንን የሚያስከትሉ ኁልቈ መሣፍርት የሌላቸው መጻሕፍት በዓለማችን ላይ ይገኛሉ፡፡ በመካከላቸው ካለው ያለመጣጣም የተነሳ ከእነርሱ መካከል ሁለቱ እንኳ በአንድ ጊዜ እውነት ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ከእነዚህ ሁሉ መካከል ትክክለኛ ቃለ እግዚአብሔር ሊሆን የሚችለው አንዱ መጽሐፍ ብቻ ነው፡፡ ይህንን መጽሐፍ ለይተን እናውቅ ዘንድ የሚያስችሉን የማያሻሙ፣ ግልፅ የሆኑ እና አብዛኞቹ ሰዎች ሊገነዘቧቸው የሚችሏቸው ማስረጃዎች ሊኖሩን ያስፈልጋል፡፡
አንዳንድ ኃይማኖቶች ቅዱሳት መጽሐፍታቸው እውነተኛ የእግዚአብሔር ቃል መሆናቸውን ለማሳየት አሻሚ የሆኑና በግላዊ ስሜትና መረዳት ላይ የተመሰረቱ (Subjective) መስፈርቶችን ይጠቀማሉ፡፡ ለምሳሌ ያህል የሞርሞን እምነት ተከታዮች አንድ ሰው በቅዱስ መጽሐፋቸው ላይ እጆቹን አድርጎ ቢፀልይ ልቡ አካባቢ የማቃጠል ስሜት እንደሚሰማውና በዚህ መፈተኛ ተጠቅሞ እውነተኛነቱን ማረጋገጥ እንደሚችል ይናገራሉ፡፡ ሙስሊሞች ደግሞ ቁርኣን ከሁሉም መጽሐፍት የላቀ ሥነ ጽሑፋዊ ውበት ስላለው ይህ የፈጣሪ ቃል መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ይናገራሉ፡፡ ክርስቲያኖች ግን መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ለማረጋገጥ መሰል “ማስረጃዎችን” አይጠቅሱም፡፡ ከነዚህ ይልቅ ጠንካራ የሆኑ እና በግል ስሜት ላይ ያልተመሰረቱ (Objective) ማስረጃዎችአሉን፡፡ እነዚህ ማስረጃዎች ምንድናቸው? ሊጠቀሱ ከሚችሉት መካከል የተወሰኑትን በሚከተሉት ክፍሎች እንመለከታችኋለን፡፡
Repost from የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሚነሱ ተቃውሞዎችና ምላሾቻቸው
በመግቢያችን ላይ እንዳልነው በዚህች ዓለም ላይ እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ተቃውሞዎችንና ትችቶችን ያስተናገደ መጽሐፍ የለም ብንል ማጋነን አይሆንም፡፡ በተለይም ደግሞ ከዘመነ አብርሆት (Enlightenment) በኋላ የተነሱ ብዙ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን በማጣጣልና በመተቸት ብዙ ጽሑፎችን ጽፈዋል፤ ብዙ ንግግሮችንም አድርገዋል፡፡ በዚያን ዘመን ብቅ ያለው የለዘብተኛ ሥነ መለኮት አስተምሕሮ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለሚገኙ አንኳር አስተምህሮዎች የራሱን አማራጭ ትንታኔዎች በማዘጋጀት የክርስትናን መሠረት ለማናጋት በከፍተኛ ትጋት ሲሠራ ቆይቷል፡፡ በዘመናችን የሚገኙ አምላክ የለሾችና የሌሎች ኃይማኖታዊ ቡድኖች ምሑራን የለዘብተኛ ሥነመለኮት አቀንቃኞችን ትምህርቶች በመቀበል ያስተጋባሉ፡፡
ዛሬ በተለያዩ መጽሐፍቶችና የኤሌክትሮኒክስ የመገናኛ አውታሮች ተሰራጭተው የምናያቸው የተለያዩ የመሟገቻ ሐሳቦች ቅርፃቸው ቢለዋወጥ እንጂ ከጥንት ጀምሮ የነበሩና በቤተ ክርስቲያን አባቶች ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት ምላሽ የተሰጠባቸው ናቸው፡፡ ክርስቲያኖች እንደ መሆናችን ሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያላቸውን ጥያቄ በነፃነት መጠየቃቸው ያስደስተናል፡፡ ጥያቄዎችንም በፍቅርና በአክብሮት መመለስ ኃላፊነታችን መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ አሳዛኙ ነገር ግን እነዚህን ጥያቄዎች ከሚጠይቁ ወገኖቻችን መካከል አብዛኞቹ ፍላጎታቸው መልስ ማግኘት ሳይሆን ክርክር መሆኑ ነው፡፡ ለዚህ ነው እልፍ ጊዜ የተመለሰን ጥያቄ በሌላ ጊዜ ምንም ማሻሻያ ሳያደርጉለት መልሰው የሚጠይቁት፡፡ ከእነዚህ ወገኖች ጋር የሚደረገው ውይይት ፍሬ አልባና አድካሚ ቢመስልም ነገር ግን መልስ ለመስጠት አንታክትም፡፡ ይህንን የምናደርግበት ምክንያቱ እውነትን በቅን ልብ የሚፈልጉ ሰዎች በእነዚህ የተሳሳቱ መረጃዎች እንዳይታለሉ ለመርዳት ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዟልን?
በመጽሐፍ ቅዱስ ተኣማኒነት ላይ የሚነሳው የተለመደ ተቃውሞ መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዟል የሚል መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ይህንን ስሞታ በተደጋጋሚ የሚያሰሙት ደግሞ ሙስሊም ወገኖቻችን ናቸው፡፡ ከቁርአን አስተምህሮና ከቀደሙት ሙስሊሞች እምነት ጋር የማይስማማ ቢሆንም አብዛኞቹ የዘመናችን ሙስሊሞች ስለ ነቢዩ መሐመድ የተተነበዩትን ትንቢቶች ለማስወገድና ለማድበስበስ አይሁድና ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስን በርዘውታል የሚል አቋም አላቸው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሚነሱ “ግጭቶች” እና “ሳይንሳዊ ስህተቶችን ”የመሳሰሉ ውንጀላዎች በሙሉ የዚህኛው ውንጀላ ንዑሳን ክፍሎች ናቸው፡፡ ዓላማቸውም መጽሐፍ ቅዱስ “መበረዙን” ማረጋገጥ ነው፡፡
https://t.me/Nn4F7fF
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
