fa
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

رفتن به کانال در Telegram

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Ethiopian Public Service University

کانال Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 12 734 مشترک است و جایگاه 15 756 را در دسته آموزش و رتبه 2 642 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 12 734 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 11 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 106 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 3 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 34.72% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.17% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 419 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 058 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 27 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 12 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

12 734
مشترکین
+324 ساعت
+207 روز
+10630 روز
آرشیو پست ها
በኢፐሰዩ የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ትስስር መድረክ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ ‎በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ/ም በአባይ አዳራሽ “የቤተሰብ ትስስር ለተማሪዎች ውጤማነት” በሚል መሪ-ቃል በተዘጋጀው መድረክ፣ የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ትስስር ተመሰረተ፡፡ ‎በመርሃ ግቡሩ መክፈቻ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ እንደተናገሩት፣ “ተማሪዎቹ ገና ለጋ ወጣት ከመሆናቸው የተነሳ ከጎናቸው የሚቆም እና የሚያበረታታ ሰው ይፈልጋሉ፤ ብዙ ተማሪዎች ከቤተሰቦቻቸው በመራቃቸው እና ሁኔታዎች ስላልተመቻቹላቸው፣ ትልቅ አቅም ቢኖራቸውም ቀላሉን ችግራቸውን የሚረዳላቸው በማጣት ውጤታቸው ዝቅተኛ ሊሆን ይችላል፡፡” በማለት የቃል ኪዳን ቤተሰብ ሊሞላ የሚችለውን ክፍተት ጠቁመዋል፡፡ አስከትለውም፣ “ተማሪው ምን እንደቸገረው እና ምን መታገዝ እንደሚፈልግ ጠይቆ ከጎኑ መቆም ለዩኒቨርሲቲ ተማሪ የሚሰጠው ትርጉም ትልቅ ነው፡፡” በማለት የመርሃ-ግብሩን አስፈላጊነት ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም ለተማሪዎቹ የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ለመሆን ከአካባቢው በመጡ ግለሰቦች እና በተማሪዎቹ መካከል፣ የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ትስስር ፊርማ ስነስርዓት ተካሂዷል፤ በፊርማ ስነስርዓቱ ላይ ለመሳተፍ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮን ወክለው የመጡት አቶ ሙሉቀን እንየው ባደረጉት ንግግር፣ የቃል ኪዳን ቤተሰብ ትስስር የተማሪውን ችግር ከመፍታት አልፎ፣ በሀገር ላይ ሰላምንና አንድነትን ለማስጠበቅ የሚኖረውን ፋይዳ ገልጸዋል፡፡ እንዲሁም ከሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ ተወክለው የመጡ የሃይማኖት አባቶችም ቃለ ቡራኬ አሰምተው፣ ለቃል-ኪዳን ቤተሰብ ትስስር መሳካት ጸሎት አድርገዋል፡፡ በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር እና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተሸመ ዱላ ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር፣ “የዛሬው መድረክ ሰላማዊ የሆነ ካምፓስ ከመፍጠር እና ለተማሪዎች አካዳሚያዊ ስኬት ከማምጣት ባሻገር፣ ሀገር የምትጸናበት እና የምትኮራበት ኢትዮጵዊ ስሜት እና ኢትዮጵያዊ ባህሪ የሚፈጠርበትን ብሄራዊ ምሰሶ የተከልንበት ነው፡፡” በማለት ያለውን ሀገራዊ ፋይዳ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ የቲያትር ቤቶች አስተዳደር የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የሙዚቃ ባንድም መርሃ-ግብሩ ላይ ተገኝቶ፣ የተለያዩ ባህላዊ እና ዘመናዊ ሙዚቃዎችን በማቅረብ ድምቀት የሰጠ ሲሆን፣ የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች ባህላዊ ዘፈኖችና ውዝዋዜ እንዲሁም ዘመናዊ ዳንስ በማቅረብ ታዳሚውን አዝናንቷል፡፡

በኢፐሰዩ የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ትስስር መድረክ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ
+7
በኢፐሰዩ የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ትስስር መድረክ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ

IPD Organizes Capacity-Building Training on Organizational Transformation Ethiopian Public Service University (EPSU) Internationalization and partnership Directorate(IPD), in collaboration with the Office of the Vice President for Research and Technology Transfer, organized a half-day training program titled “Organizational Transformation, Agility, and the AI Era” for EPSU Council members on May 13, 2026 at Hidassie Hall. In his opening remarks, Dr. Amanuel Kussia, Vice President of Academic Affairs, welcomed the trainees and noted that the training is a timely and strategically important forum. "This engagement goes beyond a one-time training program; it will be strengthened through long-term collaboration with our university through professional engagement, joint initiatives, knowledge exchange, and the co-creation of innovative ideas with our academics and professional staff," Dr. Amanuel stated. He emphasized that in today’s world, universities can no longer depend on traditional administrative structures and conventional operational approaches. They must stay relevant, responsive, innovative, and impactful. "Today, organizational transformation is not an option; it has become a strategic necessity. Agility, adaptability, and customer-centered service delivery, collaboration, and partnership now define the future success of institutions." According to Dr. Amanuel ,this training is vital because the university is currently undertaking multiple interconnected reform processes of national significance. These reforms demand a new institutional culture. "The insights to be shared today will help us better understand how to be a resilient institution, strengthen institutional effectiveness, improve service culture, enhance stakeholder engagement, and foster transformational leadership across all levels of the university," he added. He also extended his appreciation to the organizing offices for their commitment to this capacity-building platform and requested that participants actively engage in the training to contribute to the ongoing transformation journey of the university and the public sector in general. Dr. Dereje Teklemaram, Director of Internationalization and Partnership at EPSU, welcomed the participants and said that "One of our directorate's key functions is to explore global best practices that support our institutional goals, invite experts to share their insights, and facilitate knowledge exchange. Accordingly, today’s program was organized to feature two highly experienced scholars who will share their extensive expertise and practical lessons with us," Dr. Dereje said. The training was facilitated by Dr. Dereje Besufekad, from Florida University and Ayenachew Assefa from Jordan Town University, USA. Both trainers brought international practices to the session, sharing global perspectives on digital transformation and institutional agility. Their presentations focused on bridging the gap between current academic structures and the evolving demands of the AI era, providing participants with actionable insights drawn from their extensive professional backgrounds. Finally, Dr. Mitiku Addis, Vice President for Research and Technology Transfer, awarded certificates of recognition to the trainers in honor of their contribution to the training session.

IPD Organizes Capacity-Building Training on Organizational Transformation
+4
IPD Organizes Capacity-Building Training on Organizational Transformation

Externally Reviewed and Validated Undergraduate Curricula 1.     College of Finance and Economics   Accounting and Finance   Economics   Logistics and Supply Chain Management   Marketing Management   Procurement and Asset Management   Public Financial Management   Tax Administration 2.     College of Social Science and Development Studies Sociology Psychology Political Science and international relations Journalism and Communication 3.     College of Urban Studies Urban Land Management & Information System Urban Planning and Design Environmental Science Urban Engineering Property Valuation Surveying Engineering 4.   College of Computing and Digitalization Software Engineering and Intelligent System Applied Computer Science Data Science and Analytics IT Infrastructure and Cybersecurity 5.     School of Law Law 6.      College of Management, Leadership and Governance     Management     Public Administration and Governance     Development Management

በኢፐሰዩ በሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ውይይት ተካሄደ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ በአካባቢው ከሚገኙ የጸጥታ አካላት ጋር፣ በሰላምና ደህንነት ጉዳይ በዘርፉ ያለውን አቅም በማቀናጀት የተሻለ ውጤ
+3
በኢፐሰዩ በሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ውይይት ተካሄደ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ በአካባቢው ከሚገኙ የጸጥታ አካላት ጋር፣ በሰላምና ደህንነት ጉዳይ በዘርፉ ያለውን አቅም በማቀናጀት የተሻለ ውጤት ማምጣትን ያለመ የውይይት መድረክ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ/ም በአስተዳደርና ልማት ዘርፍ ም/ፕሬዘዳንት ጽ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሄደ፡፡ በመድረኩ ላይ ተገኝተው ከጸጥታ አካላቱ ጋር ውይይት ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ልማት ዘርፍ ም/ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተሸመ ዱላ፣ የውይይት መድረኩ ትኩረት ከፀጥታ አኳያ አከባቢው ምን እንደሚመስል መገምገም፣ የአከባቢውን አጠቃላይ ፀጥታ ከማስከበር አንጻር እስከ አሁን የነበረውን ቅንጅት መፈተሽ እና ማሻሻል፣ በቅርቡ በዩኒቨርሲቲው የሚከናወነው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሰላም እንዲጠናቀቅ፣ ያለውን አቅም በማሰባሰብ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ማድረግ እና ለሚከናወኑ የጸጥታ ስራዎች ጥምር ኮሚቴ በማቋቋም በጋራ ቅንጅት በሚሰራበት አግባብ ላይ ለመወያየት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ በበዩኒቨርሲቲው ግቢ ያሉ የፌደራል ፖሊስ አመራሮች፤ በለሚኩራ ክ/ከተማ የመሪና አከባቢው ፖሊስ ጣቢያ እና በየካ ክ/ከተማ የላምበረትና አከባቢው ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል መከላከል እና የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡

በኢፐሰዩ የሪፎርም አጀንዳዎች ላይ የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና የአስተዳደር አገልግሎት አሰጣጥን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለማሸጋገር የሚያስችሉ የሪፎርም ሰነዶች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ሚያዝያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ ተካሄደ። በመድረኩም በተለያዩ የሪፎርም ቡድኖች የተዘጋጁ ሰነዶች ላይ ዝርዝር ግምገማ የተከናወነ ሲሆን፣ ተቋማዊ የዲጂታላይዜሽን ሂደቱን በላቀ ፍጥነት ለመተግበር የሚያስችሉ ውሳኔዎችና የቀጣይ አቅጣጫዎችም ተቀምጠዋል፡፡ የውይይት መድረኩን የመሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ በመክፈቻው እንደተናገሩት፣ የዛሬው መድረክ የዩኒቨርሲቲውን አገልግሎት አሰጣጥ ወደዲጂታላይዜሽን ለማዘመን በተለያዩ ቡድኖች ሲሰራና ሲገመገም የቆየውን ተግባር፣ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ገምግሞ የጋራ ማድረግ እና ለቀጣዩ ስራ የአፈጻጸም አቅጣጫ ለመወሰን ታስቦ የተጠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በምክክር መድረኩ ላይ የዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንቶች፣ የኮሌጅ ዲኖች እና ምክትል ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች እና ስራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡ ለውይይት የቀረቡት ሰነዶችም፣ የስልጠና እና የማማከር ፍኖተ ካርታ፣ የዓለም አቀፍ የስልጠና ፍላጎት ልየታ፣ የአሰልጣኞች ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት አሰጣጥ ዝክረ ተግባር፣ የስልጠና ፣ የሬጅስትራር፣ የቤተ መጻህፍት አገልግሎት፣ የምርምር እንዲሁም የአስተዳደር እና የካምፓስ ሰላምና ደህንነት ሥራዎችን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተዘጋጁ ሰነዶች ሲሆኑ፣ ሰነዶቹ የደረሱበትን ደረጃ የሚገልጹ ሪፖርቶች በተለያዩ የቡድን ተወካዮች ቀርበው፣ በውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች ሀሳብ እና አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ መድረኩን ሲያጠቃልሉ፣ የተዘጋጀውን ሰነድ ወደ ተግባር ለመለወጥ ከትንሹ መጀመር እንደሚገባና ዩኒቨርሲቲውም ከትንሹ ጀምሮ ከፍ ወዳለው ደረጃ ለመሄድ የሚያስችል አቋም እንዳለው ገልጸዋል፤ “የጀመርነውን የዲጅታላያዜሽን ጉዞ ሰነዶች ወደማጠቃለያው አምጥተን በተግባር እና በተጨባጭ ወደሚታይ ስራ መግባት አለብን፡፡” በማለት አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

በኢፐሰዩ የሪፎርም አጀንዳዎች ላይ የምክክር መድረክ ተካሄደ
+4
በኢፐሰዩ የሪፎርም አጀንዳዎች ላይ የምክክር መድረክ ተካሄደ

በኢፐሰዩ የኮምቲዩቲንግ እና ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ ያዘጋጀውን የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ለውጪ ገምጋሚዎች አቀረበ፡፡ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) የኮምቲዩቲንግ እና ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ (College of Computing and Digitalization) በአራት የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ሲያዘጋጅ የቆየውን የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ/ም በህዳሴ አዳራሽ ለውጪ ገምጋሚዎች አቀረበ፡፡ ለግምገማ የቀረበው የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ሶፍትዌር ኢንጅነሪንግ እና ኢንተልጀንስ ሲስተም፣ /Software Engineering and Intelligent System/ ተግባራዊ ኮምፒዩተር ሳይንስ፣ /Applied Computer Science/ ዳታ ሳይንስ እና አናሊቲክ፣ /Data Science and Analytics/ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት እና ሳይበር ሴኩሪቲ፣ /IT Infrastructure and Cybersecurity/ በሚሉት የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ገምጋሚዎቹ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተጠሩ መምህራን፣ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች እና ኤክስፐርቶች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር አማኑኤል ኩሲያ በመርሀ ግብሩ መክፈቻው ተገኝተው፣ ውድ ጊዜያቸውን ሰውተው በግምገማው ላይ ለተገኙ ተሳታፊዎች በዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፤ አስከትለውም ዩኒቨርሲቲው ከ30 ዓመት ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሲቪል ሰርቪሱ ያበረከተውን አስተዋጽኦ አውስተዋል፤ በአሁኑ ጊዜም ከመንግስት የቀረበለትን አዲስ ተልእኮ እና አደረጃጀት ተቀብሎ በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኑን ገልጸው፣ ስርአተ ትምህርቱን መከለስ ያስፈለገበት ምክንያትም፣ ተማሪዎችን በአዲሱ ተልእኮ መሰረት ማብቃት የሚችል የትምህርት ፕሮግራም እንዲኖር ታስቦ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ የኮሌጁ ዲን አቶ አለባቸው ጪጬ በበኩላቸው ለታዳሚዎቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸውን ካስተላለፉ በኋላ፣ “ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና ኢንደስትሪ የመጣችሁ እንደመሆናችሁ መጠን፣ ልምዳችሁን እና አስተያየታችሁን በማካፈል ለታሰበው የስርዓተ ትምህርት ክለሳ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ እጠይቃለሁ፡፡” በማለት ከተሳታፊዎች የሚሰጠው አስተያየት ጠቀሜታው ላቅ ያለ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ ቀጥሎም ገምጋሚዎቹ አስቀድሞ የተላከላቸውን የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ረቂቅ ሰነድ መነሻ አድርገው የተዘጋጁበትን የግምገማ ውጤት አቅርበዋል፡፡ በቀረበው የግምገማ ውጤት ላይም በተሳታፊዎቹ ውይይት ተደርጎ አስተያየት እና ምክረ ሀሳቦች ተሰጥተውባቸዋል፡፡

በኢፐሰዩ የኮምቲዩቲንግ እና ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ ያዘጋጀውን የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ለውጪ ገምጋሚዎች አቀረበ
+4
በኢፐሰዩ የኮምቲዩቲንግ እና ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ ያዘጋጀውን የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ለውጪ ገምጋሚዎች አቀረበ

የኢፐሰዩ የቀድሞ ተማሪዎች (አሉሙናይ) ማህበር መስራች ግብረ-ኃይል የሥራ ሂደት ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫ ውይይት አደረገ፡፡ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች (አሉሙናይ) ማህበ
+5
የኢፐሰዩ የቀድሞ ተማሪዎች (አሉሙናይ) ማህበር መስራች ግብረ-ኃይል የሥራ ሂደት ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫ ውይይት አደረገ፡፡ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች (አሉሙናይ) ማህበር መስራች ግብረ-ኃይል ሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ/ም በንዑሳን ኮሚቴዎች የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት እንዲሁም ንዑሳን ኮሚቴዎቹ ባዘጋጁት ረቂቅ ፍኖተ ካርታና የድርጊት መርሃ ግብር ላይ ውይይት አካሄደ፡፡ በውይይቱ ወቅት የዳታ ቤዝ አደራጅ፣ የመተዳደሪያ ቻርተር አዘጋጅ፣ እንዲሁም የተግባቦት እና ማርኬቲንግ ንዑሳን ኮሚቴዎች እስካሁን ያከናወኗቸው ተግባራት በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪም ንዑሳን ኮሚቴዎቹ ባዘጋጇቸው የፍኖተ ካርታ እና የድርጊት መርሃ ግብር ረቂቆች ላይ ሰፊ ምክክር የተደረገ ሲሆን፣ ለምስረታ ሂደቱ መሳካት ይረዳሉ የተባሉ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ዩኒቨርሲቲዎች የአሉሙናይ አደረጃጀት ተሞክሮዎች ቀርበው እንደ ግብዓት ጥቅም ላይ እንዲውሉ ውይይት ተደርጎባቸዋል። በመጨረሻም የግብረ ኃይሉ ሰብሳቢ ዶ/ር ዋቅጋሪ ነገሪ ምንም እንኳን ግብረ ኃይሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ቢሆነውም፣ በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ የተሰራው ስራ የግብረ ኃይሉ አባላት ለስራው ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያመላክት መሆኑን አመላክተው በቀጣይም ይህ ቁርጠኝነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪአቸውን አቅርበዋል፡፡

EPSU Holds Undergraduate Programs External Curriculum Validation Workshop Ethiopian Public Service University (EPSU) Held Undergraduate Programs External Curriculum Validation Workshop on May 4, 2026 at EPSU Training Center Syndicate Rooms. During the workshop, seventeen undergraduate curricula from the College of Finance and Economics, the College of Urban Studies, the College of Management, Leadership and Governance, and the School of Law were externally validated. In his opening remarks, Dr. Amanuel Kussia, Academic Vice President of EPSU, stated that it is a privilege to have reviewers from applied science universities, the public sector and EPSU faculty members, as each group brings a distinct and essential perspective. He also noted that the university is currently undertaking a comprehensive institutional reform, aimed at transforming the university into a high-performing and nationally impactful center of excellence in public services. The reform integrates three major national reform initiatives; Autonomus University Status, differentiation related reform and public service and governance reform. This transformation aims to enhance equity, quality, relevance, responsiveness, accountability and impact ensuring that teaching, training, research and community engagement directly contribute to improve public sector performance and nation development, Dr. Amanuel noted . According to Dr. Amanuel, over the past months, the university has engaged in an intensive curriculum revision and development processes that covers 25 academic programs. The guiding principles throughout the process include, the programs alignment with the national priorities and development goals, respond directly to the evolving needs of the public sectors and society, meets the national and international institutional qualities and accreditation standards, balance theory and practices, aligned with Applied University Framework , consider digitalization and digital technology; and equip the graduates with practical competence , innovation capacity and strong ethical grounding. He also thanked the reviewers, curriculum committees and participants for their efforts and contributions. In his welcoming address, Ato Albachew Goshim , Director for Academic Programs, highlighted the university's legacy, noting its significant contributions to national development over the past three decades. However, he emphasized that to remain relevant, the university must align its academic programs with contemporary demands. Recognizing that education is inherently dynamic and requires the integration of emerging knowledge, he noted that curricula demand periodic revision and rigorous evaluation. Consequently, the university has established the review and redesign of programs, alongside the development of modern curricula, as a central pillar of its reform agenda. Ato Alebachew further remarked that this comprehensive process involved the dedicated participation of faculty members. Following extensive internal reviews, these programs have now been presented for external validation. He finally concluded by expressing his deep gratitude to the members of the curriculum committees for their tireless efforts throughout this transition.

EPSU Holds Undergraduate Programs External Curriculum Validation Workshop
+5
EPSU Holds Undergraduate Programs External Curriculum Validation Workshop

ኢፐሰዩ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላን ልማት ቢሮ የፋይዳ ግምገማ የመነሻ ሪፖርት አቀረበ፡፡ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር የ10ኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን አፈጻጸም ዉጤታማነት እና ተጽዕኖ የግምገማ ጥናት ለማካሄድ በገባው ውል መሰረት፣ የፋይዳ ግምገማ የመነሻ ሪፖርቱን ከአዲስ አበባ አስተዳደር ቢሮዎች እና ከሌሎች ተቋማት የተጠሩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ/ም በቢሮው የመሰብሰቢያ አዳራሽ አቀረበ፡፡ የአዲስ አበባ ፕላን ላማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አደም ኑሪ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ፣ የከተማ አስተዳደሩ 10ኛው መዋቅራዊ ፕላን ሊጠናቀቅ አንድ አመት የሚሆን ጊዜ እንደቀረው እና ለ11ኛው መዋቅራዊ ፕላን ዝግጅት አስቀድሞ ለመዘጋጀት ክብርት ከንቲባዋ የሚመሩት የፕላን ቦርድ መቋቋሙን ገልጸው፣ “ዛሬ የሚቀርበው የመነሻ ሪፖርት 10ኛው መዋቅራዊ ፕላን ምን ምን ውጤቶችን አስገኝቷል? ምን ጉድለቶችስ ነበሩበት? የሚለውን ለመፈተሸ እና ለ11ኛው ዙር መዋቅራዊ ፕላን ግብዓት ለማግኘት የሚያስችሉ ጭብጦችን የሚዳስስ ነው፡፡” በማለት ዓላማውን አስረድተዋል፡፡ ከዚያም፣ በመርሃ ግብሩ ላይ ለተገኙ ባለድርሻ አካላት ከመጡበት ተቋም ተልዕኮ አንጻር ያልተካተቱ የፋይዳ መገምገሚያ ጭብጦች ካሉ በማንሳት እና መረጃ በመስጠት ጭምር እንዲሳተፉ በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡ በመቀጠልም የጥናት ቡድኑ አስተባባሪ ፕሮፌሰር ሳምሳን ካሳሁን ፣ ለጥናቱ ማጣቀሻ እንዲሆን ከቢሮው በተሰጠው ዝርዝር መግለጫ (TOR) መሰረት የከተማ አስተዳደሩን ቢሮዎችን እና የተለያዩ አደረጃጀቶችን ታሳቢ በሚያደርጉ ዘጠኝ ጭብጦች ተለይቶ በጥልቀት እና በዝርዝር የተዘጋጀውን የፋይዳ መገምገሚያ የመነሻ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ የመነሻ ሪፖርቱ በዝርዝር ከቀረበ በኋላም፣ ከታዳሚዎች በርካታ ሀሳቦች፣ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች ቀርበው፤ የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ምትኩ አዲሱ እና ፕሮፌሰር ሳምሶን ካሳሁን በጋራ ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ የሪፖርቱን ይዘት እና አቀራረብ አስመልክተው አቶ አደም ኑሪ ሲናገሪ፣ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ጥናቱን ለማካሄድ ከቀረቡት መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች መካከል የቀረበውን መስፈርት አሟልቶ እና አግባብነት ያለው ዋጋ አቅርቦ በከፍተኛ ውጤት ያሸነፈ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ እንዳንዱን የከተማውን ጉዳይ ታሳቢ አድርጎ ለቀረበው ሪፖርት ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በማስከተልም “ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከትርፍ ይልቅ ማህበራዊ ሀላፊነቱን የሚወጣ ተቋም መሆኑ ይታወቃል፤ ስለዚህ በጋራ ውጤታማ ስራ እንሰራለን ብለን እናምናለን፡፡” በማለት ከዩኒቨርሲቲው ጋር በጋራ ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡

ኢፐሰዩ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላን ልማት ቢሮ የፋይዳ ግምገማ የመነሻ ሪፖርት አቀረበ፡፡
+6
ኢፐሰዩ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላን ልማት ቢሮ የፋይዳ ግምገማ የመነሻ ሪፖርት አቀረበ፡፡

የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዝ መሰረተ የዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ በ23/08/2018ዓ.ም ባደረገው 3ኛ መደበኛ ስብሰባ እና በህግ በተሰጠው ስልጣን መሰረት የዩኒቨርሲቲውን ኢንተርፐራይዝ መስርቷል ። የኢንተርፕራይዝ አላማ ለዩኒቨርስቲው ዘላቂ የገቢ ምንጭ በመፍጠር የዩኒቨርሲቲውን ዋና ዋና ተግባራት ማለትም መማርና ማስተማር፣ ምርምር፣ ሥልጠና፣ ማማከር እና ማህበረሰብ አገልግሎት በጥራትና በዘላቂነት እንዲፈጸሙ መደገፍ ነው። በዚሁ መሰረት ኢንተርፕራይዙን እንዲመሩ:- 1. ዶ/ር አዜብ አሰፋ ......የኢንተርፕራይዙ ዋና ስራ አስኪያጅ 2. ዶ/ር ዘላለም እጅጉ..... የቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ስራ አስኪያጅ 3. ወ/ሮ ፍሬህይወት አበራ.....የአስተዳደርና ፋይናንስ ዘርፍ ምክትል ስራ አስኪያጅ ሆነው ተመድበዋል። ስራ አመራር ቦርዱ አዲስ ለተመደቡት አመራሮች መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው ምኞቱን ይገልፃል። ሚያዝያ 24/2018ዓ.ም የዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ

የኢፐሰዩ የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር መስራች ግብረ-ኃይል በይፋ ማህበሩን የመመስረት ስራውን ጀመረ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር መስራች ግብረ-ኃይል በይፋ ማህበሩን የ
+4
የኢፐሰዩ የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር መስራች ግብረ-ኃይል በይፋ ማህበሩን የመመስረት ስራውን ጀመረ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር መስራች ግብረ-ኃይል በይፋ ማህበሩን የመመስረት ስራውን ጀመረ፡፡ ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ሴኔት አዳራሽ ይፋ በሆነው ግብረ-ኃይሉን ስራ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት መመስረት የዩኒቨርሲቲውን መልካም ስም ለመገንባትና አጋርነት ከማጠናከር አንጻር የሚኖረውን ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው፤ የግብረ ኃይሉ ተቀዳሚ አላማም ደረጃውን የጠበቀ የዩኒቨርሲቲውን የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር ማደራጀት መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡ ስምንት አባላትን ያቀፈው ይህ ግብረ-ኃይል፣ ከፕሬዚዳንቱ የተሰጠውን አቅጣጫ መነሻ በማድረግ ዝርዝር የሥራ ዕቅድ አዘጋጅቶ፣ የቀድሞ ተማሪዎችን (Alumni) መረጃ የሚያደራጅ፣ የመተዳደሪያ ደንብና ሕጋዊ ሂደቶችን የሚያከናውን፣ እንዲሁም የኮሚኒኬሽንና ማርኬቲንግ ሥራዎችን የሚያሳልጡ ሦስት ንዑሳን ቡድኖችን በማዋቀር ተግባሩን በይፋ ጀምሯል። በቀጣይም የማህበሩን የምስረታ ሂደት አስመልክቶ ለማህበረሰቡ ወቅታዊ መረጃዎችን ተደራሽ በማድረግ፣ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የምስረታ ሂደቱን ለማጠናቀቅ በትጋት እንደሚሰሩ የግብረ-ኃይሉ አባላት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡

CSSDS holds External Curriculum Validation Workshop College of Social Science and Development Studies held External Curriculum Validation Workshop on April 28, 2026 at Hidasse Hall. In his opening remarks, Dr. Amanuel Kussia noted that the workshop is not just an academic exercise, but a critical milestone in the broader transformative reform the university is undertaking. This reform is comprehensive in scope, ambition, and strategy, reflecting an intent to position the university as a center of excellence. He emphasized that curriculum reform stands at the core of this transformation. Over the past several months, the university has engaged in an extensive curriculum revision and development process. This process has been guided by critical aspects, including program relevance to national priorities and industry needs, alignment with national and global standards, and the goal of equipping graduates with practical skills, innovation capacity, and a strong ethical foundation. Addressing the participants and external reviewers, Dr. Amanuel stressed that their presence is vital, as internal efforts alone are insufficient to guarantee quality and relevance. "We are honored to have such distinguished scholars and experienced practitioners with us. Your contributions as evaluators are essential for our curricula, and we genuinely welcome your feedback and professional suggestions," he added. In his welcoming speech, Dr. Waqigari Negeri, Dean of College of College of Social Science and Development Studies, welcomed the evaluators and participants, noting that the workshop was unique due to the diverse range of attendees. The event brought together representatives from various organizations in Addis Ababa, as well as participants from Embassies of China, Djibouti, Somaliland, and South Sudan. He also highlighted that the workshop takes place amidst a holistic transformation agenda that impacts every function of the university. "This is the first of its kind in the history of the university, that is why we say special occasion during special time," he added. Dr. Waqigari further explained that the curricula were developed based on the "Outcome-Based Education" philosophy. He expressed confidence that the external reviewers would provide vital input to align the curricula with contemporary global trends and academic phenomena. During the workshop, four curricula Political Science and International Relations, Psychology, Sociology, and Journalism and Communication prepared by the College Curriculum Committee were presented. Reflections from external reviewers were shared, and an extensive discussion was held on the issues raised by the presenters and evaluators.

CSSDS holds External Curriculum Validation Workshop
+4
CSSDS holds External Curriculum Validation Workshop